Wednesday, January 30, 2013

በቅ/ላሊበላ ገዳም በዓለም ቅርስነት የተመዘገቡ ቤቶች በቃጠሎ ወደሙ


  • ቤቶቹ ከቤተ መድኃኔዓለም እና ቤተ ዐማኑኤል አጠገብ የተሠሩ ነበሩ 
  • በልደት ክብረ በዓል የቱሪስቶች ቁጥር መቀነሱ ኅብረተሰቡን አስደንግጧል 
በቅዱስ ላሊበላ ደብረ ሮሃ ገዳም ከዐሥራ አንዱ ውቅር አብያተ መቅደስ ጋር በዩኔስኮ የዓለም ቅርስነት የተመዘገቡ አራት ጥንታውያን ቤቶች በእሳት ቃጠሎ መውደማቸው ተገለጸ፡፡ ባለፈው እሁድ ለሰኞ አጥቢያ መንሥኤው ባልታወቀ ምክንያት በተነሣው የእሳት ቃጠሎ የወደሙት አራት ቤቶች የሣር ክዳን ያላቸው ፎቅ ቤቶች ሲኾኑ፣ የላሊበላን ጥንታዊ የቤቶች አሠራር የሚያሳዩ በመኾናቸው እየተጠገኑ እንዲጠበቁ በዩኔስኮ የዓለም ቅርስነት የተመዘገቡ ነበሩ፡፡ በቃጠሎው የወደሙት ጥንታውያኑ ቤቶች፤ ከቤተ ክርስቲያኒቱ የአብነት ትምህርቶች መካከል በቅኔና ዜማ ትምህርት መስጫነት ሲያገለግሉ እንደቆዩ ተገልጧል፡፡ ገኛ ቦታቸውም ከዐሥራ አንዱ አብያተ መቅደስ መካከል በታላቁ ቤተ መድኃኔዓለም እና በቤተ ዐማኑኤል አጠገብ ከ20 - 30 ሜትር ርቀት ላይ መኾኑ፣ የገዳሙ አስተዳደር ጽ/ቤት ለቅርሶቹ ደኅንነት ትኩረት ሰጥቶ በቂ ጥበቃና ክብካቤ እንደማያደርግ በካህናቱ እና ምእመናኑ የሚነሡበትን ስጋቶችና ተቃውሞዎች ያጠናከረ ነው ተብሏል፡፡ ለአዲስ አድማስ አስተያየታቸውን የሰጡ የከተማው ነዋሪዎች እንደሚያስረዱት÷ የቃጠሎ አደጋው በደረሰበት ዕለት ሌሊት በሁለቱም አብያተ መቅደስ አካባቢ የገዳሙ ጥበቃ አባላት አልነበሩም፡፡

የኛ ራእይ ሁላችንም ያለ አድልኦ የምንኖርባትን አገር መገንባት ነው ። በሙት መንፈስ መመራት አይደለም !


የኢትዮጵያ ህዝብ ራእይ በአንባገነኖች እንደትንኝ እየተጨፈለቀ መኖር አይደልም። የኛ ራእይ ህወሃቶችን እየፈራንና እየተንቀተቀጥን፣ እየገደሉ፣ እየቆረጡ፣ እያሰቃዩ ኢትዮጵያን ምድራዊ ሲኦል ሲያደርጉ ተለጉመን መኖር አይደለም።

East Africa stagnates near bottom of the index, Ethiopia 137th


In Somalia (175th, -11) 18 journalists were killed, caught up in bomb attacks or the direct targets of murder, making 2012 the deadliest in history for the country’s media. The Horn of Africa state was the second most dangerous country in the world for those working in news and information, behind Syria. In Eritrea (in last place in the index for the sixth successive year), no journalists were killed but some were left to die, which amounts to the same thing. With at least 30 behind bars, it is Africa’s biggest prison for journalists. Of 11 incarcerated since 2001, seven have died as a result of prison conditions or have killed themselves. Since the independent media were abolished more than 10 years ago, there are no independent Eritrean news outlets, other than outside the country, and terror prevails.

Monday, January 28, 2013

የወያኔን ሰላዮችን ከውጭ አለም ማጽዳት።



ኢትዮጵያ የነጻነት ቀንዲል ነች፡እንደ ስበሃት ነጋ ላሉ ባንዳ ወያኔዎች ግን ጣሊያንን አሸንፈን ለመላው የጥቁር ህዝብ የነጻነት ጎህ ቀዳጅ መሆናችን ኩራት ሳይሆን እፍረት ስለሚመስላቸው አገሪቷ ከነሰንደቅ አላማዋ ጥፍታ ማየት የዘወትር ጥረታቸው ነው፡ ሌት ተቅን የሚተጉትም ለዚህ ስለሆነ የኢትዮጵያዊነት ሰሜት ያላቸውን ሁሉ ማሰር፤ መግደል፤ ማጥፋት ዋና ትግባራቸው ነው፡ ይህም ተግባራቸው ከበረሃ እስከ አዲስ አበባ ከዛም ጎረቢት አገሮች ድረስ ዘልቆ አሁን ደግሞ ወደ ምእራብ ሐገራትም መጣሁ እያለ ነው፡

የኦሮሞ ተወላጆች የፖለቲካ እስረኞች እንዲፈቱ ጠየቁ

ጥር ፳ (ሀያ) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
ኢሳት ዜና:-በኦሮሞ ጥናት ማኅበር፣ በዋሽንግተን ዲሲና አካባቢዋ የኦሮሞ ማኅበረሰብ ድርጅት፣ የኦሮሞ ወጣቶች ራስ አገዝ ማኅበር፣ የአፍሪካ ቀንድ የሰብዓዊ መብቶች ሊግና የኦሮሞ ድጋፍ ቡድን የተዘጋጀው ደማቅ የተቃውሞ ሰልፍ አቶ በቀለ ገርባ እና አቶ ኦልባና ሊሌሳን ጨምሮ ሌሎች የፖለቲካ እስረኞች እንዲፈቱ ጠይቀዋል።
የአሜሪካ ድምጽ እንደዘገበው ከአቶ በቀለ ገርባ እና ከአቶ ኦልባና ሌሊሣ በተጨማሪ በስም የተጠቀሱት ወልቤካ ለሚ፣ አደም ቡሣ፣ ሃዋ ዋቆ፣ ሞሐመድ መሉ፣ ደረጀ ከተማ፣ አዲሱ ምክሬ እና ገልገሎ ጉፋ በእሥር ላይ እንደሚገኙ የሠልፉ አስተባባሪዎች ተናግ

የዋልድባ መነኮሳትን ከፍተኛ ግፍና መከራ እየተፈጸመባቸው መሆኑን ገለጹ


የጸለምት ወረዳ ባለስልጣናት፣ በዋልድባ ያለዘር ልዩነት ለዘመናት የኖሩ መነኮሳትን ትግሬ ካልሆናችሁ በዚህ ገዳም ውስጥ መኖር አትችሉም በማለት ከፍተኛ ግፍና መከራ እየፈጸሙባቸው መሆኑን ዘጋቢያችን መነኮሳቱ የጻፉትን አቤቱታ ዋቢ በማድረግ በላከልን ዘጋባ ገለጸ።

እንደ ዘጋቢያችን ሪፖርት መነኮሳቱ ለክልሉ የወያኔ ባለስልጣናትና ለሰብዓዊ መብት ኮሚሽን በጻፉት አቤቱታ እንዳሉት ባለስልጣናቱ ግፍና በደል የሚፈጽሙባቸው በጣት የሚቆጠሩ የነሱን መነኮሳት፣የአካባቢውን ታጣቂዎችና ሚሊሺያዎች በመጠቀም ነው።

የፍርሃት እስረኛ መሆን የለብንም !!!


እንኳን ሰው ፈረስ እንኳን አልለጎምም ካለ ማንም እንደፈለገው አይጋልበውም። ሲያስፈራሩን ካልፈራናቸው፣ አትናገርሩ ሲሉ ከተናገርን፣ አትጻፉ ሲሉ ከጻፍን፣አትንቁ ሲሉ ከነቃን፣ ተከፋፈሉ ሲሉ ከአበርን፣ ፍሩን ሲሉ ከደፈርናቸው፣ ተንበርከኩ ሲሉ ከቆምን፣ አወድሱን ሲሉ ካወገዝናቸው...እንደ ጥንት አባቶቻችን እንቢ አሻፈረኝ ብለን በጋራ ከአመጽንባቸው እነርሱ ጥቂቶቹ አኛን ብዙሃኑን ፈጽሞ ሊረግጡን አይቻላቸውም። አንድ ህዝብ በጨቋኞች ጫማ ስር ወድቆ የሚረገጠው ጨቋኞቹ ስለበረቱ ሳይሆን የፍርሃት እስረኛ ከሆነ ብቻ ነው።

FBI aware of TPLF’s terrorist activities: Genocide Watch



By Abebe Gellaw
(ESAT News)–Genocide Watch, the Global coalition to end genocide and mass atrocities, says that the Federal Bureau of Investigation (FBI) is well aware of the fact that the Tigray People Liberation Front (TPLF) is a terrorist organization that the United States should label as such.
In an exclusive interview with ESAT, President of Genocide Watch, Prof. Gregory Stanton, said any specific threats from TPLF agents and operatives in the United States should be reported to the FBI right away.  “The FBI has got the TPLF already in its sights. It knows very well that the TPLF is a terrorist organization,” he said.
He also pointed out that the U.S. should declare the TPLF a terrorist organization and made clear that efforts would be exerted to bring that to the attention of the concerned authorities. TPLF is already registered in the Global Terrorism Database (GTD), kept by the National Consortium for the Study of Terrorism and Responses to Terrorism, a center of the U.S. Department of Homeland Security.

Sunday, January 27, 2013

ሰራዊታችን ተከታታይ ወታደራዊ ጥቃት ፈጸመ፡ ብዛት ያላቸው ሴት ታጋዮችም ግንባሩን ተቀላቀሉ!



የኢትዮጵያ ሕዝብ አርበኞች ግንባር ነበልባል ጦር ጥር 17-2005 ዓ.ም በወልቃይት ጎብለል በተሰኘ የወያኔው መከላከያ ካምፕ ላይ በወሰደው ድንገተኛ ማጥቃት በካምፑ የሚገኙ የመከላከያ አባላትን ደምስሷል። በውጤቱም 25 ሙት 36 ቁስለኛ እንዲሁም  20 ክላሽንኮፍ ጠብመንጃ ፣ 4 የእጅ ቦንብና 1 ስናይፕር ጠብመንጃ ከነ ሙሉ ትጥቁ በመማረክ በማግስቱ ማለትም በትናንተናው እለት በቀጠለው የነበልባል ሰራዊት ወታደራዊ ጥቃት በወልቃይት ጠበቆ በተባለ ቦታ 24 የአገዛዙ ታጣቂዎች ሙትና 29 ቁስለኛ ሆኗል። በድምሩ በሁለት ቀናት ውጊያ በጠቅላላው 49 ሙት 65 ቁስለኛ ሲሆን፦ የአምባገነኑ አገዛዝ ሰራዊት የአርበኛውን ጡጫ መቋቋም ተስኖት እግሬ አውጭኝ ብሎ ከመፈርጠጡም ባሻገር የውጊያ ሞራሉ ክፉኛ በመዳከሙ ምክንያት በአድጎሹ ፣ አደባይ፣ሁመራና እድሪስ አካባቢ የሚገኙ የጦር አመራሮች በመሰባሰብ የመልሶ መቋቋም እንቅስቃሴ ላይ እንደተወጠሩ ታውቋል።

ከአሜሪካ የህወሓት ሰላዮች ዛቻ



(ከኢየሩሳሌም አርአያ)
አሜሪካ የመሸጉ የሕወሐት ሰላዮች ዛቻና ማስፈራሪያ መሰንዘር ጀምረዋል። አልፈው ተርፈው «ክስ» እንመሰርታለን ብለዋል። ለማስፈራሪያቸው የሚበረግግ ባይኖርም - ነገር ግን ነፃነት ባለበት አሜሪካ ያሉ የፍትህ አካላት በብርሃነ፣ ስብሃት፣ በረከት፣ አዜብ አሊያም ሽመልስ….የሚሽከረከሩ መስሎዋቸው ያለሃፍረት አንደበታቸውን ሞልተው ሲደነፉና ለማሸማቀቅ ሲሞክሩ መታየታቸው …ምን ያክል የሞራል ድቀት እንደተጠናወታቸው ያሳያል። ባለፉት ወራት ከተሰነዘሩ ተራ ስድቦችና ዛቻዎች የትላንቱ ለየት የሚያደርገው ነጥብ ስላለ ነው፥ ይህችን መልክት ለመፃፍ የተገደድኩት። እነዚህ ሰዎች አሜሪካ ዋሽንግተን ዲሲ የመሸጉ የሕወሐት ሰላዮች እንደሆኑ ላሰምርበት እወዳለሁ። ከጀርባቸው ብርሃነ እንዳለ በግልፅ በአንደበታቸው አረጋግጠውልኛል። ዋናው አላማቸው ደግሞ « ሳንጋለጥ..ቀድመን እናሸማቅ፤..» ከሚል ከንቱ አስተሳሰባቸው የመነጨ ነው።

የፈራ ይመለስ ! የሃይማኖት መብቶች እንዲከበሩ ለሁሉም መብቶች የመታገያ ግዜው አሁን ነው!

ፍትህ፣ ነጻነት፣ እኩልነትና አንድነት የብዙ ሃይማኖቶች መሰረታዊ መርህ እሴቶች ናቸው። እነዚህ ቲውፊቶች ለአለፉት 21 አመታት በዘረኛው ወያኔ እየተሸረሸሩና እየመነመኑ ዛሬ ከእነ አካቴው በሀገራችን ኢትዮጵያ ስለመሰረታዊ የሰው ልጆች መብት ነጻነት እንዳይወራ፤ ወያኔ የጥይት አፈ ሙዞች በእያንዳንዱ የህዝብ አገልግሎት ተቋማት ላይ በመደቀን የአምልኮ ቦታዎችን ሳይቀር በመዳፈር ህዝበ ምእመናኑ የእኔ የራሴ የሚለው የአምልኮት ቦታ እና ህግ እንዲያጣና እንዳይኖረው እያደረገ ነው። 

በሀገራችን ኢትዮጵያ ከቀን ወደቀን እየተባባሰ የመጣው የእምነት ነጻነት እጦት ሁላችንንም ሊያሳስበን እና ሊያስተሳስረን የሚገባበት ጊዜ ላይ ደርሰናል። በተለይም በታሪካችን፡ የኢትዮጵያ ህዝብ በእምነት፣ በዘር፣ በፖለቲካ እስከ ቅርብ ጊዚያት ድረስ ሳይለያይ ተከባብሮና ተሳስቦ የሚኖር ህዝብ እንደሆነ የማይካድ ሃቅ ነው።

Saturday, January 26, 2013

ጉድ ነው ጠ/ሚኒስትሩ “ነፃ አገር ነው” ብለዋል - ማተሚያ ቤቶች እንዳትፈሩ!

በስልክ “ጋዜጣ አታትሙ” ብሎ ማዘዝ ቀረ! (የዲሞክራሲ አገር ነዋ)
ሰሞኑን ቴሌቪዥን ተመልክታችኋል ብዬ እገምታለሁ (ፓርላማ በኢቴቪ ማለቴ እኮ ነው!) አንዳንድ ወገኖች ምን እንደሚሉ ታውቃላችሁ? “ፓርላማም ኢቴቪም አያዝናኑም!” በእርግጥ ኢቴቪ አያዝናናም በሚለው እኔም እስማማለሁ (እንኳን እኔ ኢቴቪም ይስማማል!) እኔን ያልገባኝ ምን መሰላችሁ? ፓርላማው አያዝናናም የተባለው ጉዳይ ነው፡፡ እንዴ --- የት አገር ነው ፓርላማ የሚያዝናናው? የየትም አገር ፓርላማ እኮ (ሲንጋፖርና ታይዋንን ጨምሮ) ትላልቅ የአገር ጉዳዮች የሚታሹበትና የሚፈተጉበት እንዲሁም ህግ የሚወጣበት እንጂ ሰርከስ የሚቀርብበት የመዝናኛ ፕሮግራም አይደለም፡፡
በነገራችሁ ላይ በፓርላማ ብቸኛው የተቃዋሚ ፓርቲ ተወካይ የተከበሩ አቶ ግርማ ሰይፉ፤ በክላስተር ስለተሾሙት ባለስልጣናት ጉዳይ ላነሱት ጥያቄ ጠ/ሚኒስትር ኃይማርያም ሲመልሱ፣ ክላስተር በእኛ አገር የተጀመረ ሳይሆን በሲንጋፖርና በታይዋንም እየተሰራበት እንደሆነ አስረድተዋል (እንደ ፀረ ሽብርተኝነት ህጉ ቃል በቃል የተቀዳ ነው ባይሉም!)
ፓርላማው የመዝናኛ ፕሮግራም አይደለም ብንልም ትንሽ ዘና የሚያደርግ ነገር ቢታከልበት ግን ብዙ ተከታታይ ያገኛልና ቢታሰብበት አይከፋም፡፡ እኔ የምለው ግን--- አንዳንዴ እንኳን ምናለ ኢቴቪ ሳቅ በኢፌክት ቢጨምርበት! የፓርላማ ፕሮግራም ላይ እንጂ ዜና ላይ አልወጣኝም (ካልሆነ እኮ ከሰራዊት ፍቅሬ ቶክ ሾው ተመክሮ መውሰድም ይቻላል) አያችሁ-- ፖለቲካ “የቻይና ቋንቋ” የሚሆንባቸው አንዳንድ ወገኖች ስላሉ የሚያስቅ ነገር ቢኖር በእሱ እያዋዙ ይውጡታል - ፖለቲካውን! እንደውም ትዝ ይላችሁ እንደሆነ --- ከአንድ ከሁለት ዓመት በፊት ፓርላማ ውስጥ አዝማሪና ገጣሚዎች እየገቡ በየመሃሉ ያዝናኑ የሚል ሀሳብ ሰንዝሬ ነበር (እንደመድረክ ፓርቲ የሰማኝ የለም እንጂ) አሁንም ግን አልረፈደም፡፡ እንደውም ያ ሃሳቤ በትክክል መተግበር ያለበት አሁን ይመስለኛል። እንዴ --- ፓርላማ ውስጥ እንኳን ሳቅ ደረቅ ፈገግታ እንኳ ጠፋ እኮ! እኔ የምለው--- የኢህአዴግ የምክር ቤት አባላት ለጠ/ሚኒስትሩ የሚያቀርቡትን ጥያቄዎች ፓርቲው አዘጋጅቶ ነው አይደል የሚያከፋፍላቸው? (ከተሳሳትኩ እታረማለሁ!) እናላችሁ --ለምንድነው የጥያቄው ወረቀት አንዳንድ ቦታ ላይ (ሳቅ) የሚል በቅንፍ የማይፃፍበት? አንዳንዴ በትእዛዝም ቢሆን እንዲስቁ ብዬ እኮ ነው! (ሳቅ ሲጠፋስ?)

ለካንስ ሁሉ ነገር ጨለማ አይደለም?!

ጭዋታው ከመካሄዱ አንድ ቀን ቀደም ብየ ይህን ፅፌ ነበር። "ይህ ሰውየ ምናለ ቢለቀን ሞቶም ይህ የአጋንንት መንፈሱ አለቀቀም። ይህ መንፈስ ደቡብ አፍሪካ ድረስ ሄዶ የኔ ምስል ያለበትን ቲሸርት ካላደረጋችሁ እያለ በተጫዋቾች መሀል የስነልቦና ጫና እየፈጠረ ነው። አብዛኛዎቹ እንቢታን ሲመርጡ ጥቂቶች ግን በውስጥ ደርበን እንለብሳለን ጎል ሲገባም በአደባባይ ይህን ሙት ሰውየ እናሳያለን እያሉ ተጫዋቾቹን እየከፋፈሉ ነው። በደቡብ አፍሪካ የምትገኙ ኢትዮጵያኖች እንዳታሳፍሩን። ይህን መንፈስ ወደ ኢትዮጵያ እንዳይመለስ አድርራችሁ እዛው ውቅያኖስ ውስጥ ጨምሩት። ድል ለብሄራዊ ቡድናችን።" እንዳልኩትም ይህ አጋንንት መንፈስ ሳውዝ አፍሪካ ድረስ ተካትሎ ሄዶ ተጫዋቾቻችን ድንብርብራቸውን አወጣው። የዝህ ሰውየ መንፈስ እስካለ ድረስ ኢትዮጵያ ሰላም አታገኝም።

Wednesday, January 23, 2013

አቤት! አቤት! አቤት!. . . በደል አዳምጡ፤ መፍትሄ ስጡ


በአንድ ወቅት ዜና ላይ “ኢትዮጵያዊነት መብትና ክብር ነው” ማለትን ሰምቼ ነበር በእኔ ትርጉም የዚህ ዓረፍተ ነገር ትክክለኛ ተጠቃሚዎች ያላቸው ሀብታሞች፣ የፖለቲካ ባለወንበሮች፣ ሕገወጥ ደላሎችና ከራይ ሰብሳቢ ተብለው የተፈረጁ ግለሰቦች ናቸው ብል የተሳሳትኩ አይመስለኝም፣ ከደረሰብኝና እየደረሰብኝ ካለው ተከራይቶ የመኖር መብት ጥሰትና በደል አኳያ” አለን ትዕግስቱ ብለን የሰየምነው የመረጃ ምንጫችን።
እንደ ትዕግስቱ የበደሉ መነሻ ደግሞ ገዥ ፖለቲከኞቻችን ራስን ብቻ ማዳመጥ እንጂ ሌላውን አለማዳመጥ፣ ሕገ ወጥ ድርጊትን ከጅምሩ ባለመቅጨት ሥር እስኪሰድ በቸልተኝነት ወይም የግለሰብ ጉዳይ ነው ብለው ዝም ብለው መመልከት ያዳበረው ችግር ነው። የግለሰብ ችግር ወደማህበራዊ ችግር ይህም ወደፖለቲካዊ ችግር እንደሚሸጋገር ግንዛቤ አላገኘም። አንዳንዴ ደግሞ አንዳንድ ባለሥልጣኖቻቸው ከደላሎች ሕገ ወጥ ድርጊት ተጠቃሚዎች ናቸው ወይስ እነሱና በቤት ኪራይ ሰብሳቢነት ታሳታፊዎች ናቸው የሚል ጥርጣሬም እንዳለው ነግሮናል። 

Monday, January 21, 2013

ፍረደም ሐውስ የ 2013 ኢትዮጵያ ነጻነት የሌለባት ናት አለ


ጥር ፲፩ (አስራ አንድ) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
በአለም ላይ ያሉ አገሮችን ነጻነት ( ፍሪደም) በማወዳደር ሪፖርቱን የሚያወጣው አለማቀፋዊ እውቅና ያለው ፍሪደም ሀውስ የ2013 ሪፖርቱን ይፋ ሲያደርግ እንደገለጠው  ኢትዮጵያ ነጻነት የሌለባት አገር ናት ብሎአታል።
ፍሪደም ሐውስ የአለም አገራትን ነጻነት የሰፈነባቸው ከፊል ነጻነት ያለባቸውና ነጻነት የሌለባቸው አገራት በማለት በሶስት ከፍሎ የተመለከተ ሲሆን ፣ ነጻነት የሌለባቸው አገራት ተብለው የተፈረጁት መሰረታዊ የሆኑት የፖለቲካ መብቶች የሌሉባቸው፣ እንዲሁም የሰቪል ነጻነቶች የተነፈጉባቸው አገሮች ናቸው።

Friday, January 18, 2013

አስርቱ እኩኝ የወያኔ መንግስት ስትራተጂዎች



ከእለት ወደ እለት የወያኔ መንግስት በኢትዮጵያ ህዝብ ላይ የሚያደርሰዉ ግፍ እየተባባሰ ሀይ የሚለዉ በመታጣቱ፤ ምንአልባትም ብዙዎች የወያኔን ክፋት ቢያዩት በሚል ብእሬን እንዳነሳ ተገደድኩኝ፡፡ ወያኔ ስልጣን ላይ ከመጣበት ከ 1983 አነስቶ እስካሁን የስልጣን ዘመን ድረስ የኢትዮጵያን ሕዝብ ምን አተረፈ ምንስ ጎደለበት፤ ወያኔስ የገባዉ የተስፋ ቃል ምን ላይ ወደቀ ምንስ ግቡን መታለት እያልኩ ሳሰላ፤ ሚዛን የሚደፋ ምንም መልካም አጣሁ፡፡ ስለዚህ የወያኔ መንግስት ስልጣን ላይ ለዘመናት ለመቆየት የዘረጋቸዉን እኩይ እስትራቴጂዎች ከእዚህ በታች እደተዘረዘሩት ተመለከትኳቸዉ፡፡

Tuesday, January 15, 2013

‹‹አላሁ አእለም! ይቅርታ አንጠይቅም›


ሁለት ወቅታዊ ጉዳዮች

1. ከመለስ ሞት በኋላ መረጋጋት የተሳነው ኢህአዴግ ከበርካታ ችግሮች ጋር ፊት ለፊት ተፋጧል፡፡ ከችግሮቹ በከፊልም የሚከተሉት ይጠቀሳሉ፡፡ …በረከት ስምኦን የነበራው ተደማጭነት እየተሸረሸረ ነው፣ የበረከት ባለቤት የበረከትን መፅሃፍ ለመሸጥ (ገዥ ፍለጋ) በየተቋማቱ እየተንከራተቱ ነው፤ አዲሱ ለገሰ የተደማጭነት መስመሩን ‹‹ኢህአዴግን ለማጠናከር›› በሚል ምክንያት ይበልጥ እያደረጀ ነው፤ ደብረፅዮን ገ/ሚካኤል ከቀን ወደ ቀን በህወሓት ውስጥ ተሰሚነቱ እየጨመረ ነው፣ በእርግጥም ከድርጅቱ ከፍተኛ አመራሮች የአስጊ ህመም ችግር የሌለባቸው ተብለው የሚመደቡት ደብረፅዮን፣ አባይ ፀሀዬና ቴውድሮስ አድሃኖም ናቸው፣ አቦይ ስብሃት ነጋ ‹‹መፈንቅለ ፓርቲ›› በህወሓት ውስጥ ለማድረግ ቀን ከለሌት እያሴሩ ነው፣ ከሁለት ወር በኋላ የሚደረገው የኢህአዴግ ጠቀላላ ጉባኤ አዲስ ነገር ያስተናግዳል ተብሎ ይጠበቃል፤ ኦህዴድ በሹም ሽር ሊናጥ ነው፣ አለማየሁ አቱምሳ በሩቅ ምስራቅ ለሚከታተለው ህክምና እስከአሁን ያለውንም ሆነ በቀጣይ የሚያስፈልገውን ወጪውን እየሸፈነ ያለው ሼክ መሀመድ አላሙዲ ነው፤ ለምን? አለማየሁ የመንግስት ባለስልጣን ነው፣ በተጨማሪም ሆን ተብሎ በተሰጠው መርዝ ነው ታማሚ የሆነው የሚባለውን ወሬ ይዘን፣ ከዚህ ጀርባ ማን ነው ያለው? የሚል ጥያቄ መቀርቡ አይቀርም (የሰማሁት መረጃ ጆሮ ያቃጥላል) ግን ለምን? ኩማ ደመቅሳ መልካም አስተዳደር ባለማስፈንና ሙስናን መቆጣጠር ባለመቻል እየተወቀሰ ሲሆን፣ በተቃራኒው አባዱላ ገመዳ በኦህዴድ ውስጥ መረጋጋትን በማስፈንና ስራውን በብቃት በመወጣት በሚል ተመስግኗል፣ (የማኪያቬሊ ከፋፍለ ግዛ ማለት ይህ ይሆን?) በሚያዚያ ወር የሚደረገውን ምርጫ ተከትሎ የቱኒዝያንና የግብፅን መሰል ህዝባዊ አመፅ ይቀሰቀሳል በሚል አገዛዙ ፍርሃት አድሮበታል፣ 33ት ፓርቲዎች ነገ በምርጫው ላይ የሚኖራቸውን አቁም በሰማያዊ ፓርቲ ፅፈት ቤት ከጠዋቱ አራት ሰአት ላይ የፋ ያደርጋሉ (በእርግጥ የደረሱበት ውሳኔን ብግሌ ትክክል ነው ብዬ አምናለሁ፣ ከዚህ ውጪም ገዥው ፓርቲን ለድርድር የሚያስገድድ ዕድል የላቸውም)፣ በአማራ ክልል ደቡብ ጎንደር ኦስትሪያዊውን አገር ጎብኚ ማን ገደለው? ለምን ተገደለ? የደብረማርቆስ ማረሚያ ቤት ድራማስ በማን የተቀነባበረ ነው? ኃላፊነቱንስ ማን ነው የሚወስደው? የብሄራዊ መረጃና ደህንነት ኤጀንሲ ¬¬‹‹ለሽብር ድርጊት ሊውል ሲል ደረስኩበት›› በማለት ከተቀበረበት እንዳወጣው የነገረንን የጦር መሳሪያ ማነው የቀበረው? ይህ መሳሪያስ በእነማን የክስ መዝገብ ላይ ማስረጃ ሆኖ ሊቀርብ ነው የታቀደው? በቀጣይስ የቦንብ ፍንዳታ በየትኛው ከተማ፣ መቼ፣ ስንት ሰዓት ላይና በምን ሁኔታ ይደርስ ይሆን? …ይህኛው መንገድስ የት ድረስ ያስኬዳል? ‹‹አዲስ ታይምስ›› መፅሄትን ማፈኑስ ለምን አስፈለገ?

አዉራ የሌለዉ ትግል፤ እረኛ የሌለዉ መንጋ ነዉ - እኔ መሪዩን መርጫለሁ እናንተስ?



ከፍስሃ እሸቱ (ዶ/ር)


በቅርቡ ከዳር ቆሞ ለዉጥን መጠበቅ የህልም እንጀራ በሚል በትግሉ ጎራ ላይ ያለኝን የግሌን አመለካከት የሚገልፅ ፅሁፍ ለወገኖቼ ማቅረቤ ይታወሳል። ይንንኑም ተከትሎ የተለያዩ አስተያቶች ከበርካታ አንባብያን ደርሰዉኛል። ወገኖቼም በቀረበዉ ሀሳብ ላይ ተነስታችሁ ለሰጣችሁኝ ገንቢ አስተያቶች የከበረ ምስጋናዬን አቀርባለሁኝ። ከበርካታ ወገኖችም በፅሁፉ የተዘረዘሩትን ችግሮችና የመፍትሄ ሀሳቦች በመገምገም በቀጣይነት ምን ማድረግ አለብን ትላለህ የሚሉ በርካታ ጥያቄዎችም ቀርበዉልኛል። በበኩሌም ለጥያቄዉ ከፍተኛ ትኩረትን በመስጠት የላይና የታቹን በማሰላሰል፤ የግራና የቀኙን በማመዛዘን፤ በልቤ የሚሰማኝን ከህሊናዩ ጋር በመሟገት ለዉይይትና ለተግባራዊነቱ በጋራ እንድንቀሳቀስ አዲስ ሀሳብ (thesis) አቀርባለሁኝ።

“የመለስን ሌጋሲ ማስቀጠል የማንችል ከሆነ ህዝቡ እሳት ሆኖ እንዳያቃጥለን እንሰጋለን” ሲሉ የኢህአዴግ አባላት ተናገሩ

ጥር ፬ (አራት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም 
በሚስጥር የደረሰን በአዲስ አበባ  የኢህአዴግ ድርጅት ጽህፈት ቤት ያዘጋጀው ሚስጢራዊ ሪፖርት እንደሚያመለክተው  የኢህአዴግ አባላት ከመለስ ሌጋሲ እና ከልማት ጋር የተያያዙ በርካታ ጥያቄዎችን ማንሳታቸው ተመልክቷል።
የኢህአዴግ አባላት  ካነሱዋቸው ሀሳቦች መካከል “  መስመሩን ያላወቁ አባላት ባለበት እንዴት ሌጋሲውን ማስቀጠል ይቻላል? አባሎች ራሳቸው ጀርባቸው መጠናት አለበት፣ ንፋስ ወደ ነፈሰበት የሚነፍሱ ቁጥራቸው እየበዛ ነው፣ የመለስ ሌጋሲ ሊኖር የሚችለው ስርአቱ እስካለ ድረስ ነው፣ የሚስጥር ጠባቂነት ችግር በአመራሩ ከላይ እስከታች አለ፣ አመራሩ ኪራይ ሰብሳቢነትን አምርሮ አይታገልም፣ህወሀት ሀይለማርያምን ማስቀጠል የለበትም ምክንያቱም ታግሎ የመጣ ሰው ነው መምራት ያለበት”   የሚሉት ይገኙበታል።

Monday, January 14, 2013

ዐቃቤ መንበሩ መንግሥት ጣልቃ እንዲገባ መጠየቃቸው ተሰማ


  • ዕርቀ ሰላሙንና የፓትርያሪክ ምርጫውን በተጓዳኝ እንዲካሄድ ለማስወሰን ታስቧል
  • ‹‹ዕርቀ ሰላሙ ይቅደም›› የሚሉት አባቶች አቋምና ብዛት እየተጠናከረና እየጨመረ ነው
  • የሰላምና አንድነት ጉባኤው ለቅዱስ ሲኖዶሱ ደብዳቤ ጽፏል
  • ከ4ው ፓትርያሪክ ጋራ ፊት ለፊት መወያየት ቀጣይ የመነጋገሪያ ነጥብ ነው ተብሏል
ቅ/ሲኖዶስ በነገው ዕለት አስቸኳይ የምልአተ ጉባኤ ስብሰባ ለመቀመጥ በሚዘጋጅበት ዋዜማ ዐቃቤ መንበረ ፓትርያሪክ ብፁዕ አቡነ ናትናኤል መንግሥት ጣልቃ እንዲገባ በይፋ መጠየቃቸው ተሰማ፡፡ ዐቃቤ መንበሩ ጥያቄውን ያቀረቡት ለመንግሥት አካል በጻፉት ደብዳቤ ነው ተብሏል፡፡ ደብዳቤው የተጻፈው ሁለት ከፍተኛ የመንግሥት ባለሥልጣናት (አቶ ኣባይ ፀሃዬ እና ዶ/ር ሽፈራው ተክለ ማርያም) በሳምንቱ መጨረሻ በዐቃቤ መንበረ ፓትርያሪኩ ቢሮ ተገኝተው ከተወያዩ በኋላ መኾኑ ተገልጧል፡፡
ጥያቄው ስለቀረበበት ምክንያት የዜናው ምንጮች ሲያስረዱ÷ ‹‹ቅድሚያ ለዕርቀ ሰላሙ›› በሚል ለስድስተኛው ፓትርያሪክ ምርጫ የሚደረገውን ዝግጅት በሚቃወሙ ብዙኀን ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት እና ‹‹ዕርቀ ሰላሙ ከፓትርያሪክ ምርጫው ጋራ ግንኙነት የለውም፤ ሁለቱም በተጓዳኝ/በትይዩ ሊከናወኑ ይችላሉ›› በሚሉ ጥቂት ነገር ግን ተጽዕኖ ፈጣሪ ናቸው በሚባሉ ብፁዓን ሊቃነ ጳጳሳት መካከል በተያዘውና ከዕለት ወደ ዕለት እየተካረረ በመጣው ፍጥጫ ሳቢያ ነው ብለዋል፡፡

Saturday, January 12, 2013

የኢትዮጵያ ብሄራዊ የሽግግር ምክር ቤት በአበበ ገላዉ ላይ በወያኔ ስርአት የተቃጣዉን የግድያ ሴራ አስመልክቶ መግለጫ አወጣ


ከኢትዮጵያ ብሄራዊ የሽግግር ምክር ቤት በጀግናዉ አበበ ገላዉ ላይ በወያኔ ስርአት የተቃጣዉን የግድያ ሴራ አስመልክቶ የተሰጠ መግለጫ
ENTC
ጥር 10/2013 ዓ/ም (እኤአ)በቅርቡ ጀግናዉ አበበ ገላዉን ለመግደል በህወሀት/ኢህአዴግ የተጠነሰሰ ሴራ በአሜሪካ በFBI መጋለጡንና ተጠርጣሪዎቹም መያዛቸዉንና ምርመራ ላይ መሆናቸዉ ተገልጿል። ይህን እጅግ አሳፋሪ ተግባር የኢትዮጵያ ብሄራዊ የሽግግር ምክር ቤት አጥብቆ ያወግዛል። የፋሽሽቱና ዘረኛዉ ህወሀት/ኢህአዴግ ስርአት ምርጫ 97ትን ተከትሎ በውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ተረቆ በአዉሮፓ አሜሪካና በሌሎች ሃገሮች ለሚገኙ የኢትዮጽያ ኤምባሲዎች በሚስጢር የተሰራጨው ባለ 52 ገጽ በአለም ዙሪያ የሚገኙ ተቃዎሚዎችን ለመምታትና ለማዳከም ያወጣዉን እቅድና ዝርዝረ ጉዳዮችን የያዘ የስርአቱ ሰላዮች ሰነድ ሾልኮ በመውጣቱ ለኢትዮጵያኖችና ለአለም አቀፍ ህብረተሰቡ ይፋ መሆኑ የታወሳል።

የአቶ መለስ ዜናዊ ዜና እረፍት በተሰማ ማግስት አንድ ሃገር ወዳድ ኢትዮጵአዊ ከአውሮፓ ለአበበ ገላው ስልክ ይደውልለታል።


የአቶ መለስ ዜናዊ ዜና እረፍት በተሰማ ማግስት አንድ ሃገር ወዳድ ኢትዮጵአዊ ከአውሮፓ ለአበበ ገላው ስልክ ይደውልለታል። ግለሰቡ ደጋግሞ ሲደውል የአበበ የእጅ ስልክ ጠፍቶ ስለነበር ሶስት ተከታታይ የድምጽ መልእክቶችን ትቶ ነበር።

አበበ እባክህን ባስቸኳይ መልሰህ ደውልልኝ። አንተን በተመለከት ከአገርቤት የመጣ መረጃ አለ።እባክህን መልሰህ በዚህ ቁጥር አስቸኳይ ደውልልኝ።ይላል መልእክቱ። ደዋዩ ከልብ እንደተጨነቀ ከድምጹ መረዳት ይቻላል።

Thursday, January 10, 2013

Torture, Inhuman Treatment and Arbitrary Detention in Ethiopia


Independent human rights organizations such as Human Rights Watch, Amnesty international, and the Anti-TortureAtrocious Torture and Inhuman Treatment in EthiopiaCommittee of the United Nations have several times reported of systematic persecution as well as use of violence and torture against Ethiopian journalists, opposition political leaders and members as well as anyone who are critical of the tyrannical regime. Amnesty International, for instance, says in its press release issued on 28 August 2012 that it regularly received several information about the use of torture in pre-trial and arbitrary detention.

Wednesday, January 9, 2013

‘‘የሕሊና ሰላም አለኝ’’ አንዱአለም አራጌ


በሽብርተኝነት የወንጀል ክስ ቀርቦበት በፌዴራሉ ከፍተኛ ፍ/ቤት 3ኛ ወንጀል ችሎት ጥፋተኛ ተብሎ የዕድሜ ልክ የተፈረደበት የአንድነት ለፍትህና ለዲሞክራሲ ፓርቲ አመራር የነበረው አንዱአለም አራጌ ‘‘የሕሊና ሰላም አለኝ’’ ሲል ለፓርቲው አመራሮች ተናገረ። 
አንዱአለም ይሄንን ቃል የተናገረው ባለፈው እሁድ ታህሳስ 28 ቀን 2005 በቃሊቲ ማረሚያ ቤት ተገኝተው ለጠየቁት የፓርቲው አመራር አካላት ነው። የፓርቲው ሊቀመንበር ዶ/ር ነጋሦ ጊዳዳን ጨምሮ ሌሎች 15 የሚሆኑ የፓርቲው አመራሮች፣ የጽ/ቤት ሰራተኞችና የፓርቲው አባላት የገናን በአል ምክንያት በማድረግ በማረሚያ ቤቱ በመገኘት ጠይቀውታል። 

የጋዜጠኛ ርዕዮተ አለሙ የሰበር ይግባኝ ውድቅ ተደረገ


የፌዴራሉ አቃቤ ህግ የአገሪቱ አንድነት እና ህገመንግስታዊ ስርዓቱን ለመናድ ተንቀሳቅሳለች ሲል ውጪ ሀገር ለሚገኙና ለአንደኛው ተከሳሽ ኤሊያስ ክፍሌ አማካኝነት መረጃዎችን አቀብላለች ሲል በአንደኛ ክስ እንዲሁም፤ በሽብርተኛ ቡድን ውስጥ በህቡዕ በመሳተፍ አባል በመሆንና አባል በመመልመል ጭምር ተሳትፋለች እና ከኤርትራ መንግስት እና ከግንቦት ሰባት ጋር ምስጢራዊ ግንኙነትን በመጠቀም ከሽብር ቡድኑ የሚገኝን ገንዘብ ተቀብላ ጥቅም ላይ አውላለች የሚሉ ሦስት ክሶችን ያቀረበባት ጋዜጠኛ ርዕዮት አለሙ፤ በይግባኝ ሰሚ ሰበር ችሎት ያቀረበችው አቤቱታ ትናንት ውድቅ ሆነ። 

በሃይማኖት ጉዳዮች ውስጥ የሚደረገው ጣልቃ ገብነት ይቁም!




በሃይማኖት ጉዳዮች ውስጥ የሚደረገው ጣልቃ ገብነት ይቁም!
የህወሓት/ኢህአዴግ መንግሥት በሃይማኖቶች የውሰጥ አስተዳደር የሚያደርገውን ጣልቃ ገብነት አሁንም በፊት ከነበረው በበለጠ አጠናክሮ ቀጥሎበታል። የውስጥ አሰተዳደራችን ይከበርልን ብለው በሰላማዊ መንገድ በጠየቁ የእስልምና ዕምነት ተከታይ ኢትዮጵያውያን ላይ እየወሰደ ያለው እርምጃ ዘግናኝና አሳፋሪ ከመሆን አልፎ ፍጹም -ዴሞክራሲያዊ መሆኑ ያሳሰበናል።   በትዕቢት የተወጠረው ህወሓት/ኢህአዴግ ግን አሁንም በማናለብኝነት የእስልምና እምነት ተከታይ ማኅብረሰብ ተወካዮችን በአሸባሪነት አስሮ እያንገላታቸው፤ እያሰቃያቸውና እየገደላቸው መሆኑ ለኢትዮጵያ ሕዝብ የተሰወረ አይደለም። ይህ አጉራ ዘለል የመብት ረገጣ በተቃዋሚው ጎራ ብቻ ሳይሆን በውጭ መንግሥታትም ጭምር ተቃውሞ እየቀረበበት ያለ ቢሆንም ህወሓት/እህአዴግ ግን ከዚህ እኩይ ተግባሩ ሊታቀብ አልቻለም።