Sunday, August 31, 2014

የኢትዮጵያውያን ስደተኞች መበራከት

አርያም ተክሌ
ነጋሽ መሀመድ
መንግሥት በአንዳንድ የግል ጋዜጦች ላይ ክስ ከመሠረተ እና ባለፈው ግንቦትም ዘጠኝ ጋዜጠኞች እና የድረ ገፅ አምደኞች ከታሰሩ ወዲህ ቁጥራቸው ትንሽ የማይባል ጋዜጠኞች ኢትዮጵያን ለቀው ወጥተዋል።

43f5db4e4
ባለፉት ጊዚያት ሀገር እየለቀቁ የወጡት ግን ጋዜጠኞች ብቻ አይደሉም፣ ብዙ ወጣቶችም በተለያዩ መንገዶች መሰደዳቸውን የመገናኛ ብዙኃን ዘገባዎች ያሳያሉ። ለጋዜጠኞች ደህንነት የሚሟገተው ድርጅት፣ የ«ሲ ፒ ጄይ» የምሥራቅ አፍሪቃ ተጠሪ ቶም ሮድስ፣ ኢትዮጵያውያን ሕይወታቸውን ለአደጋ እያጋለጡ የሚወጡበት ጉዳይ ከሰብዓዊ መብት ጋ የተያያዘ ነው ይላሉ።
ብዙ ወጣት ኢትዮጵያውያን በየመን ፣ በኬንያ እና ታንዛንያ፣ እንዲሁም በሱዳን እና በሊቢያ በኩል እያደረጉ አደገኛ በሆነ ጉዞ ወደ መካከለኛው ምሥራቅ፣ ደቡባዊ አፍሪቃ እና አውሮጳ ለመግባት ይሞክራሉ፣ በዚሁ ሙከራቸው ወቅት በየበረሃው እና በየጫካው ወድቀው የሚቀሩት እና ባህር የሚበላቸው ጥቂቶች እንዳልሆኑ እና የሕገ ወጥ ሰው አሸጋጋሪዎች ሰለባም እንደሚሆኑ በየጊዜው የዜና ምንጮች የሚያወጡዋቸው ዘገባዎች ያሳያሉ፣ ከጥቂት ጊዜ በፊት በዚምባብዌ በኩል አድርገው ደቡብ አፍሪቃ የገቡ 24 ኢትዮጵያውያን የመኖሪያ ፈቃድ ስላልነበራቸው በሀገሪቱ ፖሊስ መያዛቸው የሚታወስ ነው። ኢትዮጵያውያኑ ራሳቸውን ለዚህ ሁሉ መከራ የሚያጋልጡበት የተለያዩ ምክንያቶች መኖራቸውን ለጋዜጠኞች ደህንነት የሚሟገተው ድርጅት፣ «ሲ ፒ ጄይ» የምሥራቅ አፍሪቃ ተጠሪ ቶም ሮድስ ገልጸዋል።

እውነት አብርሃ ደስታ አሸባሪ ወይስ ህወሓት? ኢህአዴግ ነው ለሰላማዊ ትግል ፈሪ?

ክብሮም ብርሃነ (መቐለ)
Free Abreha Desta አብርሃ ደስታ ይፈታ
Free Abreha Desta አብርሃ ደስታ ይፈታ
ነሐሴ 1 ቀን 2006 ዓ.ም የአረና ትግራይ ፓርቲ ስራ አስፈፃሚና የመቀሌ ዩኒቨርስቲ የፖለቲካ ሳይንስ መምህር አብርሃ ደስታ በሽብር ተጠርጥሮ በተከሰሰበት ልክ በወሩ ፍ/ቤት እንደሚቀርብ በፌስ ቡክ አይቼ እኔም እንደ ዜጋና እንደ አድናቂው የሚቀርቡለትን የድራማ ክስ ለመስማት ጓጉቼ ፍ/ቤቱ ስደርስ እንደ እኔ አብርሃ ደስታን በአይናቸው ለማየትና የክሱን ድራማ ለማወቅ እንዲሁም ለቆራጡ ወጣት ፖለቲከኛ አብርሃ ደስታ የሞራል ድጋፍ ለመስጠት የተሰባሰቡ የተለያዩ የክልላዊና ሀገራዊ የፖለቲካ ፓርቲ መሪዎች፣ አባላት፣ ጋዜጠኞችና ብሎገሮች እንዲሁም የወጣቱ ፖለቲከኛ አድናቂዎች ሽማግሌዎችና ወጣቶች ተደማምረው ያልገመትኩት የሕዝብ ብዛት በቡድን በቡድን ሰብሰብ ብለው የአብርሃ ቆራጥነትና የሀገራችን የፖለቲካ ሁኔታ ሲወያዩ አገኘኋቸው፡፡
የክሱን ሁኔታ ለመመልከት የመጡ የፖለቲካ ፓርቲ አመራሮች

ኢትዮጵያና ኢትዮጵያውያንን/ብሔራቸውን ነጻ ለማውጣት በኤርትራ የሚንቀሳቀሱ የነጻ አውጪ ድርጅቶች ዝርዝር

1- የትግራይ ህዝብ ዲሞክራሲያዊ ንቅናቄ ( ደምሕት )
2 -የኦሮሞ ነጻ አውጪ ግንባር (ኦነግ – ዳውድ )
3- የኦሮሞ ነጻ አውጪ ግንባር (ኦነግ – ከማል )
4- የኦጋዴን ብሄራዊ ነጻ አውጪ ግንባር (ኦብነግ)
5- የግንቦት ሰባት ሕዝባዊ ሃይል
6- የኢትዮጵያ ሕዝባዊ አርበኞች ግንባር
7- የድቡብ የእኩልነት እን የፍትህ ግንባር
8- የጋንቤላ ነጻ አውጪ ግንባር

ጋዜጠኛ ብስራት ወ/ሚካኤል ተሰደደ

በጌታቸው ሺፈራው
ብስራት ወ/ሚካኤል
ብስራት ወ/ሚካኤል
በተለያዩ ጋዜጦች፣ መፅሔቶች የራሱ “አዲስሚዲያ” ብሎግን ጨምሮ በተለያዩ ድህረ-ገፆች አዘጋጅ እና ፀሐፊ ጋዜጠኛ ብስራት ወ/ሚካኤል መሰደዱ ታወቀ፡፡ ጋዜጠኛው ቀደም ሲል የፍኖተ-ነፃነት ጋዜጣ አዘጋጅ፣የኢቦኒ መፅሔት ዋና አዘጋጅ፣ በደቡብ አፍሪካ የሚገኘው ኢሳው መፅሔት ባልደረባና አምደኛ፤ በኢትዮ-ምህዳር ጋዜጣና በቅርቡ ወደህትመት የገባው ቀዳሚ ገፅ ጋዜጣ ላይም የተለያዩ የፖለቲካ፣ ሰብዓዊ መብት ጥሰትና ማኀበራዊ ጉዳዮች ላይ ትኩረት አድርጎ በራሱና በብዕር ስም እንደሚፅፍ ይወቃል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ የተመሰረተውና በመንግስት ከፍተኛ ቁጥጥርና ጫና ላይ የወደቀው የኢትዮጵያ ጋዜጠኞች መድረክ (ኢጋመ) መስራች አባል፤ በኋላም የማኀበሩ ትምህርትና ስልጠና ኃላፊ በመሆን እያገለገለ እንደነበር ይታወቃል፡፡ 

አቶ አባይ ፀሐዬ ቤተክርስቲያን የግል ፕሬሶች ላይ እየተከታተለች ክስ እንድታቀርብ መመሪያ መስጠታቸው ተጋለጠ

(ዘ-ሐበሻ) ከሁለት ወራት በፊት አቶ አባይ ጸሐዬ ለኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤ/ክ በፕሬሶች ላይ እየተከታተለች ክስ እንድታቀርብ መመሪያ ማስተላለፋቸውን የዘ-ሐበሻ የቤተ-ክህነት ምንጮች አጋለጡ። እንደምንጮቹ ገለጻ ቤተክርስቲያኗ ይህን መመሪያ ከተቀበለች በኋላ የተለያዩ ክሶችን በፕሬሶች ላይ አዘጋጅታ የነበረ ሲሆን ከነዚህም መካከል በሎሚ መጽሔት ላይ የታሰበው ክስ ጋዜጠኞቹ በመሰደዳቸው የተነሳ ክሱ ሊቀር ችሏል።
(ሎሚ መጽሔት ሊከሰስበት የነበረው ጽሑፍ ይህ ነበር)
(ሎሚ መጽሔት ሊከሰስበት የነበረው ጽሑፍ ይህ ነበር)

የቤተክህነት ምንጮቻችን ዜናውን ሲያደሱን “የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ በተክርስቲያን በሎሚ መጽሄት ላይ ልትመሰርት የነበረውን ክስ ሰረዛዋለች።” ካሉ በኋላ “ከትላንትና በስቲያ በንብረኡድ ኤሊያስ አብርሃ ለሕግ ክፍል በደረሰ የስልክ ትእዛዝ መሰረት የሎሚ መጽሄት ባልደረቦች ስለተሰደዱ እና ጹሁፉን ጻፈ የተባለው ግለሰብም የሚኖረው በአውሮፓ ሞናኮ መሆኑን የመንግስት አካላት ባደረስን መረጃ ክሱ ዝግጅቱ ቢጠናቀቅም እንዲሰረዝ በስልክ በንበሩድ ኤሊያስ ተነግሮናል።” ብለዋል። እነዚሁ ምንጮች እንዳሉት “ክሱ እንዲመሰረት የተፈለገው “ዜጎችን ያልታደጉ ቆባቸውን ያውልቁ ” በሚል ርእስ ስር የተጻፈው የሃይማኖት መሪዎችን መብት ይጋፋል እንዲሁም የእምነት ነጻነትን በማደፍረስ ሕዝቡ በሃይማኖት መሪዎች ላይ ታማኝነት እንዳይኖር ያደርጋል ..ወዘተ በሚሉ ተያያዥነት ካላቸው ጉዳዮች ጋር ሰበብ እና አቃቂር በመፍጠር መጽሄቱን እና ጸሃፊውን ለመክሰስ ታስቦ ለሕግ ክፍሉ ተጠንቶ ክሱ እንዲዘጋጅ ትእዛዝ ተላልፎልን የነበረ ቢሆንም ከመንግስት በተገኘ በሚል መረጃ መሰረት በንብረኡድ ኤሊያስ አብርሃ ተሰርዟል።” ብለዋል።

መንግስት ተብዬው ምን እየሰራ ነው?

እያለማ፣በህዳሴው ግድብ፣ በባቡር መንገድ ግንባታው በኢቲቪ በሚባለውም በማይባለውም ሀገር የመገንባት ስራ ተወጥሯል የምትሉኝ ካላችሁ እሱን ተዉት!! አይደለም፡፡ህውሃት ምሽግ እየቆፈረ፣ ቦምብ እየቀበረ ነው ያለው፡፡2007 ምርጫ እየደረሰ ነው፡፡በዚህ ምርጫ ኢህአዴግ/ህውሃት እሸነፋለሁ ብሎ ባይሰጋም፣እየተደገሰልኝ ነው ብሎ እያሰበው ባለው ነገር እረፍት የተሰማው አይመስለኝም፡፡በጣም ሰግቷል፡፡ሰማያዊ ፓርቲን አይደለም የሚሰጋው፣ አንድነትም አይደለም ፣ግንቦት ሰባትን የኤርትራ መንግስትንም አይደለም፣ህዝቡ ነው፡፡እነ ሰማያዊ እነ ግንቦት 7 እነ አንድነትና ሌሎችም ጉልበት የሚኖራቸው ህዝብ ካለ ብቻ ነው፡፡ይህ ህዝብ ምቹ ቀንና አጋጣሚ ካገኘ አንዴ ከተነሳ ወደነበረበት ለመመለስ እንደማይቻል ተርድቷል፡፡ ስለዚህ ለዚህ ህዝብ ምቹ ነገር አለመፍጠር አጋጣሚ አለመስጠት አማራጭ የሌለው የመከላከያ መሳሪያ አድርጎ ነው ያለው፡፡ከነዛ መሳሪያዎች ደግሞ በአሁኑ ወቅት በልማት ስም የሚደሰኮሩ ፕሮፖጋንዳዎች፤ህዝብን ከህዝብ የመለየት ስራዎች ፣ህውሃት እራሱን አስፈሪ እሱ ከሌለ ሀገሪቷ ወደሲኦልነት እንደምትለወጥ አድርጎ የማቅረብና የመሳሰሉት ነገሮች ተጠቃሾች ናቸው፡፡ከላይ ምሽግ እየቆፈረ ቦምብ እየቀበረ ነው ያልኩት ለዛ ነው፡፡እንዴት ብትሉኝ፡

የተሰደዱ ጋዜጠኞች ቁጥር አሻቅቧል

የተሰደዱ ጋዜጠኞች ቁጥር አሻቅቧል
ባለፉት አራት ወራት ብቻ 17 ጋዜጠኞች አገር ጥለው የተሰደዱ ሲሆን 12 ባለፉት ሳምንታት ውስጥ ከአገር መውጣታቸው ይታወቃል፡፡ ባለፈው ሳምንትም ውስጥም ተጨማሪ ሶስት ያህል ጋዜጠኞች አገር ጥለው ተሰደዋል፡፡ በመሆኑም አገር ጥለው የተሰደዱት ጋዜጠኞች ቁጥር 20 ደርሷል፡፡ በአሁኑ ወቅት ገዥው ፓርቲ ከሚወስደው አፈና፣ የማተሚያ ቤትና ሌሎችም ችግሮች ተዳምረው የስደተኛ ጋዜጠኞች ቁጥር ከዚህም እንደሚያሻቅብ ይጠበቃል፡፡ በቅርብ የተሰደዱት ጋዜጠኞች የደህንነት ሁኔታ አንጻር ስማቸውን መጥቀስ አልፈለኩም፡፡

Friday, August 29, 2014

The retarding role of foreign aid in Ethiopia By Aklog Birara (PhD)

ሰማያዊና ቴዲ አፍሮ የስልጠናው የልማታዊ ዲሞክራሲያዊ ስርአት ግንባታ ትግላችንንን ፈተናዎቹ አጀንዳ ሆነዋል።

ሰማያዊ ፓርቲ እና የቴዲአ ፍሮ ጥቁር ሰው አልበም በወያኔ ተብጠልጥለው ተወንጅለዋል።
Minilik Salsawi (ምንሊክ ሳልሳዊ) ነገረ ኢትዮጵያ / Negere Ethiopia Teddy Afro
‹‹ኢህአዴግ ራሱ በአኖሌ ስም እየነገደ ለእሱ የሚቀርቡት አካላት ከእነ ቴዲ አፍሮና ሰማያዊ ፓርቲ ጋር አላትሞ መውቀሱ የሚያስገርምና ውይይት ላይ ከፍተኛ ተቃውሞ ያስነሳ ነው›› የቴዎድሮስ ካሳሁን (ቴዲ አፍሮ) ጥቁር ሰው አልበም በስልጠና ሰነዱ ላይ ለአክራሪነት ምሳሌ ተደርጎ የቀረበ ሲሆን ተማሪዎችም ቴዲ አፍሮ ለአገር አንድነት የቆመ መሆኑን በመግለጽ መከራከራቸውን ገልጸውልናል፡፡

መኢአድ ሁሉን አቀፍ የሆነ የፖለቲካ ስርዓት እንዲሰፍን የማያቋርጥ ጥረት ያደርጋል፡፡

የኢትዮጵያ ሕዝብ ሆይ!
ወያኔ/ኢህአዴግ እየተገበረው ያለው ኢትዮጵያና ኢትዮጵያዊነን ማጥፋት ነው፡፡ 

ከዘመናት በፊት የሥልጣኔ ችቦ ከተቀጣጠለባቸው ጥቂት አገሮች መካከል አገራችን ኢትዮጵያ አንዷ ናት፡፡ በዚህ ረጅም የሥልጣኔና የታሪክ ዘመን ውስጥ የኢትዮጵያ ሕዝብ በተለያዩ መንገዶችና በማንኛውም ሁኔታ ነፃነቱን ለማስከበር ከውጭ ወራሪ ሐይሎች ጋር ሲታገል መኖሩ የዓለምን ቀልብ ከመሳቡ ባሻገር ለአፍሪካውያንና በዓለም ላይ ላሉ ጥቁር ሕዝቦች የነፃነት አርአያና ተምሳሌት በመሆን የጥቁርን ዘር ክንድ ብርታትና ፅኑነቱን አስመስክሯል፡፡ ይህ አስደናቂና ወደር የማይገኝለት ድል ዘወትር የሚከነክናቸው ባዕዳን የሀገር ውስጥ ባንዳዎች በማዘጋጀትና ግንባር ቀደም ተዋናይ በመሆን ብዙና ከባድ የችግር ቀንበር ሊጭኑብን ሲሞክሩ በዚህ ምክንያት ህዝባችን ዘርፈ ብዙ መሰዋዕትነትን እንዲከፍልም ሆኗል፡፡

Wednesday, August 27, 2014

ከጥቅሙ ጉዳቱ ይበልጣል

(ፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም)
better

ጉልበት አራዊት የሚተዳደሩበት ሕግ ነው፤ ሕገ አራዊት የሚባለው አራዊት የሚተዳደሩበት ጉልበት ነው፤ በአራዊት ዓለም ማናቸውም ነገር በጉልበት ያልቃል፤ በሰዎችም መሀከል ጉልበት አድራጊ-ፈጣሪ ሆኖ ጎልቶ ሲወጣ የአእምሮንና የኅሊናን መዳከም ወይም ጭራሹኑ አለመኖር ያመለክታል፤ ጉልበት አለን በማለት፣ ወይም ተመችቶናል በማለት፣ ወይም ጠያቂ የለብንም በማለት የማንኛውንም ሰው ሰብአዊ መብቱንና ሰብአዊ ክብሩን መግፈፍ ሦስት ነገሮችን ያመለክታል፤ አንደኛ ጉልበት እንጂ አእምሮና ኅሊና እንደሌለ፣ ሁለተኛ ጉልበት እንጂ ሕግ እንደማይከበር፣ ሦስተኛ በአንተ ላይ እንዲያደርጉብህ የማትፈልገውን አንተም በሰዎች ላይ አታድርግ የሚለውን ሕግ መጣስን ያሳያል፤ በመጨረሻም፣ ዘግይቶም ቢሆን በራስ ላይ ቅሌትን መጋበዝን ያስከትላል፤ የሌላውን ሰውነት ስናረክስ ሰውነትን በጠቅላላው ማርከሳችን ነው፤ ሰውነትን በጠቅላላው ስናረክስ ራሳችንን ከነጉልበታችን ማርከሳችን ነው፤ ራሳችንን፣ ሰውነታችንን ካረከስን በኋላ ዋጋ የለንም፤ ለራሳችን ዋጋ ከሌለን ለሌለች ሰዎችም ዋጋ አንሰጥም፤ ያኔ ክፉ በሽታ ይይዘናል፤ እግራችን ስር በወደቀ ሰው ስቃይ የምንደሰትና የምንስቅ፣ የምንፈነድቅ  እንሆናለን፤ ያን ጊዜ የለየለት በሽተኛ ሆነናል።

፸ ደረጃ

(በውቀቱ ስዩም)
70  dereja

ሣልሳዊ ቴዎድሮስ ወይም “ቴዲ አፍሮ” በሰባ ደረጃ የተባለ(ች) ነጠላ ዘፈን ለቆልናል፡፡
“በሰባ ደረጃ”ን እኔ ስሰማው እልም ያለ የፍቅር ዘፈን ነው፡፡ ፍቅርን ልዩ በሆነ ቦታና ልዩ በሆነ ሥፍራ የሚያሳይ ዘፈን፡፡ በአማርኛ ዘፈን ባህል ውስጥ ቦታን ማስጎብኘት የተለመደ ነው፡፡ “የሐረር ልጅ ነች ወጣቷ/ጀጎል ነው ቤቷ” አይነት ዘፈን ሞልቶናል፡፡ አብዛኛው ያገራችን ዘፋኝ፣ ያስጎብኝነት ሚናም ደርቦ ሲጫወት ኖሯል፡፡ በዚህ ምክንያት ተፈቃሪዋ ሴት ሁሌም ከታሪካዊ ቦታ አጠገብ ለመወለድ ትገደዳለች፡፡
ቴዲ በዚህ ዜማው ባልተሄደበት መንገድ ሄዷል፡፡ ሲጀምር፣ እዚህ ግባ የማይባል፣ ለዓይን የማይሞላ ቦታ መረጠ፡፡ ብዙ ጊዜ፣ ታሪካዊ ቦታ ሲባል አክሱም፣ ላሊበላ፣ ፋሲል፣ ሶፍኡመር፣ ጀጎል እንላለን፡፡ ካሜራው በኒህ ቅርሶች ላይ አፍጥጦ ኖሯል፡፡ ታሪክ አክሱም ላይ ጀምሮ ጀጎል ላይ የተጠናቀቀ ይመስል፡፡

የኢቲቪ “ያልተገሩ ብዕሮች” ዘጋቢ ፊልምና ያልተገራው አቀራረብ

d3

ከሁለት ሰአቱ የኢቲቪ ዜና አወጃ ተከትሎ የቀረበውን “ያልተገሩ ብዕሮች” ዶክመንተሪ በደረቁ ሌሊት ድጋሜ ስርጭቱ ተከታትየ ጨረስኩት … ላፍታ እንደተጠናቀቀ ዝም፣ ጭጭ አልኩና በሃሳቤ በህዝብ ገንዘብ ከፍተኛ ወጭ እየተደረገባቸው የሚሰራጩትን የመንግስት የህትመት ጽሁፍና የኤሌክትሮኒክስ መገናኛ ብዙሃንን አሰብኳቸው … በምናብ ብዙ ርቄ ሔጀ በዶለደመ፣ ባልተገራ እና በተባውና  በተገራው ብዕር ውስጥ ራሴን አትኩሮት ሰጥቸ የመገናኛ ብዙሃን ውጤቶች በሃሳብ ተመላለስኩባች! ሰፊ ሽፋን ያለውን ኢቲቪና ራዲዮኑን፣ በየቀኑ እየታተሙ የሚወጡትን እነ አዲስ ዘመንን ጋዜጣንና የመሳሰሉት እሰብኳቸው  … አስቤ አሰላስየ ወደ ደረስኩበት ድምዳሜ ከማቅናቴ በፊት ግን በ”ያልተገሩ ብዕሮች” ዘጋቢ ፊልም ዙሪያ የታዘብኩትን ቀዳሚ አድርጌ የተሰማኝን ላካፍልዎ ወድጃለሁ…

የወያኔ መንግስት በቅርቡ በፕሬሱ ላይ የከፈተው ዘመቻ ለስደት ከዳረጋቸው ጋዜጠኞች ጋር የተደረገ ቃለ ምልልስ

ከጥቅሙ ጉዳቱ ይበልጣል [ መስፍን ወልደ ማርያም]

የወያኔን ዕድሜ ለማሳጠር አብረን እንሰራለን- አርበኞች ግንባር፤ ግንቦት 7 ና የአማራ ዲሞክራሲያዊ ኃይሎች ንቅናቄ

የማለዳ ወግ … ይድረስ ለ”ጥቁር እንግዳዋ” ፈርጥ ተዋናኝ …ውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩን ብሶታችን ንገሪልን ! * ለባህሬኗ ወዳጀ ለአርቲስት እስከዳር ግርማይ

ብርቱ ወዳጀ እስከዳር Esky አንች የብርቱም ብርቱ ሰው መሆንሽን አውቃለሁ ። ከባህሬኑ የስደት ኑሮ ግብግብ ፣ ለወገን ድጋፍ ማድረግና ባህልን ከማስተዋወቅ አልፈሽ ተርፈሽ ” የጥቁር እንግዳን” ፊልም ለዛሬ ያበቃሽ ድንቅ እህታችን ነሽ ። ፊልሙን በቡድን ከማዘጋጀት እስከመተወን ባደረግሽው ድንቅ ጥረት በባህሬን ምድር የክብር ቀይ የክብር ምንጣፍ አስነጥፈሽ ስማችን በረከሰበት የአረብ ሃገር ፊልምሽን ስታስመርቂ የኮራሁት ኩራት ከውስጤ አይጠፋም ። ያንን ስሜት ሌላ ጊዜ አወራዋለሁ … ዛሬ ወደሳበኝ ግስጋሴሽ እና ልታደርሽልኝ ስለምፈልገው መልዕክት ጭብጥ ላምራ … !
ወዳጀ እስከዳር ግርማ ልጆችን ከማሳደግ የአረብ ሃገር ስደት ኑሮን ግብግብ ጋር ታግለሽ ዛሬ “ጥቁር እንግዳ ” የሚለው ከ25 ዓመት በኋላ ወላጆችዋን ፈልጋ ስለተመለሰችው ስለማደጎዋ ልጅ ምስኪኗን ሳራ ሆነሽ የተወንሸው አስተማሪ ፊልም በሃገር ቤት ፊልም መናኘት መታየት በመጀመሩ የተሰማኝን እርካታ ከፍ ያለ ነው።

ኢትዮጵያዊነት ማለት አንዱ ዓለም ተፈራ

“ ኢትዮጵያዊነት ማለት፤ ኢትዮጵያዊያንን መውደድ፣ ኢትዮጵያን ማፍቀር፤ የኢትዮጵያን መንግሥት በተገቢው መንገድ መደገፍና፤ ይህ መንግሥት የተሳሳተ መንገድ ሲይዝ መቃወም ማለት ነው። በሥልጣን ላይ ያለው ክፍል ፀረ-ኢትዮጵያዊያንና ፀረ-ኢትዮጵያ ሲሆን፤ ያንን ክፍል በማንኛውም መንገድ ማስወገድ፤ የያንዳንዱ ኢትዮጵያዊና የያንዳንዷ ኢትዮጵያዊት፤ ኢትዮጵያዊ ግዴታ ነው። ”
አብዛኛዎቻችን በየጊዜው የምናነሳው ጉዳይ፤ ሀገራችን ኢትዮጵያ ያለችበትን የፖለቲካ ሀቅና በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ እየደረሰ ያለውን በደል ነው። ኢትዮጵያዊ ነኝ ወይንም አይደለሁም የሚለውን ጥያቄ አይደለም። በየቦታው፣ በተገኘው አጋጣሚ፣ በየዕለቱ በሕዝቡ ላይ የሚደረገውን በደል እናውጠነጥናለን። ኢትዮጵያዊያን ናቸው ወይንም አይደሉም የሚለው ከጥያቄያችን መካከል አይደለም። መቼም አርባ ዓመት ሙሉ፤ በአረመኔው መንግሥቱ ኃይለማርያምና በወገንተኛው የትግሬዎች ነፃ አውጪ ግንባር መንግሥት፤ በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ የደረሰውን ግፍና በደል ገና ብዙ ፀሐፊዎች ብዙ ይውሉበታል፣ ሊቃውንት ይቀኙበታል፣ አንጎርጓሪዎች ይደረድሩበታል፣ ሰዓሊዎች ያቀልሙታል፣ ገጣሚዎች ይሰነኙበታል፣ መጽሐፎች ይደረሱበታል። ያ ግን፤ ከኛ ቀጥለው የሚመጡት ኢትዮጵያዊያን፤ ስለኛ ስለቀደምናቸው ኢትዮጵያዊያን ለማወቅ የሚያደርጉት ጥረት ውጤት ነው እንጂ፤ ኢትዮጵያዊ ስለመሆናችን ወይም ኢትዮጵያዊ ስላለመሆናችን አይደለም።

Sunday, August 24, 2014

አስራ አንድ ጋዜጠኞች ተሰደዱ

(ከላይ ከግራ ወደቀኝ) ቶማስ አያሌው፣ ዳንኤል ድርሻ እና ግዛው ታዬ፣ (ከታች) ሰናይ አባተ እና አስናቀ ልባዊ (Top, left to right) Thomas Ayalew, Daniel Dirsha and Gizawe Taye. (Bottom, left to right) Senay Abate and Asnake Lebawi
በአምስት ሣምንታዊ መጽሔቶችና አንድ ጋዜጣ ላይ የተመሰረተውን ክስ ተከትሎ አስራ አንድ ጋዜጠኞች ለስደት ተዳረጉ። አስራ አንዱ ጋዜጠኞች የተሰደዱት በፍትህ ሚኒስቴር ሐምሌ 28 ቀን 2006 ዓ.ም. “የዐመጸ ቅስቀሳና የሐሰት ወሬዎችን በመንዛት ሕገ-መንግሥታዊ ሥርዓቱን ለመናድ ጥረት አድርገዋል” በሚል በተመሰረተባቸው ክስ መሆኑን ለኢትዮጵያ ዛሬ ድረ ገጽ የደረሰን መረጃ ያስረዳል።
ፍትህ ሚኒስቴር ክስ የመሰረተባቸው ሎሚ፣ ዕንቁ፣ ፋክት፣ ጃኖ እና አዲስ ጉዳይ መጽሔቶች እና አፍሮ ታይምስ ጋዜጦች ሲሆኑ፤ ይህ ዜና እስከተጠናከረበት ጊዜ ድረስ አስራ አንድ ጋዜጦች ለስደት መዳረጋቸውን ለማረጋገጥ ችለናል።

በኢትዮጵያ ሕዝብ መራራ ትግል እብሪተኛው የወያኔ መንግስት መውደቁ አይቀርም!!

በኢትዮጵያ ሕዝብ መራራ ትግል እብሪተኛው የወያኔ መንግስት መውደቁ አይቀርም!!

በኢትዮጵያ ሕዝብ መራራ ትግል እብሪተኛው የወያኔ መንግስት መውደቁ አይቀርም!!

Gezahegn Abebe  (ገዛኸኝ አበበ) 
የኢህዲግ ወያኔ መንግስት   የስልጣን ወንበር በትሩን በሀይል ከተቆናጠጠበት ጊዜ ጀምሮ የኢትዮጵያ ሕዝብ የአኖኖር ሁኔታ ከእለት ወደ እለት እያሽቆለቆለ እና እየወረደ በመምጣቱ ከምቼውም ጊዜ በበለጠ በአሁኑ ወቅት ሕዝቡ ኑሮን መቋቋም በማይችልበት አደገኛ ሁኔታ ውስጥ እንደሚገኝ በኢትዮጵያ ውስጥ ያለውን የኑሮ ውድነት ተቋቁሞ መኖር ከባድ ፈተና እየሆነባቸው እንደሆነ የችግሩ ሰለባና ተጠቂ የሆኑት ሰዎች በየጊዜው ከሚያሰሙት ሮሮና ጩኸት መረዳት ይቻላል:: በአሁኑ ወቅት ጥቂትየስርአቱ  ደጋፊዎች እና የወያኔ ካድሬዎች ካልሆኑ በስተቀር የኑሮ ውድነቱን መቋቋም በማይችሉበት ደረጃ ላይ ደርሰዋል::

የተስፋኞች ትውልድ በተስፋ ቢስዋ ምድር

“የሶስተኛው አለም የለውጥ ሱናሜው ቀስቃሽ ወጣቱ ነው!” ሀ ሁ ... በል,
እኔም ኤ ቢ ሲ ... ልበል
ሳምሶን ሳህሌ
መንደርደሪያ፡
ይህ አጠር ያለች መጣጥፍ ፡ ቁም ነገር አዘል ስንቅ ባላሰብኩት ሰዓትና ግዜ ያጋጠመኝን የነገር ዱብ እዳ ለናንተ ላካፍላችሁ በማለት እነሆ እንደኔው እያዘናችሁ፤ እየተበሳጫችሁ፤ ውስጣችሁ እየተብሰለሰለ አንብቡት። ካልሆነም እየሳቃችሁ ፤
እየተገረማችሁ ማንበብ ይቻላል። ማልቀስ በጥብቅ የተከለከለ ነው።
የገጠመኝ ዱብ እዳ እዳለ ለእናንተ ለማካፈል ፈለኩ። በውስጡ ያነሳቸው ነጥቦች ለኔ እንደገባኝ ወጣቱን የሚያብጠለጥልሲሆን ፤ በወጣትኛው ቋንቋ ግን ሊዋጥላቸውና የማይቀበሉት ነጥቦች ተካተዋል። የእንግሊዘኛውን ውይይት ነጥብ በነጥብ ወደ አማርኛው እንዳለ ቀርቧል። በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ መልኩ ለቀረበው ጥሬ ነጥቦች ስሜት የሚነካ ቃላቶች/ መልክቶች ካሉ ይቅርታ እጠይቃለሁ። ዋናው ነገር አንባቢው በገባው መንገድ መተርጉም ይችላል ። መልካም ንባብ።
፩: አንደተለመደው ከምሳ በኋላ ከመሰሪያ ቤት ወጣ ብዬ ቡና ለመጠጣት ባካባቢው ወደ ሚገኝው ካፊ ገባሁ። ቡናዬን እየጠጣሁ የእለቱን ጋዜጣ አነባለሁ። ወቅቱ የአፍሪቃ fg የሕብረቱ ምስረታ በዓል የተዘከረበት ሳምንት ነበር።

ጠብ-መንጃ አናነሳም! (ተመስገን ደሳለኝ)

ብሶት የወለደው” ኢህአዴግ ከሁለት አስርታት በፊት በሰሜን ተራሮች ላይ ከኢትዮጵያ መንግስት ወታደሮች ጋር ያደረገውን የጎሬላ ውጊያ “አጃኢብ” በሚያሰኝ ቆራጥነት በድል መወጣቱ የማይታበል እውነትነው፤ ሥልጣን ከተቆናጠጠ በኋላም ለሚሰነዘርበት ማንኛውም አይነት የኃይል ጥቃት፣ ያውም ማቸነፍ አለማሸነፉን ሳያሰላ በፍጥነት ዘሎ ለመዘፈቅ ሲያንገራግር የተስተዋለበት ጊዜም አልነበረም፤ አሀዱ ብሎ የአመፅ ትግል ከጀመረበት ዕለት አንስቶ ላለፉት አርባ ዓመታት ከጀብሃ እስከ ኢህአፓ፤ ከኦነግ እስከ ኦብነግ፤ ከትህዴን እስከ አርበኞች ግንባር፤ ከሻዕቢያ እስከ አልሸባብ… በስም ተዘርዝረው ከማያልቁ ብረት-ነካሽ ድርጅቶች ጋር ወደ ፍልሚያ ለመግባት ከመወሰኑ በፊት ሰላማዊ መፍትሄዎችን ግራና ቀኝ የመፈተሽ ትዕግስትም ሆነ ልባዊ ፍላጎት እንዳልነበረው የራሱ የታሪክ ድርሳናት ሳይቀሩ በግላጭ ይናገራሉ፡፡

ጄ/ል ባጫ ደበሌና ተስፋዬ ገ/አብ[ከኢየሩሳሌም አርአያ]

(ከኢየሩሳሌም አርአያ)
ጄ/ል ባጫ ደበሌ በአሜሪካ ሜሪላንድ ግዛት በ350ሺህ ዶላር ቤት መግዛታቸው ታውቋል። የባጫ ባለቤትና አንድ ልጃቸው እንደሚኖሩበት ሲታወቅ ልጃቸው በተርም ከ20ሺህ ዶላር በላይ እየተከፈለለት እንደሚማር ማወቅ ተችሏል። በከፍተኛ ሙስና ውስጥ ከተዘፈቁ የመከላከያ ከፍተኛ የጦር አዛዦች አንዱ የሆኑት ባጫ ደበሌ በቦሌ ከለንደን ካፌ ፊት ለፊት ባለሁለት ፎቅ ዘመናዊ ቪላ ገንብተው እንደሚያከራዩ ይታወቃል። በኢትዮ- ኤርትራ ጦርነት ወቅት አሰብን ለመቆጣጠር ይገሰግስ የነበረውን የኢትዮጵያ ሰራዊት ከመለስ ዜናዊ በተላለፈ ትእዛዝ ግስጋሴው እንዲገታና ወታደራዊ እቅዱ እንዲኮላሽ ከፍተኛ ሚና የተጫወቱት ባጫ ደበሌ መሆናቸውን የቅርብ ምንጮች ያረጋግጣሉ።

የወያኔ መንግስት በቅርቡ በፕሬሱ ላይ የከፈተው ዘመቻ ለስደት ከዳረጋቸው ጋዜጠኞች ጋር የተደረገ ቃለ ምልልስ

ኢትዮጵያዊነት ማለትትትትት አንዱ ዓለም ተፈራ - የእስከመቼ

“ኢትዮጵያዊነት ማለት፤ ኢትዮጵያዊያንን መውደድ፣ ኢትዮጵያን ማፍቀር፤ የኢትዮጵያን መንግሥት በተገቢው መንገድ መደገፍና፤ ይህ መንግሥት የተሳሳተ መንገድ ሲይዝ መቃወም ማለት ነው። በሥልጣን ላይ ያለው ክፍል ፀረ-ኢትዮጵያዊያንና ፀረ-ኢትዮጵያ ሲሆን፤ ያንን ክፍል በማንኛውም መንገድ ማስወገድ፤ የያንዳንዱ ኢትዮጵያዊና የያንዳንዷ ኢትዮጵያዊት፤ ኢትዮጵያዊ ግዴታ ነው። ”
አብዛኛዎቻችን በየጊዜው የምናነሳው ጉዳይ፤ ሀገራችን ኢትዮጵያ ያለችበትን የፖለቲካ ሀቅና በኢትዮጵያ ሕዝብ ላይ እየደረሰ ያለውን በደል ነው። ኢትዮጵያዊ ነኝ ወይንም አይደለሁም የሚለውን ጥያቄ አይደለም። በየቦታው፣ በተገኘው አጋጣሚ፣ በየዕለቱ በሕዝቡ ላይ የሚደረገውን በደል እናውጠነጥናለን።

Friday, August 22, 2014

መለስን ቅበሩት!(ተመስገን ደሳለኝ)

ከኢትዮጵያ ሀገሬ የደቀቀ ኢኮኖሚ ላይ በማን አህሎኝነት ወጪ ተደርጎ፣ ቅጥ ባጣ መልኩ በመላ አገሪቱ እየተከበረ ስላለው የቀድሞ አምባገነን ጠ/ሚኒስትር ሁለተኛ ሙት ዓመት ዝክርም ሆነ ሰውየውን ዛሬም በአፀደ-ህይወት ያለ ለማስመሰል እየሞከሩ ላሉት ጓዶቹ አንዲት ምክር ብጤ ጣል ማድረጉ ተገቢ ነው ብዬ ስለማስብ በአዲስ መስመር እንዲህ እላለሁ፡-
አብዮታዊው ገዥ-ግንባር ግንቦት ሃያ፣ የህወሓት ምስረታ፣ የብአዴን አፈጣጠር፣ የኦህዴድና የደኢህዴን ውልደት፣ የብሔር ብሔረሰቦች በዓል፣ የባንዲራ ቀን፣ የመከላከያ ሳምንት፣ የፍትሕ ሳምንት፣ የሕዳሴ ግድብ መሰረት ድንጋይ የተጣለበት… ጅኒ-ቁልቋል እያለ ዓመቱን ሙሉ በማይጨበጥ ተራ ፕሮፓጋንዳ ማሰልቸትን መንግስታዊ ኃላፊነት አድርጎታል፡፡ ይህ እንግዲህ ለቁጥር የሚያታክቱ፣ በነጭ ውሸት የታጨቁ እና በአብዮታዊ ዲሞክራሲ ቅኝት የተንሸዋረሩ ‹ዶክመንተሪ ፊልሞቹ›ን ረስተንለት ነው፡፡

Tuesday, August 19, 2014

ያገር ፍቅር ልክፍት – በዶክተር ኃይሉ አርአያ


dr hailu areaya

ከእናቴ ማህፀን ነው ስፈጠር ከጥንቱ
ከህይወት መስመሩ ካገኘን ከእትብቱ ፡፡
ወይስ ከእናቴ ጡት ካይኖቿ እይታ
ከየት ነው ያገኘኝ ከቶ ከምን ቦታ
ያገር ፍቅር ልክፍት ያገር ፈቅርበሽታ፡፡
ከረገጥኩት መሬት በውስጥ እግሬ ገባ
ወይስ በጠዋት ፀሀይ ተወጋሁ ከጀርባ፡፡
ከበላሁት ቆሎ ጠረሾ አምባሻ
ከእንጀራ ከሽሮው ጥልቅ የእናት ጉርሻ፡፡

የወያኔው ኢንሳ በአዲስ መልክ የፌስቡክ ስም አጥፊ ፔጆችን/ገጾችን ሊያደራጅ ነው


  • 7
     
    Share
=================ነቢል አህመድ ዘገፈርሳ=====================
facebook
ወያኔ የኢትዮጵያን ሕዝብ አንድነት እና ነጻነት ለመሸራረፍ ብሎም ለመበታተን ከሚጠቀምባቸው ዘዴዎች አንዱ በማህበራዊ ድህረገጹ ያሰማራቸውን ከተቃዋሚ ሃይላት ጋር ተመሳስለው የተቃዋሚ የፖለቲካ ድርጅት መስለው የተቃዋሚ ሃይሎችን ሎግ በመጠቀም እንዲሁም ለሽፋንነት በየመሃሉ የተቃዋሚ ድርጅቶችን መግለጫ እንደወሽመጥ በማስገባት በማታለል እና በማጭበርበር ላይ ተመስርተው ሲሰሩ የነበሩ ስም አጥፊ ገጾችን/ ፔጆችን በአዲስ መልክ ለማደራጀት በዚህ ሳምንት እረፍት እንዲወስዱ ያደረጋቸው መሆኑ ታውቋል።

ስደተኛውና አምላኩ በምትኩ አዲሱ

ጋዜጠኛ ተስፋዬ ገብረአብ በ “የስደተኛው ማስታወሻ” [2006] መጽሐፉ ላይ “ፍቅር በለጠ” እና “ህሊና እንደ አምላክ” [ምዕራፍ 33፣34] በሚሉ ተያያዥ ርዕሶች ሥር ስለ ክርስትና ሃይማኖት ያለውን መረዳት አስፍሯል። ጴንጤዋን “ፍቅር በለጠ” ን እንደ መስተዋት ይዞልን የሃይማኖትን አስተምህሮዎች ሊያስረዳን ሞክሯል። በዚህ ሐተታዊ ግምገማ ሁለት አሳቦችን እናነሳለን፦ 1/ “ፍቅር በለጠ” እና የያዘችው ሃይማኖት ምን ይመስላሉ? 2/ ጋዜጠኛው/ደራሲው በእጁ የያዘው መስተዋት የራሱን ማንነት እንዴት ይገልጠዋል? በመጨረሻም፣ ስለ ደራሲውና ሥራዎቹ አጭር አሠሳ አድርገን እንደመድማለን።
ደራሲው በ1987 ዓ.ም. ወደ አሜሪካ ለጉዳይ በተጓዘበት ወቅት ውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የምትሰራ “አንዲት ሴት” ዲሲ አሜሪካ “ፍቅር በለጠ” ለተሰኘች ዘመዷ በእጁ ፖስታ እንደላከችና ሲደርስ ዘመድ የተባለችው “ለረጅም ጊዜ ያላያት” ጎረቤቱ ሆና እንዳገኛት የሚገልጽ ሐተታ ነው። ከዚያ በመነሳት ያደረገችለትን መስተንግዶና ጨዋታቸውን ያጋራናል።

“ያልተሄደበት መንገድ” – ሊነበብ የሚገባው ድንቅ መጽሐፍ! ነፃነት ዘለቀ

ይህን የአንዱአለም አራጌን በራሱ አገላለጽ ከጠባቧ የቃሊቲ እስር ቤት የተጻፈ ግሩም መጽሐፍ ሳነብ የተሰማኝን ስሜት ባጭሩ ለመግለጽ እንጂ ሥነ ጽሑፋዊ ደንብ የተከተለ ሂስ ወይም የመጽሐፍ ግምገማ ለመስጠት አለመነሳቴን መግለጽ እፈልጋለሁ – መሆኑን እንዴት ከረማችሁ?
ከሁሉ በፊት ግን ከሰሞነኛ ጉዳዮች መካከል ቂላቂሉ ወያኔ በአቶ አንዳርጋቸው ጽጌ ላይ የሠራውን አስቂኝ ድራማ ስመለከት እያዘንኩ የታዘብኩትን በዓለም ወደር የማይገኝለት ምርጥ የምርመራ ውጤት በሚመለከት ትንሽ ልበል፡፡
የኢትዮጵያን ቴሌቪዥን በውነቱ አልመለከትም፤ አለመመልከቴ ስህተት መሆኑ ቢገባኝም ጤንነቴን አጥብቄ ስለምፈልገው ይሁነኝ ብዬና ቁም ነገር አገኝበታለሁ ብዬ ኢቲቪን አላየውም – ብዙዎች እኔን መሰሎች ስላሉ “የዐዋጁን በጆሮ” እንዳትሉኝ እንጂ፡፡ የሆኖ ሆኖ በቀደምለታ ከሰዎች ጋር የሆነ ቦታ ቁጭ ብዬ ቁርስ ቢጤ ስንቀምስ በፖሊስ ፕሮግራም የተከታተልኩት በዓይነቱም ሆነ በይዘቱ ድንቅ የሆነ የወያኔ የወንጀል ምርመራ ቴክኒክና ውጤት ያጫረብኝን ልዩ ስሜት በዚህ አጋጣሚ ሳላነሳው መቅረት አልፈለግሁም፡፡ ከእውነት ሰው መሆኔን ጠላሁ፡፡

የኢትዮጵያችን ችግር ገዢዎች እና አደርባዮቻቸው የሚፈጥሩት የፖለቲካ ካንሰር ነው::…. .. እየተገፋን እስከመቼ?? ተነስ እንጂ ወገን !! -Minilik Salsawi (ምንሊክሳልሳዊ)

ሁኔታዎች ገዢው ፓርቲ ብቻ በሚፈልገው መንገድ የሚቀጥል ከሆነ ደጋግሜ ለመናገር የምንፈልገው ለሃገርም ለህዝብም ከባድ እና አደገና አደጋ እንዳለው ነው:: በፖለቲካ ታማኝነት ያልተማሩ እና ከካድሬ ትምህርት ቤት ተመርቀው የወጡ በፖለቲካ ጥላቻ የተሞሉ ሰዎች የአገርን አመራር እና የህዝብን አንድነት ሊጠብቁ ስለማይችሉ በሃገሪቱ የፖለቲካ መስክ ትልቅ በሽታ ሆነዋል::
በሃገሪቱ የተከሰተውን ደዌ ከማዳመጥ ይልቅ በሽሙጥ አንዱ አንዱን እየወገረው በመብረር ላይ እንገኛለን :; እርስ በእርስ ከመወጋገር ያድነን እንዳንል እየተወጋገርን ጸሎት ለቅጽበት ነው::ማን ከማን ይማር ሎሌ ከንጉሱ ሆኖብን ሆነና የራሳችንንም ሆነ የሃገራችንን ህመም ተጋግዘን እንዳናድን ራሳችን በሽታ ሆነናል::ምን እንደተባልን እንኳን ማዳመጥ አለመቻላችን አንዱ ደንቃራችን ሲሆን የምንናገረውንም ከማንነገርው መራርጠን መተንፈስ እስኪያቅተን ድረስ እያቃተትን በሽታችንን እያባስን ብዙሃዊ ተላላፊ ህመም አድርገነዋል ከዚህ ይሰውረን እንዳንል ራሳችን አሁንም ደንቃራ ሆነናል::