Friday, June 27, 2014

በፍረጃና በጥላቻ የተዋጡ 23 ዓመታት

ጌታቸው አምሳሉ በሶሻል ሚዲያ በተለይ ደግሞ በፌስቡክ ስሙን እየቀያየረ የሚጽፍ ወጣት ነው፡፡
በተለያዩ ጊዜያት በተለያዩ ጉዳዮች ላይ የሚሰጣቸው አስተያየቶች ተመሳሳይ ቢሆኑም በተለያዩ የአማርኛ፣ የኦሮሚኛና የትግርኛ የሚመስሉ የብዕር ስሞች ይጽፋቸዋል፡፡ ስሞቹን ለመናገር ግን ፈቃደኛ አይደለም፡፡ 
ከሦስቱም ብሔሮች ስሞችን ይወስዳል፡፡ ብዙም አበላልጦ አያያቸውም፡፡ በተለያዩ ስሞች ለሚሰጣቸው አስተያየቶች የሚቀርቡለት ትችቶችና ነቀፌታዎች ግን የተጠቀመውንም ስም መሠረት ያደረጉ እንደሆኑ ይናገራል፡፡ በጣም ጥቂቶች ግን በተለያዩ ስሞች እየገባ ለሚሰጣቸው አስተያየቶች የሐሳቡ ቁም ነገር ላይ ብቻ ተመሥርተው አስተያየቶች እንደሚሰጡት ያስረዳል፡፡ ቁጥራቸው እየጨመረ ወይስ እየቀነሰ ስለመምጣቱ ተጠይቆ ነበር፡፡ የፌስቡክ ተጠቃሚ ወጣቶች ቁጥር እየጨመረ በመምጣቱ የፌስቡክ ጓደኞቹም ቁጥር ከፍ ብሏል፡፡ ሐሳባቸውን በምክንያት አስደግፈው የሚጽፉ በርካታ ሰዎች ቢኖሩም፣ በሚለጥፈው ወይም ፖስት በሚያደርገው ሐሳብ ከፍተኛውን ቦታ የሚይዙትና እንደልባቸው የሚጽፉት ግን ‹‹ፅንፈኞች›› መሆናቸውን፣ ኃላፊነት እንደማይሰማቸውና አብዛኛዎቹም በውጭ አገር እንደሚኖሩ አረጋግጧል፡፡

ውስጣዊ ጥራታችን በማጠናከር ጠንክረን እንውጣ !!

ከአስገደ ገ/ስላሴ ወ/ሚካኤል
መቐለ 

 በአንድ “ዲሞክራሲያዊ ነኝ” የሚል ፖለቲካዊ ፓርቲ ውስጣዊ የአንድነትና የትግል 
ህይወት ከሌለው ውጤቱ ውድቀት ነው። 
 በ60ዎቹ ዓ.ም በሃገራችን ፀረ የተበላሸ ዘውዳዊ ስርአትና ፋሽሽታዊ ደርግን በመቃወም ይታገሉ የነበሩ ወገኖች አወዳደቅ 
ስንመለከት ፤መጀመርያ መደራጀቱ ሲጀምሩት የሃገራችን ሙሁራን፤ተማሪዎች ፤ወዛደሮች ጨቋኝ ስርአቶችን አስወግደው 
ዲሞክራሲያዊና ህዝባዊ መንግስት ለመመስረት የኢትዮጵያ አርሶ አደሮች ፤ወዛደሮች፤ተማሪዎችና ሌሎች ማ/ሰብ 
በመንቀሳቀስና በመደራጀት መልካም የሚባል የኢትዮጵያ አንድነት የሚያንፀባርቅ እንቅስቃሴ አድርጓል፡፡ 
 የኋላኋላ ግን ደርግ ሁሉም ነገር የዲሞክራሲያዊ ጥያቄ በመዝጋቱ በአንድነት ይንቀሳቀሱ የነበሩ የዩኒቨርሲቲ ተማሪዎች ፡ 
ሙሁራኖች መሰረታዊ ባልሆነ ልዩነት፡አንዳንዶቹ “የብሄር ጭቆና ጥያቄ መመለስ አለበት” ፡አንዳንዶች ደግሞ “የመደብ ገዢዎች ከተገረሰሱ ሁሉም ነገር አልጋ 
በአልጋ በሆነ መንገድ ይፈታል”፡በማለት ሌሎች ደግሞ “ለደርግ መታገል አያስፈልግም በውስጡ ሁነን ማስተካከል ይቻላል”፡በማለት ከደርግ ታረቁ፡፡

ምኒልክ እና አርሲ

ወርቁ ፈረደ

ኢትዮጵያዊው ቢስማርክ ዳግማዊ ምኒልክ፣ አገር ለማስገበር ካደረጓቸው ዘመቻዎች ውስጥ ትልቅ ምከታ የገጠማቸው አርሲ ላይ ነው፡፡ 
ምኒልክ በአርሲዎች ክንድ ተከታታይ ሽንፈት ከቀመሱ በኋላ፣ በራስ ወልደ ገብርኤልና በራስ ዳርጌ እልክ አስጨራሽ ዘመቻ አማካኝነት፣ አሸንፈው 
አርሲን ወደ ግዛታቸው ቀላቀሉት፡: በጦርነቱ ከአስገባሪውና ከገባሪው ወገን አያሌ ወታደሮች አልቀዋል፡፡ ውጊያው የተካሄደው፣ነፍጥ በታጠቁ የንጉሱ 
ወታደሮችና ከጦርና ጋሻ ፈረስ ውጭ ምንም በሌላቸው የአርሲ ጎበዞች መካከል በመሆኑ፣ ከተከላካዩ ወገን ያለቀው በቁጥር እንደሚልቅ እሙን ነው፡፡ 
የአርሲ ጦርነት ከተካሄደ ከጥቂት አመታት በኋላ፣ ወደ ኦሮሞ ምድር የደረሰው ደ ሳልቪያክ የተባለ የፈረንሳይ ሀዋርያ ከአርሲዎች በሰበሰበው መረጃ 
ተመስርቶ እንደጻፈው፣ ራስ ወልደገብርኤል የአርሲዎችን አይበገሬነት ለመስበር ባንድ ቀን ብቻ የአራት መቶ አንጋፋዎችን ክንድ አስቆርጠዋል፡፡ይህ 
ጻሀፊ፣ ክንዳቸውን ካጡት ትልልቅ ሰዎች ጥቂቶቹን ባይኔ በብረቱ አይቻለሁ ብሏል፡፡ 

Sunday, June 22, 2014

ፖለቲከኞቻችን የእስከዛሬ ሃሳባቸውን “ዲሊት” ያድርጉት!

አዲሱ ንቅናቄ - የምስጋና አብዮት ነው! 

     ለሁሉም ጊዜ አለው ተብሏል… አሁን ጊዜው የምስጋና አብዮት ነው፡፡ የአረቡን ህዝባዊ አመፅ አይተነዋል፡፡ የቀለም አብዮት የተባለውንም በቲቪ መስኮት በእነ ዩክሬን ታዝበነዋል፡፡ እና ምን ቀረን? ሁሉም ተሞክሯል እኮ! ሰላማዊ ሰልፉም፣ የእሪታ ቀኑም፣ ቦይኮት ማድረጉም ወዘተ… ኧረ ምን ያልተሞከረ አለ! 
አሁን በአንድ ነገር እንስማማ፡፡ በድሮው መንገድ እየሰራን አዲስ ውጤት (ለውጥ) መጠበቅ ጅልነት ነው፡፡ አሰራራችንን ሳይቀይር ለውጥ ሊመጣ ጨርሶ አይችልም፡፡ ኢህአዴግ ነፍሴ እንደሚለን፤ “ይህ የምርጫ ጉዳይ ሳይሆን የህልውና ጉዳይ ነው፡፡” (It is a must! ብያችኋለሁ) እናላችሁ.. ዛሬ ስለምስጋና አብዮት እናወራለን፡፡ ምስጋናና አብዮት ምን አገናኛቸው ይሆን? በነገራችሁ ላይ ይሄ ስብከት አይደለም፡፡ እንደ ዕውቀት (መረጃ) ሽግግር ብትመለከቱት ደስ ይለኛል፡፡ የምስጋና አብዮት አመንጪዋ ማን መሰለቻችሁ? ታዋቂዋ አውስትራሊያዊት ደራሲ ርሆንዳ ባይርኔ ናት፡፡ The secret እና The power የተባሉ መፃህፍቷን በሚሊዮን ቅጂዎች የቸበቸበችውን ደራሲ ማለቴ ነው፡፡

የአሜሪካ ትላልቅ ኩባንያዎች ከፍተኛ ኃላፊዎች ስለትምህርት ደረጃቸው ምን ብለው ዋሹ?

ቀለም የዘለቃቸው ዋሾዎች ከፖለቲከኞችም ይብሳሉ ተባለ!

           ባለፈው ሳምንት የአብዛኞቹ ሚዲያዎቻችን ሰበር ዜና የሆኑት ግለሰብ ለዚህ “ልዩ ጽሑፍ” መሰናዳት ሰበብ እንደሆኑኝ ለመግለጽ እወዳለሁ፡፡(እውነቱን መናገር ይሻላል ብዬ እኮ ነው!) ምስጋናውን ለማን ማቅረብ እንዳለብኝ ግን እርግጠኛ ስላልሆንኩ ለጊዜው “የምስጋና ማዕቀብ” ማድረጉን መርጬአለሁ፡፡ እናም በቀጥታ ወደ ርዕሰ ጉዳያችን እንግባ፡፡ ዛሬ አምዱ ለዋሾዎች ተለቋል (ድሮስ የማን ነበር አትሉኝም?)
ባለፈው ቅዳሜና እሁድ ምን ሰማሁ መሰላችሁ? እኚህ የትምህርት መረጃቸውን አስመልክቶ ዋሽተዋል የተባሉት ግለሰብ እንግዲህ አነቃቂ ንግግሮችን በማድረግ ይታወቃሉ አሉ ?! እናላችሁ ---- በሳቸው የማነቃቂያ ንግግር ተነሳስተው ለውጥ ያመጡ አንዳንድ ግለሰቦች በጣም ተናደዱ ተባለ፡፡ ለምን መሰላችሁ? የውሸት አነቃቅቶናል ብለው እኮ ነው።

Friday, June 20, 2014

አህያ ለምን ኩሊ ሆነ

አንዳንድ ጥያቄዎች በጣም አስቸጋሪ ናቸው ። ለምሳሌ አህያ ለምን ኩሊ ሆነ ተብዬ ተጠይቄ አውቃለሁ ። የሚገርመው ጥያቄውን የጠየቀኝ አንድ የ ሁለታኛ ክፍል ተማሪ ነው። እውነት እኮ ነ " እንደነዚህ ልጆች/ ሕጣናቶች ካላሰባችሁ መንግስተ ሰማያት አትገቡም " የተባለው። በይበልጥ እንደዚህ ልጅ ። ግን አህያ ለምን ኩሊ ሆነ ? ሌሎች የጋማ ከብቶች እንደ አህያ ለሸክም የሚመች ጀርባ ስለሌላቸው ወይስ አህያ ሸክምን የ አርባ ቀን እድሌ ነው ብሎ ተቀብሎት ? በ እሪት ዘፍጥረት አባትችን አዳም የእንስሳ ስም ያወጣ እንደነበር ታላቁ መጽሐፍ ይናገራል ። ምናልባት ለሚስቱ ስም ያወጣ የመጀመሪያውም የመጨረሻውም ወንድ አዳም ይሆናል ። ( በዚህ ጉደኛ እና ሙደኛ ዓለም ላይ ስለ ብዙ ነገር እርግጠኛ መህን ባይቻልም)። ቢቻልስ ምንም የምትቀይረው ነገር የለም። ለምሳሌ የሰው ልጅ ስለ አየር ትንበያ ያለው እውቀት እየላቀ መምጣቱ አዳም ስም ሲሰይም ከነበረው የመጀመሪያ እውቀቱ ብዙ የራቀም አይደለም ።

ነገን ለማስተካካል ዛሬ ላይ መነጋገር…

ፈረንጆቹ ፣ “አንድ ክፉ ነገር አሸንፎ የሚወጣው በጥቂት ሰዎች ዝምታ ምክንያት ነው” የሚል አባባል አላቸው፡፡ በዚህ ድሀ ሕዝብ ጫንቃ ተምረው፣ ኑሮአቸውን ካደላደሉ በኋላ አገር አማን ነው ብለው ዝምታን መርጠው የሚኖሩ ኢትዮጵያዊያን፤ ቢያንስ የሕሊና ወቀሳ እንደሚነዘንዛቸው ሊክዱ አይችሉም፡፡ በዚህ አደገኛ ጊዜ ዝምታ ወርቅ ሳይሆን ክህደት ነው፡፡
--------
የችግራችን መፍትሄው ሁሉም ሊገባው በሚችልበት፣ በሁለት ቃላት ማስቀመጥ ይቻላል፡፡ ይህን ያህል የዘር ጥላቻ ተካርሮ ወደ ግጭት ባላመራባት ኢትዮጵያ ቀርቶ፤ በዚያ በጥቂት ቀናት ውስጥ በዓለም ተወዳዳሪ ያልተገኘለት እልቂት በተፈጸመባት ሩዋንዳ እንኳን፤ ዛሬ በህዝቡ መሀከል እርቅ ወርዶ ሩዋንዳ በአፍሪቃ የሰላምና የእኩልነት ተምሳሌት ለመሆን ችላለች፡፡ ዛሬ ሩዋንዳ እንጂ እከሌ ሁቱ ነው እገሌ ቱትሲ ነው ማለት አጸያፊ ሆኗል፡፡ ስለዚህ፤ ምንም እንኳን መጪዎቹ ጊዜያት አስፈሪ ቢሆኑም ቅሉ፤ ብሄራዊ እርቅ በሚሉ ሁለት ቃላት፣ መፍትሄ ማስቀመጥ ይቻላል፡፡

የትግራይን መስቀል ስለመሸከም ….ከጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ

…ዕለቱ የሁለት ሺ ሶስት ዓመተ ምህረት የመስቀል በዓል የተከበረበት ማግስት፤ ሰሜናዊቷ የኤርትራ አዋሳኝ ወልቃይት ገና ከእንቅልፏ ሙሉ ለሙሉ ባለመንቃቷ፣ እስከ አፍንጫቸው የታጠቁ ጎፈሪያቸው የተንጨ(ባረረ ፋኖዎች በውስጧ ካሉ ተቋማት ወደ አንዱ እያመሩ ስለመሆኑ የጠረጠረች አትመስልም፤ ከኤርትራ የተነሱት ፋኖዎች መዳረሻ በወረዳዋ ታዋቂ የሆነው አወርቅ የመጀመሪያና ሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት በመሆኑ፤ ማንም ልብ ሳይላቸው ልክ እዚያው እንደደረሱ፣ ከፊሎቹ በሰለጠነ ወታደራዊ ስልት ትምህርት ቤቱን ከአጥር ውጪ በመክበብ ድንገተኛ ጥቃት የሚሰነዝር ኃይል ከመጣ ለመከላከል ሲያደፍጡ፤ የተቀሩት ደግሞ ወደ ውስጥ በመግባት በግቢው የሚገኙ መምህራን ሜዳው ላይ እንዲሰበሰቡ ቀጭን ትዕዛዝ አስተላለፉ፤ በጥቂት ደቂቃዎችም ውስጥ ሁሉም በተባለበት ቦታ ተሰበሰበ፤ እያንዳንዷን እንቅስቃሴ በዕቅዱ መሰረት መፈፀሙን በጥንቃቄ ሲከታተል የነበረው የቡድኑ መሪ በቅድሚያ ስለራሱና ጓደኞቹ ማንነት እና ስለወከሉት ድርጅት አጭር ማብራሪያ ከሰጠ በኋላ፣ የትግሉን ዓላማ በስፋት አብራርቶ አስረዳ፤ ሌሎች ጓዶቹም የፖለቲካ ፕሮግራማቸውን ዋና ዋና ርዕሶች የሚገልጹ በአማርኛና ትግርኛ ቋንቋ የተዘጋጁ በራሪ ወረቀቶችን የማደል ስራቸውን በማጠናቀቃቸው እንደአመጣጣቸው በሽምቅ ተዋጊ ስልት ከአካባቢው ተሰወሩ፡፡

ዜጎችን መታደግ የማይችሉ በአስቸኳይ ቆባቸውን አውልቀው ከተራው ሕዝብ የመቀላቀል ግዴታ አለባቸው። – Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ)

ቤተክርስቲያን እና መንግስት በኢትዮጵያ ውስጥ እጅና ጓንት ሆነው በኢትዮጵያውያን ላይ የማያባራ ጭቆና ማካሄድ ከጀመሩ ረዥም ዘመናት ተቆጥረዋል። ይብልጡኑ የመንግስቶች ጎህ ከቀደደ ጀምሮ በተለይ የተዋህዶ ሃይማኖት መሪዎች አስፈሪ እና አስደንጋጭ እንዲሁም አሳዛኝ ደግሞም አሳፋሪ ቃላቶችን በመጠቀም ስጋዊ እና ምድራዊ ስልጣኖችን ለገዢዎች ለማደላደል ይህ ነው የማይባል ግፍ በምእመናኖቻቸው እን በሌሎች አማኞች ላይ ፈጽመዋል አስፈጽመዋል፤ እየፈጸሙ ነው፤ እያስፈጸሙ ነው። ይህ የማይዋጥለት አሊያም የሚክድ ካለ እውነት የማይደላው ብቻ ነው።Co_existance
የኢትዮጵያ ጨቋኝ መንግስታት የሆኑ ከጥንት እስከ ዛሬ የተንሰራፉ በህዝብ ላይ የሚያደርጉት ጭቆና እና በደል ታሪክ የማይሽረው ጠባሳ በሰው ልጆች የትውልድ ሂደት ላይ መፍጠሩ እንደተጠበቀ ሆኖ የሃይማኖቶች ሚና ግን እጅግ በሚያሳዝን መልኩ ዜጎች በግፍ በጨቋኝ መንግስቶች ሲታረዱ በመባረክ የመንግስታቱን እድሜ አስረዝመዋል አሁንም እያስረዘሙ ነው።

Wednesday, June 11, 2014

በአገሩ ጉዳይ የሚያገባው ትውልድ ፍለጋ!! (zone9)

‹‹የአሁን እኛ?››

በሳምንቱ መጨረሻ ቀናት ምሽቶችን የሚያደምቁ የእንግሊዝ ፕሪሚየር ሊግ ጫወታዎን የሚታደሙ፣ ከዚያም አልፈው ጎራ ለይተው የሚሰዳደቡና የሚወቃቀሱ፣ የባሰ ዕለት ደግሞ በትልልቅ ጫወታዎች መልክ ጎራ ለይተው የሚቧቀሱ ወጣቶችን ማየት የከረመ አገራዊ ትዕይንት ሆኗል፡፡ ቅጥ ባጣ የፈረንጅ እግር ኳስ ፍቅር፣ ‹‹ከብርሃን ፍጥነት›› በላይ እየተስፋፉ ባሉ ‹‹የሱስ መሰረተ ልማቶች›› ውስጥ በመጥፋትና በቸልተኝነት የሚታማው ይህ ትውልድ ከላይ በተጠቀሱ ‹‹አደንዛዥ›› ጉዳዮች ተጠልፎ ካልወደቀም በጥልቅ ‹‹ራስን የማዳን›› ስሜት በመዋጥ አገሩን የረሳ፣ ፖለቲካ የማይገደው፣ ምርጫ የማያሳስበው ትውልድ ነው ተብሎ ይታማል፤ አለፍ ሲልም ደግሞ በተለይ ከቅርብ ጊዜ ወዲህ በስደት ወደተገኘው አገር ለመጓዝ ልቡ የቆመ፣ በአገሩ ተስፋ የቆረጠ፣ በየትኛውም አጋጣሚ አገር ጥሎ ለመሄድ ጓዙን ጠቅልሎ የተሰናዳ ወጣት እንዴት አገርን ይረከባል? ሊረከብስ ቢዘጋጅ ከማን እና እንዴት ይረከባል? ይህችን አገር ከእኛ የሚወስዳት ማነው የሚሉ ‹‹አባቶችም›› መኖር ሌላው ነባራዊ ሐቅ ነው፡፡ Zone 9 bloggers

የትግራይ ህዝብ የወያኔ ስርአት ተጠቃሚነው!

ከአንዷለም አስራት Andasr1983@gmail.com

ለዚህ ጽሁፍ መነሻ የሆነኝ በቅርቡ የማከብራቸውና የሶስት አፋኝ መንግስታትን ጭቆና ከህዝብ ጫንቃ ላይ ለማንሳት እየታገሉ ያሉት ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም እና የአረና ትግራይ አባል የሆነው አብርሃ ደስታ የትግራይ ህዝብ የወያኔ አገዛዝ ተጠቃሚ እንዳልሆነ ለማስረዳት የሞከሩት ስህተት መሆኑን ለመግለጽ ነው፡፡ The Tigray region of Ethiopia

የትግራይ ህዝብ በፖለቲካ፣ በኢኮኖሚ፣ በማህበራዊ አገልግሎት፣ በመሰረተ ልማትና በልማት ባለፉት 23 አመታት በአንጻራዊነት ከሌሎች ክልሎች በተሻለ ሁኔታ ተጠቃሚ እንደሆነ ለማስረዳት እሞክራለሁ። ይህን ስል የትግራይ ህዝብ አልፎለታል ፤ በልጽጓል፤ ከድህነት ወጥቷል እያልኩ ሳይሆን ህዋሃት በሚያደርገው በዘረኝነት ላይ የተመሰረተ አድልኦ ምክንያት ከሌሎች ክልሎች የተሻለ የስራ እድል ተፈጥሯል ፤ የተሻሉ የአገልግሎት ተቋማት አሉ፤ እንዲሁም ከፍ ያለ የገንዘብ ፍሰት አለ ይህም የሆነው የሌሎችን ክልሎች ጥቅም በሚጎዳ መልኩ ነው የሚለውን ለማስረዳት ነው። ከመጀመሪያው ማስረገጥ የምፈልገው ግን ለወያኔ ወንጀሎች የትግራይ ህዝብ ተጠያቂ ሊሆን አይችልም።

ሰማዕታትን እንዘክር፤ እራሳችንንም እንጠይቅ! (ግንቦት7)

ሰኔ 1997 በዘረኝነት፣ በአፍቅሮተ ንዋይና አፍቅሮተ ሥልጣን የተለከፉ የትግራይ ገዢ ጉጅሌ አባላት ጭካኔ በይፋ የታየበት ወቅት ነው። ለዓመታት በማስመሰያ ጭንብል ተሸፋፍኖ የቆየው የህወሓት እውነተኛ ባህርይ የዛሬ ዘጠኝ ዓመት በወርሃ ሰኔ አደባባይ ወጣ። በሀውዜን ላይ የደረሰውን የግፍ ጭፍጨፋ ሲያወግዝ የቆየው ቡድን ሌላ ሀውዜን አዲስ አበባ ከተማ ውስጥ ፈጠረ። ይኸኛው ሀውዜን ግን በአንድ ቦታ ተወስኖ የቀረ አልነበረም። ጭፍጨፋው በአዲስ አበባ ተጀምሮ ወደ አዳማ፣ ባህርዳር፣ ጎንደር፣ አዋሳ፣ ሃረር፣ ድሬዳዋ እና ሌሎች ከተሞችና ገጠሮች ተዛመተ። “አግዓዚ” የተሰኘው ገዳይ ሠራዊት በሰላማዊ እናቶችና አባቶች፤ ወጣቶችና ህፃናት ላይ ዘመተ። ደብተርና እርሳሶቻቸውን እንደያዙ ከትምህርት ቤት የሚመለሱ እምቦቃቅላ ህፃናትን ሳይቀር በጥይት ግንባርና ደረታቸውን እየመታ ጣለ።

“ነጻነትነታችን እንደ ዕርዳታ እህል ከምዕራባውያን የሚለገሰን አይደለም!”

ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ በኢትዮጵያ ለሚገኙ የፖለቲካ መሪዎች ያስተላለፈው ግልጽ መልዕክት

የተወደዳችሁ በኢትዮጵያ የምትገኙ የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎች፤
በቅድሚያ ለአዲሲቷ ኢትዮጵያ የጋራ ንቅናቄ (አኢጋን) የአክብሮት ሰላምታ በማቅረብ በትግሉ መስክ የምትከፍሉትን መስዋዕትነት የሚያደንቅ መሆኑን ይገልጻል፡፡ በተለይ በአሁኑ ጊዜ የፖለቲካ ምህዳሩ እጅግ ጠብቦ የለም የሚባልበት ደረጃ በደረሰበት ወቅት በምታገኙት ስንጥቅ ሁሉ እየተጠቀማችሁ ለህዝባችሁ የብርሃን ጭላንጭል ስለምትፈነጥቁ አኢጋን ሥራችሁን ያደንቃል፤ ያከብራል፡፡ እኛ በሥራችሁ ስኬት የምንመኘው ለቆማችሁለት የፖለቲካ ዓላማ ብቻ ሳይሆን ከህወሃት/ኢህአዴግ አገዛዝ ራሳቸውን ነጻ ለማውጣት አቅቷቸው መፈናፈኛ ላጡትም የመወሰን ኃይል እንደምትሰጧቸው በማመን ነው፡፡

ናይ ፌስቡክ ተፃረፍቲ (የፌስ ቡክ ላይ ተሳዳቢዎች)

በታደሰ ብሩ
መንደርደሪያ
ፌስ ቡክ ላይ ህወሓትን (ወያኔን) የሚተች ጽሁፍ ሲወጣ ስድቦችን “በብርሃን ፍጥነት” የሚያዥጎደጉዱ ሃያ ያህል ሠራተኞች ሬድዋን ሁሴን ቢሮ ውስጥ መኖራቸውን ሰምቼ ነበር። ይህ ራሱ እየደነቀኝ እያለ ሰሞኑን ሌሎች ዜናዎች ተከታትለው መጡ።Ethiopian's on facebook
በፌስ ቡክና መሰል ማኅበራዊ ሚዲያዎች ለሚቀርቡበት ትችቶች ፈጣን የስድብ ምላሽ የሚሰጡለት 235 “ባለሙያ ተሳዳቢዎችን” ኢህአዴግ አሠልጥኖ ማስመረቁ ከግንቦት 27 ቀን 2006 ዓም የኢሳት ዜና ሰማሁ። ዜናው እስከተጠናቀረበት ጊዜ ድረስ ኢሳት በነበረው መረጃ ሰልጣኞቹ 2, 350 የፊስ ቡክ፣ የቲውተር እና የብሎግ አካውንቶችን ከፍተዋል።
የኢሳት ዜና ከተሰማ ጥቂት ቀናት ቆይታ በኋላ ደግሞ 300 ብሎገሮች ለተመሳሳይ ተግባር በባህር ዳር ሠልጥነው የመመረቃቸውን ዜና ሴቭ አዲና የተባለው የፌስ ቡክ ባልደረባዬ አጋራን። እሱ ባለው መረጃ መሠረት ደግሞ ሠልጣኞች 3 000 የፌስ ቡክ አካውንቶች ከፍተዋል።

Saturday, June 7, 2014

የእናት ሀገር የድረሱልኝ ጥሪ ???…

ethio poor
(ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው)
ባለፈው ሰሞን ወያኔ ኢሕአዴግ ላለመው የጥፋት ተልእኮ ወሳኝ ክንውኑን መተግበሩ ይታወሳል፡፡ ወያኔ ለጥፋት ተልእኮው በእጅጉ የሚረዳውን ወሳኝ የጥፋት ሥራ የመሥራቱን ያህል ከእምነተ-አሥትዳደር (ፖለቲካ) ፓርቲዎች (ቡድኖች) አንሥቶ እስከ ሕዝባዊ ማኅበራት (Civic organizations) ድረስ ያሉ ሁሉ ልብ ሳይሉት ወይም በቅጡ ሳይረዱት ቀርተው ይሁን ምን አላውቅም ተገቢውን ትኩረት ሳይሰጡት ሲቀሩ ሳይ እጅግ ተገርሜያለሁ፡፡
ወያኔ በአሩሲ ሔጦሳና በሐረር ጨለንቆ ላይ ፋሽትት ጣሊያን ለሰበው የቅኝ ግዛት ይዞታ ዘለቄታ ሲል በነበረው ስልት (Strategy) ተአማኒነት እንዲኖረው በእውነተኛው ታሪካችን ላይ ሆን ብሎ በክፋት የፈጠረውን ፈጠራ በርዞ የሕዝባችንን አንድነት፣ ሰላም፣ ጥምረት፣ ወንድማማችነት (እኅትማማችነት)፣ መተማመን ለመፈረካከስና ለአገዛዙ ምቹ ሁኔታ ለመፍጠር ሲጠቀምበት የነበረውን ድርሰት ወያኔ ሐሰት እንደሆነ እያወቀ ነገር ግን ላለው ተመሳሳይ የጥፋት ዓላማ ከወደቀበት በማንሣት የፈጠራ ሠማዕታትን የሚዘክር የመታሰቢያ ሐውልት አስገንብቶ አስመርቋል፡፡

የኢትዮ-ኤርትራ የድንበር ጉዳይ ለምን አይቋጭም?

“የለዘብተኞችና የእስስት” ፖለቲካ ልዩነት እየፈጠረ ነው
መለስ በሁለቱ አገሮች ድንበር ላይ “የጅራፍ ድምጽ እንኳን አይሰማም” በማለት ሲመጻደቁበት የነበረው የኢትዮ-ኤርትራ ጦርነት በ”ወረራ” እና “ወረራን መቀልበስ” በሚል ድራማ ተጀምሮ ከተቋጨ አስራ አምስት ዓመት አልፎታል። ኢህአዴግና ሻዕቢያ ጉዳያቸውን በጠረጴዛ ዙሪያ ወይም በጡንቻ መቋጨት ያልቻሉበት ምክንያት ለብዙዎች እንቆቅልሽ ሆኖ እስካሁን አለ። ሁለቱም ወገኖች ድንበር ላይ ወታደር አፍስሰው መቀመጣቸውን አስመልከቶ “አውቀው ነው” ከሚለው ውሃ የማይቋጥርአስተያየት ጀምሮ በርካታ ጉዳዮች በገሃድና በሹክሹክታ ሲሰማ ቆይቷል።
የጎልጉል የዜና ምንጮች ሰሞኑን ከአዲስ አበባ የላኩት መረጃ ግን በይዘቱ የተለየ ነው። ይህንኑ አዲስ ጉዳይ የሚመለከታቸው ክፍሎች አስተያት እንዲሰጡበት ያደረግነው ሙከራ ባይሳካም ዜናው ለውይይት የሚጋብዝ በመሆኑ አትመነዋል።

ኢ- ፍትሃዊው እስሬ! እየፈሩ ጋዜጠኝነት የለም! (ጋዜጠኛ ኤልያስ ገብሩ ጎዳና )

(ሀሳብን በነጻነት የመግለጽ መብታችን ትልቅ አደጋ ላይ ነው)

አርብ ግንቦት 15 ቀን 2006 ዓ.ም ከወዳጄ ጋዜጠኛ ዳዊት ሠለሞን ጋር ቀጠሮ ነበረኝ፡፡ ረፋድ 5፡25 ሰዓት ላይ የሞባይል ስልኬ ጠራች፡፡ ከአምባሳደር ወደአራት ኪሎ በሚጓዝ ታክሲ ውስጥ ተሳፍሬ ነበር፡፡ የመስመር (የቢሮ) ስልክ መሆኑን አየሁትና “ሃሎ” አልኩኝ፡፡ ‹‹አቶ ኤልያስ፣ የዕንቁ መጽሔት ዋና አዘጋጅ?›› የሚል የሴት ድምጽ ተሰማኝ፡፡ ‹‹አዎን›› ስል መለስኩላት፡፡ ብዙ ጊዜ አንባቢዎች ስለሚደውሉ፣ ምን ዓይነት ግብረ-መልስ (feed back) ይኖራት ይሆን ነበር ሀሳቤ፡፡ ሳይሆን ቀረ፡፡ ‹‹የምደውለው ከፌዴራል ፖሊስ የወንጀል ምርመራ ነው፣ በአንድ ጉዳይ ላይ ስለምንፈልግዎት ቃልዎትን መጥተው እንዲሰጡን ነበር፡፡›› …‹‹እሺ፣ ሰኞ ጥዋት ልምጣ?›› በማለት ጠየኳት፡፡ ‹‹ቆይ አንዴ?›› ብላኝ ባልደረቦቿን ካነጋገረች በኋላ ‹‹ይቻላል›› አለችኝ፡፡ ቀጭን የጌታ ትዕዛዝ፡፡ ከዚህ የስልክ ጥሪ በኋላ የመጽሔቱ ማኔጂንግ ዳይሬክተር አቶ ፍቃዱ ማኅተመወርቅ (ፍቄ) ደውሎልኝ ስለጉዳዩ ሐሳብ ተለዋወጥን፡፡ ሰኞ በጥዋት ለመገናኘት ተቀጣጥረን ስልኩ ተዘጋ፡፡

የደህንነት ኃይሎች በጋዜጣ አዙዋሪዎች ላይ እርምጃ መወሰድ ጀመሩ

(ነገረ-ኢትዮጵያ፣ ሰበር ዜና) – በቅርቡ ገዥው ፓርቲ የግሉን ሚዲያ ለማፈን እንዲያስችል ጋዜጣ አዙዋሪዎችና አከፋፋዮችን በጥቃቅንና አነስተኛ ለማደራጀት የሚያስችል አሰራር እንደጀመረ ታውቋል፡፡ በዚህ አሰራር መሰረት ገዥው ፓርቲን የሚተቹ ጋዜጦችና መጽሄቶች ከገበያ በማስወጣት በቀጣዩ ምርጫ የሚደርስበትን ጫና ለመቀነስ እንደፈለገም ሲነገር ቆይቷል፡፡

Wednesday, June 4, 2014

ኪነ-ጥበብ አልባ ትግል (የቴዲ አፍሮ ጉዳይ)

አርአያ ጌታቸው
እስከማውቀው ድረስ ቦይኮት ኮካ ኮላ ተብሎ የተጀመረ ይፋዊ ዘመቻ የለም፡፡ ነገር ግን በርካቶች ገና ባልተጀመረ ዘመቻ ላይ ሆነው የወረደ፣ ተራ፣ የዘቀጠ… የሚሉ ቃላትን በመደርደር ለማጣጣል ሞክረዋል፡፡ ቴዲ አፍሮ ላይ ለደረሱበት የሞራል ኪሳራዎች እና ስም ማጥፋቶች ግን ምንም ለማለት አልደፈሩም፡፡ ዛሬ አርቲስት ሁሉ ለሆዱ ባደረበት ወቅት ሀሳቡን ያለምንም ፍርሀት በአደባባይ ጮሆ በመግለጽ ብቻውን በቆመ በዚህ ብላቴና ላይ እየደረሰ ያለውን በደል እና ግፍ ግን አንስቶ መወያያትን በማህበራዊ ድረ ገጽ ላይ ያለውን “የትግል እንቅስቃሴ” አቅጣጫ ያስቀይራል በሚል ለማጣጣል የሚደረግ ሙከራ መልካም አይመስለኝም፡፡

የሕዳሴ አብዮት! (ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ )

የዛሬይቱ ኢትዮጵያችን ‹‹አብዮታዊ ሁኔታ›› ላይ ለመድረሷ በብዙሃን ዜጐች ዕይታም ሆነ፤ ሂደቱን በተከታተሉ ዓለም አቀፍ ተቋማትና ምሁራን ምልከታ የማይታበል ሐቅ ሊሆን መቃረቡ በዚህ ተጠየቅ ለማነሳው አጀንዳ ገፊ-ምክንያት ነው፡፡ በአናቱም ባለፈው ሳምንት ‹‹የ‹ቀለም› አብዮት ናፍቆት›› በሚለው መጣጥፍ ላይ ለማሳያነት የጠቀስኳቸው ፖለቲካዊ፣ ማሕበራዊ እና ነገረ-ንዋያዊ ችግሮች ተደማምረው፣ ሀገሪቷን በርቀት እንደታዘብናት ሶቪየት ሕብረት፣ አሊያም በቅርበት እንዳስተዋልናት ሶማሊያ በመጪዎቹ ጥቂት ጊዜያት የመፈራረሷን አይቀሬነት ማስረገጣቸውን ልብ እንላለን፡፡ ከዚህ ክፉ የታሪክ ዕጣ ለመታደግም ከሁለት አስርታት በላይ ያስቆጠረውን ይሄን አሮጌ ሥርዓት መቀየር ብቻውን ዘላቂ መፍትሔ ሊያመጣ እንደማይችል ዛሬ ግልፅ እውነታ ሆኗል፤ ምክንያቱ ደግሞ ለዘመናት በገዥነት የተንሰራፋው የፖለቲካ ባሕልም አብሮ ካልታደሰ ነገሩ-ሁሉ ‹‹ታጥቦ ጭቃ…›› ከመሆን አለመዝለሉ ነው፡፡

Sunday, June 1, 2014

አገራዊ ስሜት ለምን ይጎድለናል?

በተክሉ አባተ
ከበርካታ ሳምንታት በፊት ከጓደኞቼ ጋር ኢትዮጵያ ስላለችበት ወቅታዊ ሁኔታ እየተወያየን ነበር:: ሁሉም ተሳታፊ የተስማማበት ጉዳይ ቢኖር ኢትዮጵያ ከምንም ጊዜ በላይ እጅግ ከባድ ማኅበራዊ ምጣኔ ሃብታዊና ፖለቲካዊ ቀውስ ውስጥ መግባቷን ነበር:: ለዚህም በግንባር ቀደምነት ተጠያቂው መንግስት እንደሆነ ቢሰመርበትም ህዝቡም ላለንበት ሁኔታ በማወቅም ሆነ ባለማወቅ ታላቅ አስተዋጽዖ እያደረገ እንደሚገኝ ተወስቷል::እንዲያውም ኢትዮጵያውያን ለአገርና ለለውጥ ያላቸው ስሜት እንደ በረዶ የቀዘቀዘ እንደሆነ ተነገረ:: ለዬት ያለና ታላቅ አገራዊና ወገናዊ ጉዳይ ሲነገር ህዝቡ ጸጥ ረጭ ብሎ ሰምቶ ሃሳቡን ሳይሰጥ ሹልክ እያለ እንደሚወጣ ሁሉም የታዘበውን እያነሳ ተናገረ:: ብዙዎች ለወገናቸው ጥልቅ ስሜት ስለሌላቸውና በተለያዩ ጉዳዮች ላይ በንቃት ስለማይሳተፉም መንግስት በጭቆናው እንዲቀጥል ሞራልና ጉልበት እየሰጡት እንደሆነም ተጨመረበት::