Sunday, March 20, 2016

"ኢህአዴግ ነው ቃሉን የሚያጥፍ። ኢህአዴግ ይመስል..." ይሄ ነበር የወሬው መነሻ....

"ኧረ፥ ምን ቃል ይበላል? ቃል አክባሪ ነው።" - ለማደናቆርና ለማናዘዝ።
ኢህአዲግማ ቃል አባይ ነው። ከተፈጠርኩኝ ቃሉን እንዲህ የሚበላ አንድ ሰውም አላየሁም።
ሌላ ሌላውን እንተወው... "20 ዓመት ተፈረደበት" ይባልና ሀብት ያለው በዛ ያለ ብር ሲሰጥ ይቀነስና ይፈታል። ብሩ ከተጠራቀመ 20 ቀንም አይፈጅም፤ ወንጀል ሰራ የተባለው ከቤተሰቡ ጋር ይቀላቀላል። ወንጀል ያልሰራው ምስኪን፣ ነካን ካሉ መቼም አይፈታም። ፃፉ ቢሉም ሲጽፉ ያስራሉ። ስብሰባ ጠርተው የጠሉትን እና ዐይን የጣሉበትን ከስብሰባ ይለቅማሉ።
በኃይለስላሴ ዘመን እንዲህ ያለ ቃል ማጠፍ የለም።
በመንግስቱም ቢሆን እንዲህ የለም። ሰዉ ቁርጡ ይነገረዋል፥ ከዚያ ሲወጣ ይቀጣል። ይሄኛው ግን ወሬው ሌላ፣ ስራው ሌላ።
በእርግጥ ውኃ ሳይሆን ቧንቧው በዝቷል በኢህአዴግ ጊዜ።

እነ ሌንጮ በጎቹን ለተኩላዎች አሳልፈው መስጠት የለባቸውም | ናኦሚን በጋሻው

naomibegachaw@gmail.com
በኦሮሞ ዴሞክራቲክ ግንባር፣ ኦዴግ ዉስጥ ያሉ አመራሮች በጣም የተከበሩ በሳል አመራሮች ናቸው። ለአመታት በትግሉ ዉስጥ ያለፉ፣ በርግጥም ለኦሮሞው ማህበረሰብ የሚበጀዉን እና የሚጠቅመዉን የተረዱ። በኦሮሞዉና በሌላው ማህበረሰብ መካከል አለመተማመን እና መጠራጠር እንዳለ ፣ ይሄንንም ለመግዛት እና ለመበዝበዝ እንዲያመቸው ሆን ብሎ ያደረገው ሕወሃት እንደሆነ በሚገባ የሚያውቁ። የኦሮሞው ማህበረሰብ ከሌላው ጋር ያለውን ግንኙነትና ትስስር አጠናክሮ ለሁሉም እኩል የሆነች ኢትዮጵያን ለመገንባት ይቻል ዘንድ ፍላጎት አላቸው። በፖለቲካ አመለካከታቸው ጥሩ መስመር ላይ ያሉ ነው የሚመስሉት።
ሆኖም እነ ኦቦ ሌንጮ ጽንፈኛ የሆኑትን እነ ጃዋር መሐመድና፣ ገረሱ ቱፋ ያሉ ወጣት አክራሪዎችን የፈሩ ይመስላል። እነ ጃዋር በሶሻል ሜዲያው እና በሚቆጣጠሩት የኦሮሞ ሜዲያ ኔትዎርክ ብዙ ስለሚጮኹ ብዙ እየተሰሙ የነኦቦ ሌንጮ ድምጽ እንዳይሰማ አድርገዉታል ። Outshine አድርገዋቸዋል።

‪#‎ሀበሻ_ማን_ነው‬

ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማርያም የኦሮሞን ህዝብ የነፃነት ትግል(The oromo movement as a Nomadic,Destructive, and Purposeless) በማለት በመጤነት ፥በዓላማቢስነት፥ በወራሪነት፥ በአውዳሚነት፥ በጎርፍነት ይመድቡና "አማሮች በጎጃምና በደንብያ ሁነው ትግሮችም በግምባራቸው ጠንክረው ባያግዱት እንደፈሳሽ ውኃ እስከ ምስር( ግብፅ) ይፈስባት ነበር።

በአቶ ሌንጮ ለታ ኢሳት ጋር የተደረጌ ቃለ ምልልስ ላይ…

ምን እንደሆነ ባላውቅም የዛን ትውልድ ታሪክ ለማውቅ በጣም እጓጓለው፡፡ከተፈጥሮአቸው ይሁን ይከተሉት ከነበር ህቡዕ የፖለቲካ አደራጃጀት በማላውቀው መልኩ ስበዙ ሚስጥረኞች ናቸው።
ለምሳሌ ሻብዕያና ወያኔ መንግስትም ሆነው ድብቅ ናቸው፡፡አንድ ጊዜ አቶ በረከት ስምኦን ይንን ድብቅነታቸውን ተናግሮ ነበር።በአንጻራዊነት ወያኔ ሳይሻል አይቀርም የኛ የፖለቲካ አምላክ እያጋጨ ይከፈሉና አንዱ አንዱን ስነካ በመሃል እኛ ወሬ እንቃረማልን።( የወያኔ ሁለት ቦታ መከፈል ልብ ይሏል 1993)።ሻብዕያ እስከ ዛሬ ለዜጎቹም ሆነ ለታሪክ የሚሆን የትግሉን ሚስጢር ያውጣ አይመስለኝም።
በደርግ በኩል ከሞላ ጎደል አያሌ መጻሃፍ ስለ ተጻፉ ችግር የለውም።በኢህአፓ በኩልም ብዙ ተብሏል።
ነገር ግን እንደ ዜጋም እንደ ተከታይ ትውልድም የአባቶቻችንን ታሪክ ማውቅ ነበረብን።እንዳውም ሞተው ከማለቃቸው በፊት ለታሪክ ሰነድ የሚሆን ዳጎስ ያለ መጽሃፍ ቢያሳትሙልን ሌላው ቢቀር "ነፍስ ይማር" እንላለን።

ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም በብሔራዊ መግባባት ላይ ከምሁራን ጋር ተወያዩ

  • ‹‹አገራዊ ታሪክንና የብሔረሰብ ታሪክን ለማጣጣም ችግር እየተፈጠረ ነው››
  • ‹‹ብሔርን ከብሔር ከማናቆር ያለፈ ፋይዳ የሌለው ሐውልት እስከመገንባት ተደርሷል››
  • ‹‹የተለየ ሐሳብ ያላቸው በፀረ ሽብር፣ በሙስናና በግብር አዋጆች ይጠለፋሉ›› በምሁራን የቀረቡ ጥያቄዎች
ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ደሳለኝ ከተለያዩ የአገሪቱ ከፍተኛ ትምህርትና የምርምር ተቋማት ከተወጣጡ ምሁራን ጋር፣ በብሔራዊ መግባባትና በበርካታ አገራዊ ፖለቲካዊ ጉዳዮች ላይ ውይይት አደረጉ፡፡
መንግሥት ‹‹የኢትዮጵያ ህዳሴ›› በሚል መሪ ቃል መላው የኢትዮጵያ ሕዝብን ማነቃነቅና ብሔራዊ መግባባት መፍጠር እንደሚፈልግ ማብራሪያ በመስጠት ማክሰኞ መጋቢት 6 ቀን 2008 ዓ.ም. ውይይቱን ጠቅላይ ሚኒስትር ኃይለ ማርያም ከፍተውታል፡፡ በዚህ የመግቢያ ንግግራቸው መንግሥት ኅብረተሰቡን ለማንቀሳቀስ ታላቁ የኢትዮጵያ ህዳሴ ግድብን፣ እንዲሁም ሌሎች ፕሮጀክቶችን አገራዊ መግባባት ለመፍጠር በሚያስችል አኳኋን ቀርፆ ተግባራዊ ለማድረግ እየጣረ ቢሆንም፣ ፖለቲከኛው ጥግ ጥጉን ይዞ ከመታኮስ ባለፈ የመቻቻልና የመወያያት ዴሞክራሲያዊ ባህልን ማዳበር እንዳቃተው ገልጸዋል፡፡

የእዉቅና መረጃ . .

የእዉቅና መረጃ . .
የብሐራዊ መረጃዉ ዳይሬክተር ጌታቸዉ አሰፋ በጥቂቱ...
ወያኔ ሀገራችንን እንደወረረ በመጀመሪያ የተቆጣጠረዉ ባዶ ስድስትን ነበር ባዶ ስድስት የእስር ቤት መገለጫ ሲሆን በእነርሱ አጠራር የኮድ ስም መሆኑ ነበር ወያኔያዊያን የማረሚያ ቤቶችን በቁጥጥራቸዉ ስር እንዳደረጉ ቀድሞ ሲያገለግሉ የነበሩት የማረሚያ ቤቶች አባላት በሙሉ በመሰወራቸዉ ምክንያት እስረኞችን በአግባቡ መያዝ ተሳናቸዉ። ስለዚህም የማረሚያ ቤቶች ሰራቶኞችን በአዋጅ መጥራቱ አስፈላጊ ሆኖ ተገኘ።
ሰራተኞቹ በአዋጅ ተጠርተዉ እንደመጡ የማረሚያ ቤቱን ሰነዶችና መረጃዎችን እንዲሁም በሰራተኖች ዙሪያ ላይ ግምገማ ለማካሄድ በማስፈለጉ ምክንያት ህወሃት አሉኝ ከሚላቸዉ ግለሰቦች መካከል ከማእከላዊ ወንጀል ምርመራ የምርመራ ቡድን ሐላፊ የሆነዉን በሻለቃነት ማእረግ የሚያገለግል ግለሰብ ወደ ማረሚያ ቤቶች ላከዉ! ሰዉየዉ በማረሚያ ቤቶች ዉስጥ ለአንድ ወራት ያህል ሰነዶች ሲያገላብጥ ቆይቶ አጠቃላይ አባላትን በመሰብሰብ ግምገማዉን ጀመረ።

ግልጽ ደብዳቤ ለጠ/ሚኒስትር ኃይለማርያም

ግልጽ ደብዳቤ ለጠ/ሚኒስትር ኃይለማርያም
Written by አስፋ ጫቦ
ግልጽ ደብዳቤ ለጠ/ሚኒስትር ኃይለማርያም
ይህን ደብዳቤ እንድጽፍልዎ ያስገደደኝ፣ ዛሬ አገራችን የገባችበት ማጥ ነዉ። ከፖለቲካነትን ይልቅ የ“ኧረ ምን ይሻላል! ኧረ ምን ይበጃል !” ደብዳቤ አድርገው ቢያዩልኝ ደስ ይለኛል። እንደ መፍትሔ አፈላላጊ የአገር ሽማግሌ ድምፅ ሆኖ እንዲታይልኝ/ቢታይልኝ እወዳለሁ። ነውም!! ”የጋራ ቤታችን” እንዲህ ማጥ ውስጥ ስትዘፈቅ የሚያይ አገር ወዳድ ሁሉ ድምጹን የመስማት ግዴታ ያለበት ወቅት ላይ ነን ብዬ አምናለሁ። ከፖለቲካ አመለካከት ልዩነት ይልቅ የአገራችን የኢትዮጵያ መሰንበት፤ ከዚያም “በነጻነትዋ ለዘላለም ትኑር!” ማለት ይቅደም እንደማለት ነው። በደርግ ቋንቋ “ኢትዮጵያ ትቅደም!” እንደማለት!
 

በኦሮሚያ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች

በኦሮሚያ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች የአጋዚ ጦር አባላት እየተገደሉ እየተገኙ እንደሚገኙ ከተለያዩ ሥፍራዎች ለዘ-ሐበሻ የሚደርሱ መረጃዎች አመለከቱ:: ታክስ ሰብሳቢዎችም እንዲሁ በኦሮሚያ ክልል የተለያዩ ቦታዎች ተዘዋውረው ግብር ለመሰብሰብ ሲሞክሩ በሚደርስባቸው ጥቃት የተነሳ ሥራ መስራት እንደተቸገሩም ለማወቅ ተቻለ:: የዘ-ሐበሻ የመረጃ ምንጮች እንዳመለከቱት በ አርሲ በባሌ በምስራቅ እና ም ዕራብ ሐረርጌ, በምስራቅ ሸዋ; በ ም ዕራብ ሸዋ የተለያዩ ቦታዎች በየቀኑ የአጋዚ ጦር አባላት ባልታወቁ ሰዎች እየተገደሉ በየጫካው ሥር እንደሚገኙ ታውቋል””

"ውሸት ሲደጋገም እውነት ይመስላል"አሉ

"ውሸት ሲደጋገም እውነት ይመስላል"አሉ አበው።በውሸት አለም ውስጥ እውነትንም በተደጋጋሚ ለማረጋገጥ መሞከር ለማያውቅ ትውልድ"ውሸት ይሆን?" የሚል ጥርጣሬ ሊያስነሳ ይችላል።ብዙ ልጆች "ወልቃይት አማራ ነው!"እያሉ ሲፅፉ አያለሁ።እኔ ደግሞ ይህን አባባል ለኦርቶዶክስ ተዋህዶ አማንያን"እየሱስ ጌታ ነው"የማለትን ያህል ዘግይቶ መመስከር ይመስለኛል።ለቀባሪ ማርዳት አይነት የተደጋገመ አባባል በሉት ከፈለጋችሁ።የወልቃይት ማንነት አያጠራጥርም እኮ።የማያውቅ አለ እንዴ?እኔ የምስማማው "የወልቃይቶች መብትና ነፃነት ይከበር!" በሚለው ነው።ለወልቃይት እኔም ያገባኛል ባይ ነኝ።

ነገሩ የሆነው በ1997 ምርጫ ወቅት ነው ።

ከአዲስ አበባና ከተለያየ አካባቢ በአጋዜ ጦር ያታፈሱ ሰላሳ ሁለት ወጣቶች አዲስ አበባ ፓሊስ ኮሚሽን ይታሰራሉ ወቅቱ የተረጋጋ ባለመሆኑ ወጣቶቹ ላይ የሚወሰደውን እርምጃ የሚያውቀው አንድ ሰው ብቻ ነው ። የሚጠበቀው የእሱ ትዕዛዝ ነው ከስር ያሉት የህዝብ ግብር ተሰብስቦ ደሞዝ የሚበሉ ፓሊስ ሜስጥረኞች የስርአቱ ዘብ ጠባቂዋች በወቅቱ የነበሩት ስምንት ነበሩ የእነዛ ሰላሳ ሁለት ሰዋች ነብስ በእነሱ እጅ ሆነ እነሱን የሚያዝ ያ አንድ ግለሰብ ይሰበስብና ይወገዱ የሚል ትዕዛዝ ያዛል ያን ትዕዛዝ ለመፈፀም ሲባል ከባድ መሳሪያ ይመጣል እነዛ ንፁሀንን በእነዛ ስምንት ሰዋች ፊርማ ተረሽነዋል ።

Sunday, January 31, 2016

ቋሚ ሲኖዶሱ ለብፁዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ ከፍተኛ ማስጠንቀቂያ መስጠቱ ተገለጸ፡፡

ቋሚ ሲኖዶሱ ፓትርያርኩን ያስጠነቀቀው፣ ባለፈው ሳምንት ረቡዕ፣ ሐምሌ ፪ ቀን ፳፻፮ ዓ.ም. ሳምንታዊ ስብሰባውን ባካሔደበት ወቅት ነው፡፡ የቤተ ክህነቱ የፋክትምንጮች እንደተናገሩት፣ የማስጠንቀቂያው መንሥኤ÷ አቡነ ማትያስ ምክራቸውን ለሥልጣነ ፕትርክናቸው አይመጥኑም ከተባሉ አማሳኝ ግለሰቦች እና የቤተ ክርስቲያኒቱን ተቋማዊ ክብርና ነፃነት በመጋፋት ከሚወቀሱ አፅራረ ሃይማኖት አካላት ጋራ በማድረግ የቅዱስ ሲኖዶሱን ውሳኔና ልዕልና የሚፃረር ተግባር በየጊዜው መፈጸማቸው የቅዱስ ሲኖዶሱን አባላት ክፉኛ በማሳሰቡ ነው፡፡

የህዝባችን እንባ ለማቆም ሁላችንም አምርረን እንታገል !

ኢትዮጵያ አገራችን ከፍተኛ የሆነ የህልውና ስጋት ተደቅኖባታል። ልጆቿ በያቅጣጫው ዋይታቸውን እያሰሙ ነው። የወያኔ የተበላሸ ስርዓት እና የስግብግብነት ተፈጥሮ ተደማምረው ህዝባችንን በቃላት ሊገለጽ በማይቻል ሰቆቃ ውስጥ ከተውታል። ህሊና ይዘው መፈጠራቸው ጥያቄ ውስጥ እስከሚገባ ድረስ፣ ቅልብ የወያኔ ገዳይ ወታደሮች በኦሮሞ እናቶችና ህጻናት ላይ የፈጸሙት ጭካኔ የተሞላበት እርምጃ በረጅሙ ታሪካችን ያላየነውና ያልሰማነው ነው። ባለፉት መንግስታት ለነጻነታቸው የጮሁ ወጣቶች በስርዓቱ የጸጥታ ሃይሎች መገደላቸው ታሪክ የመዘገበው ሃቅ ነው፣ ነገር ግን ህጻናትና ታዳጊዎች እጅግ ጭካኔ በተሞላበት ሁኔታ ግንባራቸውንና ደረታቸውን በጥይት እየተመቱ ሲወድቁ ስንመለከት ይህ በታሪካችን የመጀመሪያ ነው። አለም በፍጥነት እየተለወጠ ባለበት በዚህ ዘመን እንዲህ አይነት ጭካኔ የተሞላበት እርምጃ መወሰዱ ደግሞ የአገዛዙ ቁንጮዎችንና እነሱን ተከትለው ወደ ጥፋት አረንቋ የሚተሙትን ሁሉ ከሰው መፈጠራቸውን እንድንጠይቅ የሚያደርግ ነው። የኦሮሞ ህዝብ በአጋዚ ወታደሮችና በፌደራል ፖሊሶች በግፍ ለተነጠቀው ልጆቹ ድምጹን ከፍ አድርጎ አልቅሷል፤ ቁጭቱን በቻለው መንገድ ሁሉ ሊገልጸው ሞክሯል።

ሰበር መረጃ የአባይ ግድብ እና የቦንድ ገንዘብ ዘረፋ (ወያኔ)

February 6, 2014 8:15AM የአል ጀዚራ ባልደረባ የሆነዉ ሃሰን ሁሴን (Hassen Hussein) እንደዘገበዉ ጃንዋሪ 8 ላይ ግብጽ የአባይ ግድብ ግንባታ እንዲቋረት ጠይቃለች ይህዉም በሁለቱ ሐገራት መካከል ዉስጥ ለዉስጥ እየተካረረ የመጣ ዲፕሎማሲያዊ ጸብ ወደ ተለያየ አቅጣጫ እንደሚሄድ ሲነገር ቆይቶ ሰንብቶ ነበር። በ2017 ይጠናቀቃል የተባለዉ የአባይ ግድብ የተለያየ ችጎች ሲገጥሙት ቆይተዉ በስተመጨሻ የኢትዮጵያ ባለስልጣናት ከግብጽ ጋር ሚያደርጉት አለመግባባት ከተካረረ ግብጽ በኤርትራ የሚገኙ ተቃዋሚዎችን በማስታጠቅ ትጎዳናለች ወደሚል ስጋት ስለጣላቸዉ ብቻ የካዮዉን መንግስት (Cairo’s collaboration) ለድርድር በመጥራት እሹሩሩ ጀመረች በስተመጨረሻም ግድቡን ዉሃ ላለመሙላት በመስማማት አጭብጭባና ተጨብጭባ ወደ ወደምትዋሸዉ ህዝብ ተመለሰች።

በኑዌር እና አኝዋክ መካከል የተፈጠረው ግጭት ለግዜው ጋብ ቢል ከፍተኛ ውጥረት አለ ።

Menbere Kassaye's photo.Menbere Kassaye's photo.Menbere Kassaye's photo.
* ጤና ሳይንስ ኮሌጅ ም/ዲንና የክልሉ ምክትል ፕሬዝደንት ሹፌር መካከል በመኖርያ ቤት መሬት ጉዳይ በተፈጠረ የግል ፀብ ም/ዲኑ የአኝዋኩን ተወላጅ ሹፌር እጅ በጥይት መምታታቸውን አምነው ተናግረዋል ። ከዛ በኋላ ግጭቱ ከግለሰቦች ወደ ተማሪዎች የቡድን ፀብ ተጠናከረ ።
* በግጭቱ የተነሳ ቆስሎ የነበረ አንድ ወጣት በሆስፒታል ሲታከም ቆይቶ ህይወቱ በማለፉ የወጣቱ ወንድም ትምህርት ላይ ያሉ የአኝዋክ ተማሪዎች ላይ ቦንብ በመወርወር ብዙዎችን አቆሰለ ።

ከአፍሪካ ህብረት አጀንዳዎች ይልቅ የሙጋቤ መልእክት ትኩረት አግኝቷል

የአፍሪካ ህብረት የሊቀመንበርነት ጊዜያቸውን ያጠናቀቁት የዚምቧቡዌው ፕሬዘዳንት ሮበርት ሙጋቤ በ26ኛው የመሪዎች ስብሰባ ለተተኪያቸው ቦታቸውን ከመልቀቃቸው አስቀድሞ ህብረቱን በመወከል በተባበሩት መንግስታት፣በነጮችና በባራክ ኦባማ ላይ ጠንከር ያለ ወቀሳ ሰንዝረዋል፡፡
ሙጋቤ ንግግር ለማድረግ ወደ ተዘጋጀላቸው ቦታ ሲያመሩ ከአጋሮቻቸው ደመቅ ያለ አቀባበል ተደርጎላቸዋል፣ ፕሬዘዳንቱ በንግግራቸው ከተለመደው ከፋ ባለ መልኩ ምዕራባዊያንን፣ነጮችንና የአሜሪካውን ፕሬዘዳንት አብጠልጥለዋል፡፡
የተባበሩት መንግስታት ዋና ጸሐፊ ባንኪ ሙን የ91 ዓመቱ ሙጋቤን ንግግር እያደመጡ በተቀመጡበት ወንበር በጭንቀት ተውጠው ተስተውለዋል፣ ‹‹ሞተዋል አልያም በጠና ታመዋል›› የሚሉ ወሬዎች ሲነዙባቸው የሰነበቱት ሙጋቤ አፍሪካ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የጸጥታው ምክር ቤት ቋሚ ውክልና ካላገኘች ድርጅቱን ለቅቃ እንደምትወጣ ዝተዋል፡፡