Saturday, January 26, 2013

ለካንስ ሁሉ ነገር ጨለማ አይደለም?!

ጭዋታው ከመካሄዱ አንድ ቀን ቀደም ብየ ይህን ፅፌ ነበር። "ይህ ሰውየ ምናለ ቢለቀን ሞቶም ይህ የአጋንንት መንፈሱ አለቀቀም። ይህ መንፈስ ደቡብ አፍሪካ ድረስ ሄዶ የኔ ምስል ያለበትን ቲሸርት ካላደረጋችሁ እያለ በተጫዋቾች መሀል የስነልቦና ጫና እየፈጠረ ነው። አብዛኛዎቹ እንቢታን ሲመርጡ ጥቂቶች ግን በውስጥ ደርበን እንለብሳለን ጎል ሲገባም በአደባባይ ይህን ሙት ሰውየ እናሳያለን እያሉ ተጫዋቾቹን እየከፋፈሉ ነው። በደቡብ አፍሪካ የምትገኙ ኢትዮጵያኖች እንዳታሳፍሩን። ይህን መንፈስ ወደ ኢትዮጵያ እንዳይመለስ አድርራችሁ እዛው ውቅያኖስ ውስጥ ጨምሩት። ድል ለብሄራዊ ቡድናችን።" እንዳልኩትም ይህ አጋንንት መንፈስ ሳውዝ አፍሪካ ድረስ ተካትሎ ሄዶ ተጫዋቾቻችን ድንብርብራቸውን አወጣው። የዝህ ሰውየ መንፈስ እስካለ ድረስ ኢትዮጵያ ሰላም አታገኝም።

ለካንስ ሁሉ ነገር ጨለማ አይደለም?! ግድ የለም ተስፋ እናድርግ! በሞት አፋፍ ላይ እንኳን የመዳን ተስፋ አለም አይደል?? !! ብሄራዊ ቡድናችን ሁለት ዕድል አለው። ናይጄሪያን ማሸነፍ፡ ቡርኪናፋሶ ዛምቢያን ማሸነፍ....ይሄኛው በቀጥታ ያሳልፈናል። ወይም ደግሞ ናይጄሪያን አሸንፈን ሁለቱ ደግሞ አቻ ቢወጡ! ይሄም ያሳልፈናል። ግድየለም እንጸልይ! የዛምቢያ ተጨዋቾችን እግር ቄጤማ ያድርግል! ኢህአዴግም የመለስን ቲሸርት ገለመሌ እያለ ተጫዋቾቻችን አያስጨንቅብን! እኛ በጸሎቱ ከበረታን፡ ተጫዋቾቻችን በሞራል ከበረቱልን፡ ቡርኪናፋሶዎች ማሸነፍን ኣላማ አድርገው ወጥረው ከተጫወቱ፡ዛምቢያዎችን አንዳች ሃይል ካዳከመልን፡ የኢህአዲግ ሰዎች ከስፖርቱ እጃቸውን ከሰበሰቡልን እውነቴን ነው የምላችሁ እናልፋለን!
ተጫዋቾቻን ለምን ተሸነፉ? በእርግጥ ኳስ ነው። የስነልቦናው ጉዳት አስተዋጽኦ እንዳለው ይታመናል። የሟቹን ጠቅላይ ሚኒስትር ፎቶ ያለበትን ቲሸርት እንዲያደርጉ ጫና መፈጠሩ ስነልቦናቸው ላይ ጉዳት ነበረው። ይህ ቡድን ከዛምቢያው ጨዋታ በኋላ የቡድን ስሜቱ ደብዝዟል። የኢህአዴግ ሰዎች በእርግጥ ከዚህ አንጻር ብቸኛ ተጠያቂ ናቸው።
               ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር!!!

No comments:

Post a Comment