በሳውዲ አረቢያ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ‹‹የዜጎቼ ሰብአዊ ክብር ተደፍሯል›› ሲል የሳውዲ ሚዲያዎችንና አንዳንድ ግለሰቦችን ሊከስ በዝግጅት ላይ መሆኑ ተገለፀ፡፡
ሪያድ የሚገኘው የኢትዮጵያ ኤምባሲ አምባሳደር ጉዳዩን አስመልክተው በሰጡት መግለጫ በአገሪቱ የሚፈፀሙ ማናቸውም በመሳሪያ የታገዙ የዘረፋዎች፣ የውንብድናና የማጭበርበር ድርጊቶች ‹‹ኢትዮጵያውያን ፈፀሙት›› እያሉ ማውራት ከጊዜ ወደ ጊዜ እየጨመረ የመጣ ከመሆኑ በተጨማሪ በአገሪቱ የተለያዩ የቴሌቪዥን ፕሮግራሞችና በሌሎች ጋዜጦች ላይ ይህንኑ ስሜት ማንፀበረቅ እየተለመደ መጥቷል፡፡ ይህንን ተከትሎ ማንኛውም ኢትዮጵያዊ እንደሌባና አጭበርባሪ እየታየ መሆኑንና ዜጎችም ስራ ለመቀጠር አስቸጋሪ ሁኔታዎች እየገጠማቸው መሆኑን ገልፀዋል፡፡


