Sunday, March 20, 2016

"ኢህአዴግ ነው ቃሉን የሚያጥፍ። ኢህአዴግ ይመስል..." ይሄ ነበር የወሬው መነሻ....

"ኧረ፥ ምን ቃል ይበላል? ቃል አክባሪ ነው።" - ለማደናቆርና ለማናዘዝ።
ኢህአዲግማ ቃል አባይ ነው። ከተፈጠርኩኝ ቃሉን እንዲህ የሚበላ አንድ ሰውም አላየሁም።
ሌላ ሌላውን እንተወው... "20 ዓመት ተፈረደበት" ይባልና ሀብት ያለው በዛ ያለ ብር ሲሰጥ ይቀነስና ይፈታል። ብሩ ከተጠራቀመ 20 ቀንም አይፈጅም፤ ወንጀል ሰራ የተባለው ከቤተሰቡ ጋር ይቀላቀላል። ወንጀል ያልሰራው ምስኪን፣ ነካን ካሉ መቼም አይፈታም። ፃፉ ቢሉም ሲጽፉ ያስራሉ። ስብሰባ ጠርተው የጠሉትን እና ዐይን የጣሉበትን ከስብሰባ ይለቅማሉ።
በኃይለስላሴ ዘመን እንዲህ ያለ ቃል ማጠፍ የለም።
በመንግስቱም ቢሆን እንዲህ የለም። ሰዉ ቁርጡ ይነገረዋል፥ ከዚያ ሲወጣ ይቀጣል። ይሄኛው ግን ወሬው ሌላ፣ ስራው ሌላ።
በእርግጥ ውኃ ሳይሆን ቧንቧው በዝቷል በኢህአዴግ ጊዜ።

እነ ሌንጮ በጎቹን ለተኩላዎች አሳልፈው መስጠት የለባቸውም | ናኦሚን በጋሻው

naomibegachaw@gmail.com
በኦሮሞ ዴሞክራቲክ ግንባር፣ ኦዴግ ዉስጥ ያሉ አመራሮች በጣም የተከበሩ በሳል አመራሮች ናቸው። ለአመታት በትግሉ ዉስጥ ያለፉ፣ በርግጥም ለኦሮሞው ማህበረሰብ የሚበጀዉን እና የሚጠቅመዉን የተረዱ። በኦሮሞዉና በሌላው ማህበረሰብ መካከል አለመተማመን እና መጠራጠር እንዳለ ፣ ይሄንንም ለመግዛት እና ለመበዝበዝ እንዲያመቸው ሆን ብሎ ያደረገው ሕወሃት እንደሆነ በሚገባ የሚያውቁ። የኦሮሞው ማህበረሰብ ከሌላው ጋር ያለውን ግንኙነትና ትስስር አጠናክሮ ለሁሉም እኩል የሆነች ኢትዮጵያን ለመገንባት ይቻል ዘንድ ፍላጎት አላቸው። በፖለቲካ አመለካከታቸው ጥሩ መስመር ላይ ያሉ ነው የሚመስሉት።
ሆኖም እነ ኦቦ ሌንጮ ጽንፈኛ የሆኑትን እነ ጃዋር መሐመድና፣ ገረሱ ቱፋ ያሉ ወጣት አክራሪዎችን የፈሩ ይመስላል። እነ ጃዋር በሶሻል ሜዲያው እና በሚቆጣጠሩት የኦሮሞ ሜዲያ ኔትዎርክ ብዙ ስለሚጮኹ ብዙ እየተሰሙ የነኦቦ ሌንጮ ድምጽ እንዳይሰማ አድርገዉታል ። Outshine አድርገዋቸዋል።

‪#‎ሀበሻ_ማን_ነው‬

ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም የኦሮሞን ህዝብ የነፃነት ትግል(The oromo movement as a Nomadic,Destructive, and Purposeless) በማለት በመጤነት ፥በዓላማቢስነት፥ በወራሪነት፥ በአውዳሚነት፥ በጎርፍነት ይመድቡና "አማሮች በጎጃምና በደንብያ ሁነው ትግሮችም በግምባራቸው ጠንክረው ባያግዱት እንደፈሳሽ ውኃ እስከ ምስር( ግብፅ) ይፈስባት ነበር።

በአቶ ሌንጮ ለታ ኢሳት ጋር የተደረጌ ቃለ ምልልስ ላይ…

ምን እንደሆነ ባላውቅም የዛን ትውልድ ታሪክ ለማውቅ በጣም እጓጓለው፡፡ከተፈጥሮአቸው ይሁን ይከተሉት ከነበር ህቡዕ የፖለቲካ አደራጃጀት በማላውቀው መልኩ ስበዙ ሚስጥረኞች ናቸው።
ለምሳሌ ሻብዕያና ወያኔ መንግስትም ሆነው ድብቅ ናቸው፡፡አንድ ጊዜ አቶ በረከት ስምኦን ይንን ድብቅነታቸውን ተናግሮ ነበር።በአንጻራዊነት ወያኔ ሳይሻል አይቀርም የኛ የፖለቲካ አምላክ እያጋጨ ይከፈሉና አንዱ አንዱን ስነካ በመሃል እኛ ወሬ እንቃረማልን።( የወያኔ ሁለት ቦታ መከፈል ልብ ይሏል 1993)።ሻብዕያ እስከ ዛሬ ለዜጎቹም ሆነ ለታሪክ የሚሆን የትግሉን ሚስጢር ያውጣ አይመስለኝም።
በደርግ በኩል ከሞላ ጎደል አያሌ መጻሃፍ ስለ ተጻፉ ችግር የለውም።በኢህአፓ በኩልም ብዙ ተብሏል።
ነገር ግን እንደ ዜጋም እንደ ተከታይ ትውልድም የአባቶቻችንን ታሪክ ማውቅ ነበረብን።እንዳውም ሞተው ከማለቃቸው በፊት ለታሪክ ሰነድ የሚሆን ዳጎስ ያለ መጽሃፍ ቢያሳትሙልን ሌላው ቢቀር "ነፍስ ይማር" እንላለን።

ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም በብሔራዊ መግባባት ላይ ከምሁራን ጋር ተወያዩ

  • ‹‹አገራዊ ታሪክንና የብሔረሰብ ታሪክን ለማጣጣም ችግር እየተፈጠረ ነው››
  • ‹‹ብሔርን ከብሔር ከማናቆር ያለፈ ፋይዳ የሌለው ሐውልት እስከመገንባት ተደርሷል››
  • ‹‹የተለየ ሐሳብ ያላቸው በፀረ ሽብር፣ በሙስናና በግብር አዋጆች ይጠለፋሉ›› በምሁራን የቀረቡ ጥያቄዎች
ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ከተለያዩ የአገሪቱ ከፍተኛ ትምህርትና የምርምር ተቋማት ከተወጣጡ ምሁራን ጋር፣ በብሔራዊ መግባባትና በበርካታ አገራዊ ፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ ውይይት አደረጉ፡፡
መንግሥት ‹‹የኢትዮጵያ ህዳሴ›› በሚል መሪ ቃል መላው የኢትዮጵያ ሕዝብን ማነቃነቅና ብሔራዊ መግባባት መፍጠር እንደሚፈልግ ማብራሪያ በመስጠት ማክሰኞ መጋቢት 6 ቀን 2008 ዓ.ም. ውይይቱን ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ከፍተውታል፡፡ በዚህ የመግቢያ ንግግራቸው መንግሥት ኅብረተሰቡን ለማንቀሳቀስ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን፣ እንዲሁም ሌሎች ፕሮጀክቶችን አገራዊ መግባባት ለመፍጠር በሚያስችል አኳኋን ቀርፆ ተግባራዊ ለማድረግ እየጣረ ቢሆንም፣ ፖለቲከኛው ጥግ ጥጉን ይዞ ከመታኮስ ባለፈ የመቻቻልና የመወያያት ዴሞክራሲያዊ ባህልን ማዳበር እንዳቃተው ገልጸዋል፡፡

የእዉቅና መረጃ . .

የእዉቅና መረጃ . .
የብሐራዊ መረጃዉ ዳይሬክተር ጌታቸዉ አሰፋ በጥቂቱ...
ወያኔ ሀገራችንን እንደወረረ በመጀመሪያ የተቆጣጠረዉ ባዶ ስድስትን ነበር ባዶ ስድስት የእስር ቤት መገለጫ ሲሆን በእነርሱ አጠራር የኮድ ስም መሆኑ ነበር ወያኔያዊያን የማረሚያ ቤቶችን በቁጥጥራቸዉ ስር እንዳደረጉ ቀድሞ ሲያገለግሉ የነበሩት የማረሚያ ቤቶች አባላት በሙሉ በመሰወራቸዉ ምክንያት እስረኞችን በአግባቡ መያዝ ተሳናቸዉ። ስለዚህም የማረሚያ ቤቶች ሰራቶኞችን በአዋጅ መጥራቱ አስፈላጊ ሆኖ ተገኘ።
ሰራተኞቹ በአዋጅ ተጠርተዉ እንደመጡ የማረሚያ ቤቱን ሰነዶችና መረጃዎችን እንዲሁም በሰራተኖች ዙሪያ ላይ ግምገማ ለማካሄድ በማስፈለጉ ምክንያት ህወሃት አሉኝ ከሚላቸዉ ግለሰቦች መካከል ከማእከላዊ ወንጀል ምርመራ የምርመራ ቡድን ሐላፊ የሆነዉን በሻለቃነት ማእረግ የሚያገለግል ግለሰብ ወደ ማረሚያ ቤቶች ላከዉ! ሰዉየዉ በማረሚያ ቤቶች ዉስጥ ለአንድ ወራት ያህል ሰነዶች ሲያገላብጥ ቆይቶ አጠቃላይ አባላትን በመሰብሰብ ግምገማዉን ጀመረ።

ግልጽ ደብዳቤ ለጠ/ሚኒስትር ኃይለማርያም

ግልጽ ደብዳቤ ለጠ/ሚኒስትር ኃይለማርያም
Written by አስፋ ጫቦ
ግልጽ ደብዳቤ ለጠ/ሚኒስትር ኃይለማርያም
ይህን ደብዳቤ እንድጽፍልዎ ያስገደደኝ፣ ዛሬ አገራችን የገባችበት ማጥ ነዉ። ከፖለቲካነትን ይልቅ የ“ኧረ ምን ይሻላል! ኧረ ምን ይበጃል !” ደብዳቤ አድርገው ቢያዩልኝ ደስ ይለኛል። እንደ መፍትሔ አፈላላጊ የአገር ሽማግሌ ድምፅ ሆኖ እንዲታይልኝ/ቢታይልኝ እወዳለሁ። ነውም!! ”የጋራ ቤታችን” እንዲህ ማጥ ውስጥ ስትዘፈቅ የሚያይ አገር ወዳድ ሁሉ ድምጹን የመስማት ግዴታ ያለበት ወቅት ላይ ነን ብዬ አምናለሁ። ከፖለቲካ አመለካከት ልዩነት ይልቅ የአገራችን የኢትዮጵያ መሰንበት፤ ከዚያም “በነጻነትዋ ለዘላለም ትኑር!” ማለት ይቅደም እንደማለት ነው። በደርግ ቋንቋ “ኢትዮጵያ ትቅደም!” እንደማለት!