Thursday, December 24, 2015

ኦቦ በቀለ ገርባ ታሰሩ

(ዘ-ሐበሻ) በኦሮሚያ የተለያዩ ከተሞች የተነሳውን የሕዝብ ቁጣ ተከትሎ በርካታ ወጣቶችን እያሰረ የሚገኘው ሕወሓት መራሹ መንግስት ባለፈው ማርች 2015 ከ እስር የተፈቱትን አቶ በቀለ ገርባን እንደገና አሰረ::
ዘ-ሐበሻ ከአዲስ አበባ ምንጮቿ እንዳገኘቸው የኦሮሞ ፌዴራሊስት ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ ምክትል ሊቀመንበር የሆኑት ኦቦ በቀለ ገርባ ዛሬ የታሰሩት በኦሮሚያ የተለያዩ ከተሞች ከተከሰተው የሕዝብ ቁጣ ጋር ተያይዞ እንደሆነ ይገመታል::
ኦቦ በቀለ ከቤታቸው ሲወሰዱ በርካታ የደህንነት ሃይሎች እና ፖሊሶች እንደነበሩ ጨምሮ የደረሰን መረጃ ያስረዳል::

Monday, December 21, 2015

የትግራይ ሽፍቶች ለምን ወንድሞቻቸውን ይገድላሉ? – ፕሮፌሰር መስፍን ወልደማሪያም

አፄ ምኒልክ ጦራቸውን ሰብስበው በእግርና በበቅሎ ከደቡብ ተነስተው ትግራይ እስቲደርሱ ኤርትራና ትግራይ ምን አድርገው ጠበቁዋቸው? የኢጣልያ ጦር ትግራይን ሰንጥቆ አምባ አላጌ እስቲደርስ ማን ሊያቆመምው ሞከረ? የኢጣሊያ ጦር መቀሌ ገብቶ ሲመሽግ ማን ተከላከለው? ስብሓት እስከዛሬ ሳይገለጥለት ቀርቶ ከሆነ የኢጣልያንን ጦር ከአምባ አላጌ ያስወጣው የምኒልክ ጦር ነው፡፡ ከመቀሌም ምሽግ ያስወጣው የጣይቱ ዘዴና የምኒልክ ጦር ነው፡፡ በኢትዮጵያዊ ይሉኝታ ተሸፋፍኖ የቆየውን እናፍረጥርጠው ከተባለ ለማን አሳፋሪ እንደሚሆን ግልጽ ነው፡፡

በቅርቡ የምንሰማው ዜና በጥምር ተቀናጅተው ኦነግ እና አርበኞች ግንቦት 7 ኢትዮጵያን ነጻ ለማውጣት ወደፊት እየገሰገሱ ወያኔን መቆሚያ እያሳጡት ነው የሚለው ይሆናል።

ምከረው ምከረው እንቢ ካለ መከራ ይምክረው እንደሚሉት አበው 25 ዓመት ሙሉ ሲመከር ሲለመን ሲዘከር ምክርን እንደ ስድብ ልመናን እንደ ፍራቻ ዝክርን እንደ ማታለል አድርጎ በመቁጠር ዝም በሉ ዝም ካላላችሁ ዝም አደርጋችሃለሁ ረግጫችሁ እገዛችኋል አማራና ኦሮሞን አጋጭቶ በመሃል እኔ ስልጣኔን እያደላደልኩኝ 100 ዓመት እገዛለሁ ብሎ የቀየሰው ስልት ዛሬ በእርግጠኝነት መናገር ወደሚቻልበት ትግል የኢትዮጵያ ህዝብ  በመግባቱ ታውቋል። ኦነግና  አርበኞች ግንቦት 7 የተቀናጀ ድምጽ አሰምተውን ኦነግ በአሶሳ ፤በሀረር ፤በቦረና ወያኔን እየደመሰሰ ወደ ፊት እየመጣ ነው። አርበኞች ግንቦት 7 በጎንደር፤ በጎጃም ፤በደቦብ በድሬደዋና በመላው ኢትዮጵያ ብሎም በአዲስ አበባ ትግሉን በማቀጣጠል ወያኔን መቆሚያና መቀመጫ እያሳጡት ነው የሚለውን ዜና እንሰማለን።

ዳር ድንበራችን በአገር ከሃዲዎች አይሸጥም!

የኢትዮጵያ ድንበር ጉዳይ ኮሚቴ Ethiopian Border Affairs Committee P. O. Box 9536 Columbus, Ohio 43209 USA E-mail: ethiopianborders@gmail.com
 ዳር ድንበራችን በአገር ከሃዲዎች አይሸጥም!
 ከኢትዮጵያ ድንበር ጉዳይ ኮሚቴ የተሰጠ መግለጫ ታህሳስ 7 ቀን 2008 ዓ/ም ( December 17, 2015 ) በቅርቡ የወያኔ ጠቅላይ ሚኒስቴር አቶ ኃ/ማርያም ደሳለኝ የሱዳንን ምክትል ፕሬዚዳንት ተቀብለው ባነጋገሩበት ወቅት በሰጡት መግለጫ በያዝነው ወር ውስጥ የኢትዮጵያና ሱዳን ድንበር በመሬት ላይ የመካለሉ ሥራ እንደሚጀመር በድፍረት የሰጡት ቃል የኢትዮጵያ ድንበር ጉዳይ ኮሚቴን ጨምሮ መላው የኢትዮጵያን ሕዝብ በእጅጉ ያሳዘነና ያሳፈረ ከፍተኛ የአገር ክህደት ወንጀል ነው።

ፍልስፍና አልባ የሆነ አገዛዝና የፖለቲካ ትግል ዘዴ የአንድን ህብረተሰብ አስተሳሰብ ያዘበራርቃል - የመጨረሻ መጨረሻም አገርን ያወድማል!

 ፍልስፍና አልባ የሆነ አገዛዝና የፖለቲካ ትግል ዘዴ የአንድን ህብረተሰብ አስተሳሰብ ያዘበራርቃል - የመጨረሻ መጨረሻም አገርን ያወድማል! ፈቃዱ በቀለ፣ ዶ/ር 
 ከረዥም ጊዜ ጀምሮ በብዙ አፍሪካ አገሮች የሚታየው የአስተዳደር ብልሹነት፣ የህዝቦች ኑሮ መዘበራረቅና ዓላማ-ቢስ መሆን፣ እንዲያም ሲል በአንድ አገር ውስጥ የሚኖር ህዝብ በሃይማኖትና በጎሳ አሳቦ ርስ በርሱ እንዲጠላላ ማድረግና፣ የመጨረሻ መጨረሻም ወደ ርስ በርስ መተላለቅ እንዲያመራ መንገዱን ማዘጋጀት፣ በተራ አነጋገር ከመልካም አስተዳደር እጦት፣ ከአምባገነናዊ አስተዳደር መስፈንና ከዲሞክራሲ አለመኖር ጋር ሲያያዝ ይታያል። አንዳንዶች እንዲያውም እንደዚህ ዐይነቱን ዓላማ-ቢስ የህብረተሰብ ጉዞ የአፍሪካ መሪዎች ወይም የጥቁር ህዝብ ችግር አድርገው የሚመለከቱ አሉ። በእርግጥ ለአንድ አገር ስርዓት ባለው መልክ መተዳደርና፣ ህብረተሰቡም በዕቅድና በዓላማ እንዲመራ ከተፈለገ በዚያ የሰፈነው አገዛዝ ህብረተሰቡን በማደራጀት ረገድ የሚጫወተው ሚና አለ።

የዲሞክራሲ መብት መሳሳት ጭምር ነው!!!

 ግርማ ሠይፉ ማሩ 
girmaseifu32@yahoo.com
 ሰሞኑን በሀገራቸን ያሇው ትኩሳት በኦሮሚያ ክሌሌ የተከሰተው በአብዛኛው ተማሪውን ያሳተፈው “እንቢ የተቀናጀ ማስተር ፕሊን” በሚሌ የተነሳው ንቅናቄ ነው፡፡ ሇዚህ ንቅናቂ መንሰዔ ናቸው በሚሌ የኦሮሚያ ክሌሌ እና የፌዳራሌ መንግስቱ ከፍተኛ የኦህዳዴ ሾሞች መግሇጫ እየሰጡ ይገኛሌ፡፡ በእነሱ መግሇጫ መሰረት ዯግሞ ጥያቄው ከዚህም አሌፎ የመሌካም አሰተዲዯር ጭምር መሆኑን አምነዋሌ፡፡ ሁሊችንም እንዯምናሰተውሇው ኦህዳዴ ውስጥ የሚታየው ከፍተኛ የተማረ የሰው ኃይሌ እጥረት ከተወሰኑ ሰዎች ውጭ ሇማየት እዴሌ አሌሰጠንም፡፡ ይህ ባጠቃሊይ በኢህአዳግ ውስጥ ያሇ ችግር ነው፡፡ የዚህ ችግር ምንጭ ገዢው ፓርቲ የሚከተሇው መስመር ሇተማረ ቀርቶ ሇሚያመዛዝን ሰው እንኳን ምቾት የሚሰጥ አሇመሆኑ ነው፡፡ ኤርሚያ ሇገሠ የሚባሇው የቀዴሞ ኢሕዳግ ሹም ሂሣብ ተምረህ እንዳት ኢህአዳግ ሆንክ? የሚሌ ጥያቄ እንዯቀረበሇት ሰምቻሇሁ፡፡

Sunday, November 22, 2015

በ1997 ምርጫ

በ1997 ምርጫ የኢትዮጵያ ህዝብ የህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ ስርዓትን በቃኝ ብሎ በድምጹ ከወሰነና በኋላም ህወሀት አስከፊ እልቂት በመፈጸም በስልጣን ላይ መቆየቱን እንዳረጋገጠ ነው። በመላው ኢትዮጵያ ተማሪዎች: መምህራን: ሰራተኞች: ነጋዴዎች ሁሉም የህብረተሰብ ክፍል በየተራ ያን መከረኛ ስልጠና እንዲወስዱ ዘመቻ የታወጀበት ጊዜ ነው። በአዋሳ ስልጠናው እየተሰጠ በአንዱ ቀን እንዲህ ሆነ። የብአዴኑ አመራር አቶ ተፈራ ዋልዋ በፕላዝማ ስልጠና ይሰጣል ። አማራው እንዴት አድርጎ ሌላውን የኢትዮጵያ ብሄረሰብ እንደበደለ: የሰው መሬት እንደተቆጣጠረ ያልተጻፈ ታሪክ እየጠቀሰ መርዝ የሆነ የዘር ማጥፋት ድርጊት እንዲፈጸም ጥሪ ያደርጋል።

ኃይሌ ገ/ስላሴ ለእኔ



የስፖርተኞች ስም የተለጠፈበት ልብስ ለብሼ አላውቅም፡፡ ግን በስማቸው የታተመ ልብስ ብለብስላቸው ከማያሳፍሩኝ መካከል ኃይሌ አንዱ ነበር፡፡ ገና በልጅነቴ በሬድዮ የሀይሌን ማሸነፍ ሰምቼ ዘልያለሁ፣ ተሸነፈ ሲባል በጣም አዝኜ አውቃለሁ፡፡ እስከ ቅርብ ጊዜ ድረስ ለኃይሌ የተለየ ስሜት ነበረኝ፡፡ በቅርብ ግን ኃይሌ እየወረደብኝ መጣ፡፡ በቅርብ አመታት ኃይሌ ለምን ድሆችን (አካል ጉዳተኞችም፣ ህጻናትና አዛውንቶችን ጨምሮ) እንደማይረዳ ሲጠየቅ በተደጋጋሚ ‹‹ሰርተው ይብሉ!›› ሲል አዳምጬ ገርሞኛል፡፡ የሜቄዶንያው ቢኒያም ይህ የኃይሌ አባባል እንዴት ያናድደው?!
ከ3 አመት በፊት ግን የኃይሌ ስም ያረፈበትን ቲሸርት ብለብስ ኖሮ ይቆጨኝ እንደነበር የሚያስታውስ ነገር ሲናገር ሰማሁት፡፡ ‹‹ለምን ሰርተው አይበሉም!›› የሚለው ኃይሌ ሰርተውም የዋጋቸውን የማይከፈላቸው መምህራን ‹‹የስራ ዋጋችን ይከፈለን፣ ደመወዝ ይጨመርልን!›› የሚል ጥያቄ ሲያነሱ፣ እሱን የለመኑት ይመስል ይህን ጥያቄ ቅብጠት አድርጎ ሲወርፋቸው በሬዲዮ ሰማሁ፡፡

Tuesday, September 29, 2015

መግለጫ ወይንስ መጋለጫ – የሞላ አስግዶም ኩብለላ (ይገረም አለሙ)

ይገረም አለሙ
ከአንድ ሳምንት ወሬ የማይዘለው የሞላ አስግዶም ኩብለላ ብዙ ነገሮችን አያሳየን ነው፡፡ ወያኔ የሞላ ኩብለላ የሱ የሥራ ውጤት እንደሆነ አሳያለሁ ብሎ “ በቅሎ ሽንቷን አጠራ ብላ ሀፍረቷን አሳየች” የሚባለውን አይነት ድርጊት ፈጸመ፡፡ ለነገሩ ወያኔ መቼ ሀፍረት ያውቅና፡፡ አቶ ሞላም የተሰጠው ስልጠና የአጭር ግዜ ሆኖበት ሽክ ብሎ የቀረበበትን ጋዜጣዊ መግለጫ የወያኔና የራሱ መጋለጫ አደረገው፡፡ የወያኔ የመረጃ ስራ በጉልበት አንጂ በእውቀት እንዳልሆነ የምናውቀውንም ይበልጥ አረጋገጠልን፡፡Mola Asgedom's defection
የቱንም ያህል ቢጩኹ፤የቻሉትን ያህልም ውሸት ቢደራርቱ እውነትን ማሸነፍ እንደማይቻል ወያኔዎች ብዙ ግዜ ሞከራው ከሽፎባቸው ያዩት ቢሆንም አንዴውኑ ከእውነት ጋር ተጣልተዋልና የህይወት መሰሶአቸውም ውሸት ሆኖአልና ከውሸት ሊላቀቁ አልቻሉም፡፡ ዛሬም እየዋሹ ብዙሀኑን ኢትዮጵያዊ በግድ ሊግትቱ ይዳዳቸዋል፡፡ ጥቂት አይናቸውን ለጆሮአቸው ያስገዙ ሰዎቻቸው ደግሞ እንዴት ብሎ መጠየቅ ለምን ብሎ ማመዛዘን የለም ብቻ ውሸቱን እየተቀበሉ ከበሮ ይደልቃሉ፡፡እውነቱ ሲጋለጥም ሌላ ውሸት ይፈበርካሉ እንጂ ለእውነት እጅ አይሰጡም፡፡

የሞላ አስገዶም ነገር!

በተስፋዬ ነጋ (ዋሽንግተ ዲሲ)
ኢቲቪ ስለትህዴን መክዳት የለፈለፈው፣ አቶ ሞላ ስለ ፕሮፌሰር ብርሃኑ ነጋ፣ ስለተቃዋሚዎቹ፣ የሻብያን ጦር “እየደመሰሱ” ስለመምጣት በግነት የተናገረው፣ ሌላው የትሄዴን ጊዜያዊ ሃላፊ ኮማንድር መኮንን ተስፋዬ ስለከዳው የትህዴን ጦር እና ስለውጊያው የተናገረው እና የተለያዩ ሌሎች አስተያየቶች ሰሞኑን በማህበራዊ ድህረገጾች ተለቀዋል፣ ኢትዮጵያውያን በነቂስ ተወያይተውባቸዋል። እኔም ውይይቱን መልሼ መድገም አልፈልግም፥ የእኔ አላማ የአቶ ሞላ አስገዶም በተለያዩ አካላትና ሁኔታዎች መዳፍ ስር ቢወድቅ ኖሮ በጥትቅ በሚታገሉ የኢትዮጵያ ተቃዋሚዎች፣ በኢትዮጵያ መንግስትና፣ በኤርትራ መንግስት ላይ የሚፈጥረው አዎንታዊና አሉታዊ ተፅዕኖዎች በአጭሩ መዳሰስ ነው።

የሰካራም እግርና የሞላ አስገዶም ምላስ

ቹቸቤ
ቹቸቤ ነኝ እንዴት ከረማችሁ? በዐል እንዴት ነበር? ጉድ ሳይሰማ መስከረም አይጠባም አሉ የአገራችን ሰዎች። ዘንድሮ ከጉድም ጉደኛ ሰው ከወደ ሰሜን አቧራውን አጬሰውና የኔንም ቀልብ ሳበው። ኢካድፎች ይህንን ከሰማያዊ ፓርቲ ተዘረፈ የሚባለውን በልኩ ያልተሰፋ ሱፍ ግጥም አድርጎ ‘እኛ እኮ አንቻልም’ የሚለውን ሰውዬ አሳይታችሁን እኔንም ለሳቅና ለቅሶ ጋበችሁኝ። ሳቅሁኝ በሞላ ለጋሰራሽ ድራማ። አለቅስኩኝ ኢትዮጵያችን ሰው አጥታ ሞላ የስንትና ስንት ሺህ የነጻነት አርበኞች መሪ ነበር የሚለውን ሳስብ። ቢሆንም አቶ ተሰማ እሸቴ አንዳንድ አርበኛ የሚለውን ስም የማይመጥኑትን ለመግለጽ “እዩት ተመልከቱት የአምላክን ደግነት …. እንዴት ያስደስታል አርበኛ ሲጫወት” ብለው የተቀኙትን አስታውሼ እውነትም አር-በኛ ተጫወተብን አልኩኝ …. ሞልዬ ጎምላላዬን አይቼና ለመስማት ሞክሬ።

ፕሮፓጋዳ ዓይን ያወጣ ውሸት ማቅረብ አይደለም፣ የሚሰራ መሆን አለበት፣ ጎብልስና ወያኔ

ከቢላል አበጋዝ – ዋሽግቶን ዲሲ
የወያኔ ትልቁን “ኩዴታ” ጥምረት ውህደትን “በሾኬ የጣለበትን” የወሬ ጋጋታ እንግዲህ አለፍነው። ተመስገን። ሰማይ አልተደረመሰም። የወያኔ ቲቪ ሰዓት እላፊ ሰራ። በዳያስፖራ ያሉ የወያኔ አሽከሮች “የፍየል ወጠጤ” ዓይነት መልክት አስተጋቡ። ወያኔን አትንኩብን አሉ። የአንድን ሰው መክዳትን ድል አድርገው ሊያደናቁሩ ተሟሟቱ። አዲስ የተሻሻለች ህወሃትን የሚሹ ምሁራንም የቆሙበት በግልጥ ታየ። ሌሎችም ጥምረት ውህደቱን ተቹ። ህብረት እንፍጠር ያላችሁ ሳይገባችሁ ነው አሉ። የሞላ መክዳትት ወሬ ጥቂቶችን አናዞ እያለፈ ነው።መጭውን የወያኔ “የረቀቀ ስለላ ውጤት” እስክንሰማ እንጠብቃለን።የሞላ አስከዶም ተገቢው ጎራ መዘነቅ ወሬው ቶሎ ከሰመ::ከዚህ የሚያልፍ አይደለም።ግን መጥኔ ለአዲሳባ!

ትግሉ ለዴሞክራሲያዊ ስርአት ወይንስ ለምንይልክ ቤተ መንግሥት (ይገረም አለሙ)

ይገረም አለሙ
ፈጣሪ ዕድሜ ከጥንካሬ ጋር ያደላቸው በሀገር ጉዳይ የማይታክቱት ፕ/ር መስፍን ወልደ ማሪያም ሰሞኑን በምድረ አሜሪካ ነዋሪ ከሆኑ ኢትዮጵያውያን ጋር ያደረጉትን ውይይት ዘመነ ቴክኖሎጂ ምስጋን ይግባውና በያለንበት ሆነነን ተከታትለናል፡፡ ከውይይቱ ታዳሚዎቸች ከቀረቡ በርካታ ጥያቄዎች አንዱ በያ ትውልድ ላይ ጨከኑበት የሚል ነበር፡፡ ፕ/ር መስፍን ሲመልሱም አልጨከንኩበትም እውነቱን ነው የተናገርኩት አንዳንዶቹ እንደውም ተማሪዎቼ ነበሩና አነጋሬአቸዋለሁ፣ ፍላጎታቸው ለሀገርና ለሕዝብ ሳይሆን ሥልጣን ነበር ብለዋል፡፡
በዚሁ ሰሞን እጄ የገባው ባለ 96 ገጽ ሰነድ ውስጥ ፕ/ር የተናገሩትን የሚያረጋገጥ ከጉዳዩ ባለቤቶች አንዱ በሆነው የተነገረ አገኘሁ፡፡ ሰነዱ በእያንዳንዱ ገጽ ላይ“ በሀገርና ሕዝብ ደህንነት ጥበቃ ምኒስቴር የማዕከላዊ ምርመራ ድርጅት የወንጀል መዝገብ ቤት” የሚል ማኅተምና “ጥብቅ ምሥጢር” የሚል ማሳሰቢያ ያረፈበት ሲሆን ከኢህአፓ መሪዎች አንዱ የነበረው ብርሀነ መስቀል ረዳ በእስር ቤት የሰጠውን የምርመራ ቃል የያዘ ነው፡፡ ከአጀማመራቸው አንስቶ እስከ መንዝና መርሀ ቤት ቆይታው ይዘረዝራል፡፡

የተናገሩት ከሚጠፋ… (በኤፍሬም ማዴቦ – ከአርበኞች መንደር)

በኤፍሬም ማዴቦ
ባለፈዉ መጣጥፌ “ቃል የእምነት ዕዳ ነዉ” ብዬ ጀምሬ “ቃላችን አይለወጥ” ብዬ ነበር የተለየኋችሁ። አለምክንያት አልነበረም እንዲህ ያልኳችሁ፤ በአንድ በኩለ ቃል መከበርም መከፈልም ያለበት ዕዳ ስለሆነ በሌላ በኩል ደግሞ ቀትር ላይ የገባዉን ቃል ሳይመሽ እንደ ጴጥሮስ ሦስቴ የሚክድ ብዙ ቃላ አባይ ሰላለ ነዉ። አገሬን ከወያኔ አጸዳለሁ ብሎ ቃል የሚገባ እያንዳንዱ ኢትዮጵያዊ ዕዳ አለበት። ዕዳዉ ደግሞ ገንዘብ ወይም ንብረት አይደለም። ቃሉን መጠበቅ ወይም ቃሉን ማክበር ነዉ።Ephrem Madebo with Patriotic Ginbot 7 fighters
ደግሞም አንድ ሰዉ የተናገርዉን ቃል ሰብሮ የእምነት ባለዕዳ ከሚሆን ዕድሜ ልኩን የገንዘብ ባለዕዳ ቢሆን ይሻለዋል። የገንዘብ ዕዳ ቆይቶም ቢሆን ይከፈላል ወይም አበዳሪዉ ሊምረን ይችላል፤ የዕምነት ዕዳ ግን የማይሽር ጠባሳዉ እየቆረቆረን አብሮን ይኖራል እንጂ አይጠፋም። ማንም ሰዉ ለአገሬ ህይወቴን እሰጣለሁ ብሎ ቃል ሲገባ መሃላዉ ከህዝብና ከአገር ጋር ብቻ አይደለም፤ እንዳዉም የሰዉ ልጅ ቃል የሚገባዉ መጀመሪያ ከራሱ ጋር ነዉ። ለራሱ የገባዉን ቃል የማያከብርና ቃሌ ቃል ነዉ ብሎ የገዛ ራሱን የእምነት ዕዳ ያልከፈለ ሰዉ ለህዝብና ለአገር ቃል መግባት አይችልም።

ይቅርታ- የወያኔ ካርታ (ይገረም አለሙ)

ይገረም አለሙ
1437ኛው የኢድ አል አድኻ ( አረፋ) በአል በአዲስ አበባ ስታዲየም ሲከበር ንግግር ያደረጉት የአዲስ አበባ አስልምና ጉዳዮች ምክር ቤት ፕሬዝዳንት በሽብር ወንጀል ተከሰው ከተፈረደባቸው የሙስሊሙ ማህበረሰብ ችግሮች መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴ አባላት መካከል ስድስቱ በቅርቡ የተለቀቁት በእነርሱ ጥያቄና ጥረት አንደሆነ፤ ጥያቄአቸው ምላሽ በማግኘቱና ጥረታቸው በመሳካቱ መደሰታቸውን ገልጸው ለመንግሥት ምሥጋና ማቅረባቸውን የጀርመን ድምጽ ራዲዮ ዘጋቢ ከስፍራው ባስተላላፈው ዘገባ አሰምጾናል፡፡ ወያኔ ግዜና ወቅት እየጠበቀ የሚጠቀምባት የፖለቲካ ቁማር መጫወቻ የይቅርታ ካርድ በሌላ መንገድና መልክ ተመዘዘች ማለት ነው፡፡

ሁለት የሶማሌ የጦር አውሮፕላኖችን መተው የጣሉት የቀድሞ አየር ኃይል ጀግና አረፉ

የኮለኔል ባጫ ሁንዴ የህይወት ታሪክ

ኮለኔል ባጫ ሁንዴ በአንቦ አካባቢ በጊንጪ ከተማ ተወለዱ ።በአምቦ ከፍተኛ ሁለተኛ ደረጃ ትምህርታቸውን እንዳጠናቀቁ በ1965 እንደ አውሮፓውያን አቆጣጠር በኢትዮጵያ አየር ሃይል በአውሮፕላን ጥገና አገራቸውን ለማገልገል ተቀጥረው ስልጠናቸውን እንደጨረሱ ከክፍላቸው ያመጡት ውጤት የላቀ በመሆኑ እና የተዋጊ አውሮፕላን በራሪ ለመሆን ባሳዩት ከፍተኛ ፍላጎት ሙያው የሚጠይቀውን ማንኛውንም መስፈርት በማሟላት ወደ በረራ ትምህርት ቤት ገቡ።Colonel Bacha Debele
የሚፈለግባቸውን የበረራ ትምህርት እንደጨረሱ ወደ ተዋጊ ስኳድሮን በመመደብ የኤፍ 86 አውሮፕላን ሲበሩ ቆይተው የኢትዮጵያ አየር ሃይል F-5E የሚባል አዲስ አውሮፕላን ሲገዛ ወደ አሜሪካን አገር ተልከው በዚሁ አውሮፕላን ስልጠና በመውሰድ እና በማጠናቀቅ ወደ አገራቸው ተመልሰው በወቅቱ አገራችንን የወረሩትን የሱማሌ ወራሪዎች ጋር ፍልሚያ ውስጥ በመግባት በአየር ላይ ውጊያ ሁለት የሱማሌ ሚግ አውሮፕላኖችን መትተው የጣሉ ሲሆን በዚህም ላሳዩት ከፍተኛ ጀግንነት ከኢትዮጵያ መንግስት የጦር ሜዳ የላቀ ጀግንነት ሜዳይ ተሸላሚ ሆነዋል።

“የየጁ ደብተራ ቅኔው ሲጎልበት ቀረርቶ ሞላበት” (ስሜነህ ባዘዘው)

ስሜነህ ባዘዘው
በሻቢያ እርዳታ የሚደረግ ትግል በአፍንጫዬ ይውጣ የሚሉ ወገኖች ሃሳባቸውን በተለያየ መልክ ሲገልጹ ቆይተዋል፤ አብዛኞች የአመለካከት ልዩነታቸውን በሰለጠነ መልክ “በልዩነት” ይዘው የራሳቸውን ስራ እየሰሩ ነው። ይህ ደግሞ የብስለት ምልክት ነው።

ኑሮ በመፈክር (ጌቱ ኃይሉ)

ጌቱ ኃይሉ
አቶ ዠ 57 አመታቸው ነው። መተዳደሪያ አላቸው። እንዴት ያለ ሙያ!! ባሥራ ሰባት አመታቸው የጀመሩት። አርባ አመት ሙሉ ያለማቋረጥ እየሰሩ ያሉት። ሰዉ ከሥራው በመንግሥት ለውጥ፣ በሰበብ ባስባቡ ሲባረር እሳቸው ሥራ አላጡም። ሥራቸው? መፈክር አድምቆ መጻፍ።
መጀመሪያ በሁለት ቃላት ጀመሩ። በነጻ “ኢትዮጵያ ትቅደም!” ብለው አድምቀው ጻፉ። ከዚያ እየተከፈላቸው ደግሞ “ከቆራጡ መሪ ጋር ወደፊት !!” ብለው ቀጠሉ። ሰውየው ብቻቸውን ሲቀሩ። ወደ መጨረሻው ግድም ደግሞ “አብዮታዊት እናት ሃገር ወይም ሞት” ብለው ደጋግመው አድምቀው ጻፉ። “አብዮታዊት እናት ሃገር ወይም ዝምባብዌ!” ብለው አላፌዙም።

ለየት ባለመንገድ ደፈር ብሎ ስለማሰብ፣ ጉርብትናና በሰላም መኖር፣ በየኢትዮጵያና ኤርትራ መካከል

ከቢላል አበጋዝ – ዋሽግቶን ዲሲ
ዛሬ ካለንበት ተነስተን ስናስብ ወያኔ ህወሃት ጋር ያለን ጠብ ሳይሆን ከወያኔ በኋላ በምን ሁኔታ የምትኖር አገርን እንሻለን የሚለው ጥያቄ ግዝፈት አለው።በኢትዮጵያም በኤርትራም ያለው ህዝብ ከወያኔም፤ከሻቢያም በላይ ነው።ያአንድ አገር እድል ከፖለቲካ ድርጅቶች ፤ከመሪዎችም በላይ ነው።የአካባቢውን ህዝቦች እጣ ፈንታ ስናስብ በወሰን ተገድበን እንዳይሆን ጥንታዊና በዙ መእዘን ያለው ትስስራችን አስበን ከስሜተኝነት ርቀን እንደ ችግር ፈችዎች እንድናስብ የግድ ይለናል። የኢትዮጵያና ኤርትራ ጉዳይ እንድንወያይበት በሚል ይህ ጽሁፍ ቀርቧል።

አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን ለአዲስ አመት ዋዜማ በላፍቶ ሊያዘጋጀው የነበረው ኮንሰርት በመሰረዙ

መስከረም ፲፯ (አስራ ሰባት) ቀን ፳፻፰ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-አርቲስት ቴዎድሮስ ካሳሁን ለአዲስ አመት ዋዜማ በላፍቶ ሊያዘጋጀው የነበረው ኮንሰርት በመሰረዙ በአድናቂዎቹ ዘንድ የፈጠረው ቅሬታ ሳይረሳ ፣ አሁን ደግሞ ለመስቀል በአል ያዘጋጀው ኮንሰርት በድጋሚ በአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር እንዳይካሄድ መከልከሉን የፎርቺን ሳምንታዊ ጋዜጣ ዘገባ ያመለክታል። የአዲስ አበባ መስተዳድር የካቢኔ ጉዳዮች ዳይሬክቶሬት አቶ ፈለቀ ነጋሽ የ አዲስ አመት ኮንሰርቱ የተሰረዘው በአስተባባሪዎቹ የፈቃድ ጥያቄ የቀረበው በአጭር ጊዜ ውስጥ ከመሆኑ አኳያ አስተዳደሩ ባጋጠመው የስራ መደራረብ ሳቢያ እንደሆነ ለጋዜጣው መግለጻቸው ይታወሳል፡፡

በኢትዮጵያ ታሪክ ጉዳይ ላይ ኢሕአዴግን እንዴት ማመን ይቻላል?! በዲ/ን ኒቆዲሞስ

ወንድማችን ዲ/ን ዳንኤል የኢትዮጵያችን ልዩ ቅርስ በኾነው የዘመን አቆጣጠራችንን በተመለከተ አንድ ጥያቄ አንስቶአል፡፡ ይኸውም የኢትዮጵያን የዘመን አቆጣጠር በተመለከተ ‹‹ጠቅላይ ሚ/ሩን እንመን ወይስ አርቲስቶቻችንን?!›› የሚል ጥያቄ አንስቶ አንድ ትዝብትና ማሳሰቢያ አከል ጽሑፍ አስነብቦናል፡፡ እኔ ግን እንዲህ እላለሁ በኢትዮጵያ የዘመን አቆጣጠርም ሆነ በአጠቃላይ በኢትዮጵያ ታሪክ ጉዳይ ላይ ኢሕዴግን/ክቡር ጠቅላይ ሚ/ሩን እንዳናምናቸው የሚያደርጉን አንዳንድ የታሪክ ሐቆች እንዳሉ ላንሣ፡፡
እስቲ እነዚህን ሐቆች በጥቂቱ ብቻ ለማየት እንሞከር፡፡ በመሠረቱ የአገሪቱን ታሪክ ወደ መቶ ዓመት አውርዶ ለሚተነትነው፣ ጥንታዊው የሆነው ፊደላችን፣ ሦስት ሺሕ ዘመንን ያስቆጠረውን የሥነ-መንግሥት ታሪክ ‹‹የአቢሲኒያውያን/የነፍጠኞች ቅኝ ገዢዎች ታሪክ›› አድርጎ የኢትዮጵያን ሕዝቦች ታሪክ በብሔር ብሔረሰቦች ማዕቀፍ ቀንብቦ ዳግም ለመፍጠር ለሚውተረተረው፤ አቶ ኃይለ ማርያም ደሳለኝ የሚመሩት የኢሕአዴግ መንግሥት በምን ሞራልና ተጠየቅ፡- ‹‹ከአፍሪካ አገራት ሺሕ ዘመናትን ያስቆጠረ የራሳችን ፊደልና የዘመን አቆጣጠር ያለን ኩሩ ሕዝቦች …፡፡›› ተብሎ በአደባባይ ሊነግሩን እንደደፈሩ አይገባኝም፡፡ የታሪክ እውነት/ሐቅ ሲያሻን የምንደርበው እንዲያ ሲል ደግሞ አውልቀንና አሽቀንጥረን የምንጥለው የበረሃ ሽርጥ ኾነ እንዴ ጎበዝ …?! ይሄ በእውነት ያስተዛዝባል፡፡ ወይስ ደግሞ እንደው ሳንሰማ ኢሕአዴግ በኢትዮጵያ ታሪክ ላይ ያለውን አቋም አስተካክሎ ይሆን እንዴ … እ…እ…እ… አይመስለኝም፡፡

አቶ ሞላ ለምን ደነበረ? ታሪኩ አባዳማ

ጄነራል ከማል ገልቹ ከበርካታ ወታደሮች ጋር ድንበር ጥሶ ወደ ኤርትራ ገባ ሲባል ሰማን። በዚህ የተነሳ የወያኔ ሰራዊት ለይቶለት የተናደ መስሎን በማግስቱ አንዳች የፖሊቲካ ለውጥ ለማየት የጓጓን ልንኖር እንችላለን – ጄት እና ስልታዊ የውትድርና ተዋጊ ሄሊኮፕተር ይዘው ወያኔን የከዱ መኮንኖች ዜና ሲሰማ አሁንም የድል ቀን ተቃረበ ብለን በቅንነት ደስታ የወረረን አንጠፋም።
በተቃራኒው ደግሞ አቶ ሞላ አስገዶም የደሚህት መሪ እጁን ለወያኔ ሰጠ ሲባል ትግሉ ተኮላሸ ብለን የደነገጥንም አንጠፋም …
በመሰረቱ ከነኝህ መልካም ሆነ ክፉ አጋጣሚዎች ልንማር የሚገባን ነገር ቢኖር የነፃነት ድል ባንድ ወይንም በሁለት ያልተጠበቁ ድንገተኛ ያቋም ለውጦች የሚጨበጥ ወይንም የሚዳከም ጉዳይ አለመሆኑን ብቻ ነው። እያንዳንዱ አጋጣሚ ግን ለትግሉ የይዘት ሳይሆን የአይነት ለውጥ በማከል ያጠናክረዋል። የህዝባዊ ትግል ድል አዝጋሚ ግን የማይቀር መሆኑን ጭምር አብሮ መቀበል ያሻል።

ሁለት የአሜሪካ ከፍተኛ የጦር አማካሪዎች ኤርትራ ገቡ።

በ 1960 ዎቹ አመተ ምህረት አካባቢ ወደ ቬትናም ሄዶ ሲያሰለጥን የነበረዉ የአሜሪካዉ ምርጥ እንዲሁም ኤኮ 31 በመባል የሚታወቀዉ ሐይል U.S. Army Special Forces and Echo 31 ኤርትራ መግባታቸዉ ታዉቋል በትናንትናዉ እለት ከኤርትራ ከፍተኛ ባለስልጣናትና ተቀማጭነታቸዉ በኤርትራ በሆኑ የኢትዮጵያ ተቃዋሚዎች ጋር በተለይም ከርበኞች ግንቦት 7 አመራሮች ጋ መክሯል የተባለዉ ይህዉ ቡድን አመጣጡ ተቃዋሚዎችን ለመርዳት ነዉ ሲሉ ምንጮቻችን ገልጸዋል።

Monday, September 14, 2015

የተደበቀው የህወሓት ማንነት ከደደቢት እስከ ቤተመንግስት – ክፍል 2 “ሳሞራ የኑስ በበረሃ በርካታ የህወሓት ታጋይ ሴቶችን ድፍሯል”


የተደበቀው የህወሓት ማንነት ከደደቢት እስከ ቤተመንግስት –  “ሳሞራ የኑስ በበረሃ በርካታ የህወሓት ታጋይ ሴቶችን ድፍሯል” (ክፍል 2)

መለስ ዜናዊ፣ ስብሀት ነጋ፣ ስዬ አብርሃ፣ ስዩም መስፍን፣ አባይ ፀሀዬ፣ ገብሩ አስራት፣ አለምሰገድ ገ/አምላክ፣ አውዓሎም ወልዱ፣ አረጋሽ አዳነ፣ አርከበ ዕቁባይ፣ ፃድቃን ገ/ተንሳይ፣ አበበ ተ/ኃይማኖት እና ክንፈ ገ/መደህን ለረጅም ጊዜ መቀሌ ላይ በመዶለት በኢትዮጵያና ህዝቦቿ ላይ አሲረው የበቀል፣ የዘረፋ፣ የመከፋፈል እና የረጅም ጊዜ የአፈና ስርዐት እቅድ ነድፈው ሰራዊታቸውን በባሌ ልከው እነሱ በቦሌ አዲስ አበባ ገቡ፡፡
TPLF 2
በአንድ ጃቸው መቀሌ ውስጥ ተጠፍጥፎ ተሰርቶ የተሳለ የበቀል ሰይፍ በሌላኛው እጃቸው የዘረኝነት ረጅም ዘንግ ጨብጠው አዲስ አበባ የገቡት የባንዳ ልጆች ስብስብ ሳይውሉ ሳያድሩ የጥፋት ተልዕኳአቸውን ዕቅድ አንድባንድ መተግበር ጀመሩ፡፡
የጥፋት ቡድኑ መሪ መለስ ዜናዊ “ከእናንተ ወርቅ ከሆናችሁት የትግራይ ህዝብ በመፈጠሬ እኳራለሁ፤ እንኳን ከእናንተ ተገኘን፤ እንኳን ይሄ ህዝብ የሌላ አልሆነ፤ እንኳን በሩቅ እያየን የምንቀናባችሁ አልሆናችሁ…” በማለት በአደባባይ ተናግሮ እሱም እንዳያቶቹ ኢትዮጵያዊነቱን ሽምጥጥ አድርጎ ካደ፡፡

የናትናኤል ፈለቀ ማስታወሻ – ጥቂት ስለ ማዕከላዊ (ከቂሊንጦ እስር ቤት)


ይህንን ጽሁፍ ስጽፍ ዓላማዬ ማዕከላዊ ያሉ ሥራቸውን አክብረው የኢትዮጵያውያንን ሰላምና ደህንነት ለመጠበቅ የሚሰሩ ጥቂት ፖሊሶችን (ምናልባትም በአንድ እጅ ጣቶች ተቆጥረው የሚያልቁ መርማሪዎችን) ለማበረታታት አይደለም፡፡ ይህን ዓላማ በሌላ ጽሁፍ እመለስበት ይሆናል፡፡ ለነገሩ ሥራቸውን አክብረው የሚሰሩ ባለሙያ ፖሊሶች የኔ ማበረታታትን የሚፈልጉ አይደሉም፡፡ ያሉበት ደረጃ ላይ ለመድረስ በኃላፊነት ማሰብ የቻሉ ስለሆኑ፡፡
Nathaniel-Feleke-with-Kerry-625x370
ስለዚህ የዚህ ጽሁፍ ዓላማ በተቋሙ ውስጥ ኢትዮጵያ የምትተዳደርባቸውን ሕጎች ለማክበር (የተላለፉትን ለይቶ ለማስቀመጥና በስህተት የተጠረጠሩትን ነጻ ለማውጣት) ሳይሆን የአገዛዙን ዕድሜ ለማርዘም የሚሰሩትን አብዛኞቹን ሙያቸውን የማያከብሩ ፖሊሶች ‹‹ምርመራ›› ሴራቸውን እንዴት እንደሚፈትሉ ለማሳየት፣ ቢያንስ ሌላ ስልት እስኪፈጥሩ ድረስ በሀገሪቷ ጉዳይ ያገባናል የሚሉ ኢትዮጵያውያን አንዴ በተቋሙ ውስጥ ከገቡ በኋላ ሊገጥማቸው የሚችለውን የተንኮል መረብ ለማስረዳት እና ቀድሞ ለማዘጋጀት ያሰበ ነው፡፡

ሰበር ዜና፡ ታጋይ ዘመነ የግንቦት 7 ህዝባዊ ሃይል አመራር ከአባይ ሚደያ ጋር አጭር ቆይታ አደረገ

ሰበር ዜና፡ ታጋይ ዘመነ የግንቦት 7 ህዝባዊ ሃይል አመራር ከአባይ ሚደያ ጋር አጭር ቆይታ አደረገ።

አባይ ሚዲያ ከግንቦት 7 ህዝባዊ ሃይል የፖለቲካ ሃላፊ ከሆነው ታጋይ ዘመነ ካሴ ጋር የስልክ ውይይት አደረገ። ታጋይ ዘመነ ለአባይ ሚዲያ ሲናገሩ አቶ ኤልያስ ጋዜጠኛ ስለመሆኑም እና እንዴት እና በምን ሂሳብ ወደ ትግል አለም እንደገባም እንደማያውቁ ተናግረዋል።
ወጣቱ ታጋይ ዘመነ ለኢትዮጵያ ህዝብ ባስተላለፈው መልእክት አዲሱ አመት የሰላም እና የድል ዘመን እንዲሆን በመመኘት እና ወንድማችን ታጋይ አንዳርጋቸውን የከፈለውን መሰዋእትነት ከንቱ እንዳይሆን ህዝባዊ ሃይሉ እና ከሌሎች የነጻነት ሃይሎች ጋር እየተደረገ ያለው ሂደት መፋጠኑን በዚህ አመት የምናወራበት ሳይሆን ወደ ትጋበር ተሸጋግረን ወያኔን የምናበረክክበት ዘመን እንደሚሆን አትጠራጠሩ ሲል መልእክቱን አስተላልፉል።

አስመራ ተጉዘው የነበሩት ሁለቱ የኢሳት ጋዜጠኞች ስለ ሞላ አስገዶም መክዳት ምን አሉ?

በአዲስ ዓመት ዋዜማ ኢሳት ያሰማው ሰበር ዜና አነጋጋሪ ሆኗል:: ውህደት ተፈጸመ የሚለው ዜና 3 ሌሊት ሳያልፍ ይህ ዜና ብዙዎችን እያነጋገረ ነው:: ስለታጋይ ሞላ አስገዶም አስመራ ሄደው አግኝተውት የነበሩት ሁለቱ የኢሳት ጋዜጠኞች ፋሲል የኔዓለም እና መሳይ መኮንን ምን ይላሉ? ያንብቡት:: ፋሲል የኔዓለም ስለ ሞላ አስገዶም:- የደሚህቱ ሞላ አስገዶም መክዳቱን ስሰማ በእጅጉ ተገርሜአለሁ። ከቀናት በፊት ሞላ ፣ ሰው አክባሪ፣ ተግባቢና አገሩን የሚወድ ሰው መሆኑን ጽፌ ነበር። ኤርትራ በነበርኩበት ጊዜ ደጋግሜ አግኝቸዋለሁ ፣ በተለያዩ ጉዳዮች ላይ ሰፊ ጊዜ ወስደን ተነጋግረናል። እስከዛሬዋ ቀን ድረስ ስለሞላ የነበረኝ አመለካከት ቀደም ብዬ የገለጽኩት ነው። ስለእውነት እመሰክራለሁ፣ ኤርትራ በነበርኩበት ወቅት አንድም ቀን በሰላይነት እንድጠረጥረው ወይም በወያኔነት እንድፈርጀው የሚያደርግ ነገር አላነበብኩም። ከህወሃት ጋር የሚጋራቸው አቋሞች ቢኖሩም፣ በኢትዮጵያ አንድነት ላይ የማይናወጽ አቋም እንዳለው፣ ህወሃት ኢትዮጵያን ታሪክ አልባ በማድረጉ በጣም እንደሚያዝን ነግሮኛል። ከእርሱ ጋር የተግባባንበት የመጨረሻው ነጥብም ይህ ነበር- ህወሃት ኢትዮጵያን ከመበታተኑ በፊት እንድረስላት።

Wednesday, September 9, 2015

የፖለቲካ ለዉጥ ያስፈልገናል

ወያኔ ለኢትዮጵያ ህዝብ ያስተማረዉ ነገር ቢኖር ዘረኝነትን፡ሌብነትን፡ሙስናን፡ዉሸትን፡መስሎ መኖርን ወይም አድርባይነትንና ራስ ወዳድነትን ነዉ።ኢትዮጵያን አሁን ላይ እየመሯት ያሉት ከአብራኳ የወጡ ምሁራን ሳይሆኑ ከጫካ የመጡ ስለሀገርና ህዝብ ግድ የሌላቸው አውሬዎችና ፍርፋሪ ያጠገባቸዉ ካድሬዎች ናቸዉ፤የኢትዮጵያ የፖለቲካ ሲስተም ተበላሽቷል፤አሁን ላይ ኢትዮጵያ የትግራይ ህዝብና አሽቃባጭ ካድሬ የሚስቅባትና የሚፈነጭባት ነገር ግን ሰፊዉ የኢትዮጵያ ህዝብ ቀንና ማታ የሚያለቅስባት ለቅሶውን የሚያደምጥ መንግስት የሌለባት አገር ነች፤አሁን ላይ ኢትዮጵያ ማለት ደደብ የወያኔ ካድሬ የሚፈነጭባትና እንደፈለገ የሚያዝባት ነገር ግን ምሁር የማይከበርባትና የሚሰደድባት አገር ነች፤በምሁራን ፍልሰት ኢትዮጵያ ቀዳሚ አገር ሆናለች፤አሁን ላይ በኢትዮጵያ የትምህርት ጥራት ወድቋል፤የትምህርት ተቋሞች እየተመሩ ያሉት በምሁር ሳይሆን ለፖለቲካ ታማኝ በሆኑ ሰዎች ነዉ፤በየዓመቱ በመቶ ሺዎች የሚቆጠሩ ተማሪዎች ከዩኒቨርስቲ ተመርቀው ሲወጡ ጥሩ ስራ ማግኘት አይችሉም፣አሽቃባጭ ካድሬ ወይም ትግሬ ካልሆነ በስተቀር ሰርቶ መቀየር አስቸጋሪ ነዉ።

የአገራችን እውነተኛ ባለቤቶች ለመሆን ከምናደርገው ትግል ጎን ለጎን

የአገራችን እውነተኛ ባለቤቶች ለመሆን ከምናደርገው ትግል ጎን ለጎን፣ በስደት በምንኖርበት አገር ሁሉ ከሚደርስብን ጥቃት ራሳችንን ለመከላከል እጅ ለእጅ ተያይዘን መታገል ይኖርብናል። በደቡብ አፍሪካ የሚታየው አስቀያሚ ሁኔታ በሌሎች አገሮችም ሊከሰት እንደሚችል ልብ ልንል ይገባል። በተለይ የኢኮኖሚ ቀውስ በሚያጋጥምበት ወቅት ስደተኞች ሁሌም ኢላማ መሆናቸው አይቀርም። በስደት የሚገኙ ኢትዮጵያን ለህልውናቸው ሲሉ በየአካባቢያቸው እንዲሁም በአለም አቀፍ ደረጃ የሚሟገት ጠንካራ ማህበራትን መመስረት አለባቸው።

Somalia

"Somalia was once seen as a failed state, suffering from violence and lack of governance. But now hundreds of Ethiopians are moving to Somalia in search of a better life - although Somalia is a much poorer country. 
And while many of these migrants help boost the local economy, they face xenophobia and hostility from some locals who want to see them deported.

ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ የመስዋትነቱን ጣሪያ ከፍ አድርጎ ሰቀለው።

ፕ/ር ብርሃኑ ነጋ የመስዋትነቱን ጣሪያ ከፍ አድርጎ ሰቀለው። ለአገር፣ ለፍትህ ፣ ለነጻነት፣ ለዲሞክራሲና ለሰብዓዊ መብት መስዋት መሆን ማለት እስከምን እንደሚደርስ አሳየን። ፕሮፌሰሩ ጣሪያውን ከፍ አድርጎ ቢሰቅለውም፣ እኛም ከቻልን እንደሱ ከጣሪያው ላይ ለመውጣት፣ ካልቻልን ደግሞ ከቆምንበት ውሃ ልክ ላይ ላለመውረድ እንጠንቀቅ፤ ከውሃ ልኩ የወረደም፣ ከወለሉ በታች ላለመቀበር ይጣር።

በፍትህ እንዲህ የተቀለደበት ዘመን ይኖር ይሆን?

ወንድሞቼ ዳንኤል፣ አብርሃም፣ የሽዋስና ሃብታሙ ይፈታሉ በመባሉ በጣም ደስ ብሎኛል። በመፈታታቸው ደስ እየተሰኝን የአገዛዙን ፖለቲካዊ ጨዋታ ማየቱም አይከፋም። ከዚህ ቀድም እንዳልኩት ነው፤ አገዛዙ እድሜውን የሚያራዝመው በሰላማዊ ትግል እና በትጥቅ ትግል መካከል ያለውን የሃሳብ ልዩነት በማራገብ ነው። ሰላማዊ ትግልን የሚያቀነቅኑ ሃይሎች እየጠነከሩ ሲመጡ፣ የትግሉን መሪዎች ያስርና ህዝቡ "ሰላማዊ ትግል አያዋጣንም" ብሎ ወደ ትጥቅ ትግል ፊቱን እንዲያዞር አድርጎ አደጋውን ይቀንሰዋል። የህዝቡ ትኩረት ወደ ትጥቅ ትግል ሲዞር ደግሞ፣ የታሰሩ ሰላማዊ ታጋዮችን ይፈታና የፖለቲካ ምህዳሩንም ትንሽ ከፈት አድርጎ " አዲስ የተስፋ ዳቦ" ይሰቅላል ። ህዝቡም እንደገና በሰላማዊ ትግል ተስፋ ያደርግና ትጥቅ ትግሉን ለመቀላቀል ልቡ ያመነታል- የታጋዩን ልብ እየከፋፈሉ የመግዛት ፖለቲካ ። የእነ አብርሃን መፈታት "ሃሳብን ከፋፍሎ በመግዛት የፖለቲካ ስልት " ካየነው ስሜት ይሰጣል።

መልካም የድል ዓመት።

አራቱ ንቅናቄዎች በዚህ ፍጥነት የጋራ ድርጅት ይመሰርታሉ ብዬ አላሰብኩም ነበር። ሁሉም የድርጅት አመራሮች ምስጋና ይገባቸዋል፤ ፕ/ር ብርሃኑ ትግሉ ስርዓት ይዞ በጥሩ አቅጣጫ እንዲጓዝ እያደረገው እንደሆነ በመስማቴ እንደ ወትሮው ኮርቸበታለሁ። የደሚት መሪ ሞላ አሰግዶም ትሁት፣ ሰው አክባሪ፣ ተግባቢና አገሩን በጣም የሚወድ ሰው ነው። መአዛው ጊጡም እንዲሁ ደግ፣ቅን፣ ሰው አክባሪና አገሩን የሚወድ ሰው ነው። የአማራን ድርጅት መሪ በአካል አላገኘሁትም፣ ምክትሉንና ጸሃፊውን አነጋግሪያቸዋለሁ፤ በተለይ ጸሃፊውን በቅርበት አውቀዋለሁ፣ ገና ትግሉን በረሃ ወርዶ ሳይቀላቀል በአገር ቤት ብዙ ታሪክ የሰራና መስዋትነት የከፈለ ወጣት ነው። የአፋሩ ኢብራሂም ሙሳም ሆነ ዶ/ር ኮንቴ አገራቸውን የሚወዱ አሪፍ መሪዎች ናቸው። በሁሉም ድርጅቶች ውስጥ፣ በጣም ብዙ አገር ወዳድ ታጋዮች አሉ፤ አዲሱ ድርጅት የእነዚህ ታጋዮች ሁሉ ውጤት ነውና እነሱም ክብር ይገባቸዋል።

አይ ኦነግ አላማ የሌለው

አይ ኦነግ አላማ የሌለው ስብስብ አንዳንድ ጊዜ ለምን ኦነግ 3 ሆነ ብዬ እራሴን ጠይቅና እናም ለራሴ ስመልስ እንወክለዋለን ወይም ነፃ እናወጣዋለን የሚሉትን የኦሮሞን እዝብ ስለማያውቁት ወይም እዝቡ አንቅሮ ስለተፋቸው/Rejected by the peoples / ይመስለኝና።
** ግን ለምን እዝቡ አንቅሮ ተፋቸው ስልና ምክንያቴን ሳስቀምጥ በእርግጥ የኦነግ መሪዎች ለስልጣን እንጂ ለእዝቡ ነፃነት ግድ እ
ንደሌላቸው እዝቡ ስላወቀ ነው የኦሮሞ እዝብ ስነ ልቦና ከቀሪው እዝብ ስነ ልቦና የሚለይ አይመስለኝም በዚህ የወያኔ 25 ክፉ አመታትን አብረን ኖረናል ይህ ለአንድነታችን ምስክር ነው ከዚህም በኋላ አብረን እንኖራለን።

አንዳንድ የኦሮሞ የፌስ ቡክ "አክቲቪስቶች"

አንዳንድ የኦሮሞ የፌስ ቡክ "አክቲቪስቶች" ግንቦት7 ኦነግን አፈረሰው እያሉ አዲስ ታሪክ መጻፍ ጀምረዋል። እነዚህ ሰዎች ግንቦት7ትን ሲወነጅሉ ኦነግን እያሳነሱት መሆኑ አልገባቸውም። እስኪ እግዜር ያሳያችሁ፣ የ40 ዓመቱን ጎልማሳ ድርጅት የ7 አመቱ ግንቦት 7 አፈረሰው ሲባል፣ ድክመቱ የማን ነው? አንድ የ40 ዓመት ጎልማሳን የ7 ዓመት ልጅ ደብድቦ ቢጥለው ፣ ሰውዬው 40 ዓመት ሙሉ ምን ይሰራ ነበር? ግንቦት7 ኦነግን አፍርሶት ከሆነ፣ ኦነግ ከመጀመሪያውም ድርጅት አልነበረም ማለት ነው፤ እንዲህ በቀላሉ የሚበታተን ድርጅት ከሆነም ኦነግ በስም እንጅ በገሃዱ ዓለም ያልነበረ ድርጅት ነበር ማለት ነው።

የአርበኞች ግንቦት 7 ለአንድነትና ዴሞክራሲ ንቅናቄ የውስጥ አርበኞች በህወሓት አገዛዝ መከላከያ ሰራዊት ላይ ጥቃት በመሰንዘር ለአንድ ሰዓት የዘለቀ ከባድ ውጊያ አድርገው ከፍተኛ ጉዳት አደረሱ፡፡

asee
የአርበኞች ግንቦት 7 የውስጥ አርበኞች ህወሓት “ክልል አንድ” እያለ በሚጠራው በጎንደር-ወልቃይት ደጃች ሜዳ ወረዳ አቤራ ቀበሌ ስልኪ ዳግባ በተባለው ቦታ ነሃሴ 23 2007 ዓ.ም በህወሓት መከላከያ ኃይል ላይ ድንገተኛ የተኩስ ውርጅብኝ በመክፈት ቁጥራቸው ቀላል የማይባሉ ወታደሮችን ገድለውና አቁስለው ድል ተቀዳጅተዋል፡፡

ህወኃት ፀገዴ ላይ ያካሄደው ስብሰባ ከሸፈ፣

የትግራይ ነፃነት ግንባር /ህወኃት/ ገና ከፅንስሱ ሲነሳ ለሙን የሰሜን ወሎን፣ ምዕራባዊ ጎንደርን እና ምዕራባዊ ጎጃምን በማካተት ታላቁን የትግራይ ሪፐብሊክ መመስረትግብ አድርጎ መመስረቱና ለዚህም አላማው ስኬት የቻለውን ሁሉ በማድረግ ላይ እንድሚገኝ የሚታወቅ ነገር ነው።
በተለይም በወልቃይት፣ ፀገዴና አርማጭሆ ያካሄደው መስፋፍት በአካባቢው ነዋሪ ህዝብ ላይ ትውልድ ይቅር የማይለው ግፍ ፈጽሟል፡ አሁንም የመስፋፋት ህልሙን እውን ለማድረግና ቀሪ የአማራን መሬት ለመቆጣጠር ያለማቁአረጥ ጥረት እያደረገ ነው። ከላይ በተጠቀሱት አካባቢወች የሚኖረውን የአማራን ህዝብ በማንበርከክ እኩይ ፍላጎቱን ለማስፈፀም ቀደም ሲል የጎንደር አስተዳደር ከተሞች በነበሩና አሁን በጉልበት ወደ ትግራይ በተወሰዱ ሁመራ፣ ማይካድራ፣ ማይፀብሬ፡ ዳንሻ፣ ማክሰኞ ገበያ/ ንጉስ ከተማ/ና ዲቪዥን የተባሉ ከተሞችን ማዕከል በማድረግ በአካባቢው የሚኖሩ የትግራይ ተወላጆችን በተለይም ምልስ የህወኃት ወታደሮችን በመመልመል ከሃምሌ 2006 እስከ መስከረም 2007 ለሶስት ወር የዘለቀ በሁመራ ከተማ ለ120 ሰወች ልዩ የስለላና የአፈና ስልጠና የተሰጣቸው ሲሆን በፀለምት ዲቪዥን ከተማና በዳንሻ ከተማ በያንዳንዳቸው 1500 የሰው ሃይል ለፀጥታ ስራ በሚሊሻነት አሰልጥኗል።

“ወንድ ከወንድ፣ሴት ከሴት ጋር አላጋባም” ያሉ የህግ ሹም ወደ እስር ቤት ተወረወሩ

አንዳንዴ የዚህች አማሪካን ‘ገደብ የለሽ ‘ የሰብአዊ መብቶች ጎተራነቷን ለተመለከተ መገረሙ እና መበረገጉ አይቀረም። ለምሳሌ ንብረቴን፣ቤተሰቤን እና እራሴን እጠብቃለሁ ያለ አሜሪካዊ የጦር መሳሪያ ለመታጠቅ እንደ እኛ አገር የግድ የፓርቲ ሰው አሊያም የድሮ አብዮት ጠባቂ(ሰላም እና መረጋጋት አባል) መሆን የለበትም ።ከአቅራቢያው መደብር ጎራ ብሎ ከቀላል እስከ አውቶማቲክ የጦር መሳሪያ በቀላሉ መግዛት ይችላል። የጦር መሳሪያ ነገር ከተነሳ ዘንዳ አብዛኞቹ ፖሊሶቿ ተጠረጣሪን አድኖ ከመያዘ “አልሞ መተኮስ “ይቀደማቸዋል ይባላል።

የዞን9 ጦማርያን ጉዳይ በድጋሚ ለመስከረም 27 ተቀጠረ።

በነሶልያና ሽመልስ የክስ መዝገብ ለዛሬ በተደጋጋሚ የተላለፈው የብይን ጥበቃ በድጋሚ ዳኞች አልተሟሉም በሚል ሰበብ ለ37ተኛ ጊዜ ተቀጥሯል።
በዳኞች አለመሟላት የተነሳ ችሎቱን ማስቻል አልችልም ብለው በቢሮ ተከሳሾችን እና ጠበቆችን የጠሩት ዳኛ ዘሪሁን ብይኑ ቢሰራም ለማሳወቅ ሁሉም ዳኞች መገኘት ስላለባቸው ለመስከረም 27 ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥተናል ብለዋል ።
ተለዋጭ ቀጠሮ ተከሳሾችን ቤተሰቦችን እና ውሳኔውን ሲጠብቁ የነበሩ ብዙ አጋሮችን በከፍተኛ ደረጃ ያስከፋ ነበር ።

የኢትዮጵያ አገር አድን በዴሞክራሲ የጋራ ንቅናቄ ምስረታ በማስምልከት የወጣ ድርጅታዊ መግለጫ

editorial of alliance
የኢትዮጵያ ህዝብ የኣገሩን ሉዓላዊነትና ኣንድነት ኣስከብሮ የኖረ ብቻ ሳይሆን ኣፍሪካውያን ወንድሞቹና እህቶቹ ከቀኝ ኣገዛዝ ነፃ እንዲወጡ የራሱ ኣስተዋፅኦ ያደረገ ጀግና ህዝብ ነው። ሆኖም ይህ ጀግና ህዝብ ከኣብራኩ በወጡ ገዢዎች ነፃነቱ ተገፎ፤ መብቶቹ ተረግጠው የመከራ ኑሮ እየገፋ ኣያሌ ዘመናት ኖZል። ይህ የመከራና የሰቆቃ ኑሮ ዛሬም ኣላበቃም፤ እንዲያውም “ከጭቆና ነፃ ኣወጣንህ” እያሉ የሚሳለቁበት ግፈኛ ገዢዎች የጫኑበት የስቃይ ቀንበር ተሸክሞ የውርደት ኑሮ እየኖረ ነው።

የትግራይ ነጻ አውጭ ድርጅት /ህወሃት በተለየ ሁኔታ በኤርትራ ላይ ዛቻ እያሰማ ነው።

-ኤኤፍፒ የአገሪቱን የውጭ ጉዳይ መስሪያ ቤት በመጥቀስ እንደዘገበው፣ የኢህአዴግ መንግስት በኤርትራ ላይ የሚያሰማው የጦርነት ዛቻና አገሪቱን እወራለሁ እያለ የሚያሰማው መግለጫ ጨምሯል። የትግራይ ነጻ አውጭ ድርጅት /ህወሃት በተለየ ሁኔታ በኤርትራ ላይ ዛቻ እያሰማ ነው።
በክረምቱ ወር ይሰማ የነበረው ፉከራ ባለፉት ጥቂት ሳምንታት ተጠናክሮ መቀጠሉን የማስታወቂያ ሚኒስቴሩ ገልጿል። የህወሃት አገዛዝ ኤርትራን እንዲወር ከአሜሪካ ፈቃድ አግኝቻለሁ እያለ በመናገር ላይ መሆኑን የገለጸው የኤርትራ መንግስት፣ በተለይም ከኤርትራ ጋር ግንኙነት አላቸው ብሎ የሚጠረጥራቸውን ሃይሎች ለማሸማቀቅ እየጣረ መሆኑን ገልጿል።

‹‹ተንጠልጥሎ መቅረት እንደኢትዮጲያ !›› (አሌክስ አብርሃም)

freedom.jpg
አንዳንዴ ምን ይገርመኛል መሰላችሁ እኛ ኢትዮጲያዊያን ነገሮችን ሞቅ በማድረግና ወዲያው እርግፍ አድርጎ በመተው (በመርሳት) በሽታ የተለከፍን ይመስለኛል ….ለዛም ነው ታሪካችን በእንጥልጥል ፣ እውቀታችን በእንጥልጥል ፣ ስልጣኒያችን በእንጥልጥል ፣ፍቅራችን በእንጥልጥል ሁሉም ነገራችን በእንጥልጥል የሚቀረው !! …እንደኔ እንደኔ የፕሮፌሰር መስፍን የ‹‹መክሸፍ›› ቲዎሪ ከመክሸፍ ይልቅ ‹‹ተንጠልጥሎ መቅረት›› የሚለው ቃል በትክክል የሚገልፀው ይመስለኛል …መክሸፍ የተጀመረ ነገር ዳግም ላይመለስ ላያንሰራራ እንደገናም ከቆመበት ላይቀጥል መበላሸት መጨናገፍ መቆም ነው ትርጓሜው …እንደውም መክሸፍ እረፍት ነው !! በቃ አንድ ነገር ላይመለስ መኮላሸቱን አውቆ ከ ሀ ለመጀመር ሳያበረታታ አይቀርም ! ለመክሸፍማ አልታደልንም!

በሶርያ .የኢትዮጵያውያን ስደተኞች አቤቱታ.

” በጦርነት ውስጥ እያለን የዜግነት ማረጋገጫ አቅርቡ ተባልን “
* ” ማጣራት ካስፈለገ ከወጣን በኋላ ያጣራ !”
* ” በሊባኖስ ቤሩት ኢንበሰሲያችን አይተባበረንም !”
* ” የምንኖረው በኢትዮጵያ አምላክ ጥበቃ ብቻ ነው! “
የሻም ታሪካዊ ምድር ጥንታዊዋ ደማስቆስ ሶርያ በጦርነት አረንቋ ተዘፍቃ ትገኛለች ። በዚህችው ምድር በመቶዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን በህገ ወጥ ደላሎች እየታለሉ ለስራ ይገባሉ ። ይህ ሁኔታ አሁን ድረስ መቀጠሉን ከሶርያ ደማስቆ የደረሰኝ ተጨባጭ መረጃ ያስረዳል ። ከደማስቀስ የደረሰኝን ይህንን መረጃ መሰረት አድርጌ በዚያው ስላሉ እንደ ጨው የተበተንን ዜጎች ጩኸት በዛሬው የማለዳ ወጌ የምለው አለኝ …

ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ ከአስመራ ለመጀመሪያ ጊዜ ለጋዜጠኛ ሲሳይ አጌና ተናገሩ

ብረት አንስተው የሕወሓትን መንግስት እጥላለሁ ብለው አስመራ የዘመቱት ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ ከአንድ ወር በኋላ ለመጀመሪያ ጊዜ ከጋዜጠኛ ሲሳይ አጌና ጋር ቆይታ አድርገዋል:: ዶ/ር ብርሃኑ እርሳቸው ከዘመቱ በኋላ ሕዝብ እያወራው ስላለው ነገር ሲናገሩም “ጆሮ ሰጥቼ ስከታተለው አልነበረም” ብለዋል:: ሙሉውን ያድምጡት::

‹‹ከዳኞች ጋር ምንም ችግር የለብንም ከማን ጋር እንደተጣላን ገብቶናል›› በእስር ላይ ያሉ ጦማሪያን

‹‹አንድ ዳኛ ምንም ማድረግ አይችልም›› ዳኛ ዘሪሁን ደሳለኝ ‹‹ከዳኞች ጋር ምንም ችግር የለብንም ከማን ጋር እንደተጣላን ገብቶናል›› በእስር ላይ ያሉ ጦማሪያን በተጠረጠሩበት የሽብር ተግባር ወንጀል ክስ ከተመሠረተባቸው በኋላ የከሳሽ ዓቃቤ ሕግ የሰውና የሰነድ ማስረጃ ቀርቦባቸው ለብይን የተቀጠሩት አራት ጦማሪያን፣ ለአራተኛ ጊዜ ጳጉሜን 2 ቀን 2007 ዓ.ም. ተለዋጭ ቀጠሮ መሰጠቱን ተቃወሙ፡፡ ተከሳሾቹ ጦማሪያን ናትናኤል ፈለቀ፣ አቤል ዋበላ፣ አጥናፍ ብርሃኔና በፍቃዱ ኃይሉ ጳጉሜን 2 ቀን 2007 ዓ.ም. ብይን እንደሚሰጥ የጠበቁ ቢሆንም፣ ጉዳያቸው በሦስት ዳኞች የሚታይ ከመሆኑ አንፃር በዕለቱ አንድ ዳኛ አቶ ዘሪሁን ደሳለኝ ብቻ የተገኙ በመሆናቸው ብይኑ ሳይሰጥ ቀርቷል፡፡

ሰበር ዜና ህዝባዊ ወያኔ ሐርነት የሚመራዉ ጽንፈኛ ቡድን ድንጋጤ ላይ ወድቋል፤፤

asee
ህዝባዊ ወያኔ ሐርነት የሚመራዉ ጽንፈኛ ቡድን ድንጋጤ ላይ ወድቋል፤፤
ዛሬ ይህዉ ወንጀለኛ ቡድን በመከላከያ ሚኒስቴር በኩል የመከላከያ ሰራዊቱ አጠቃላይ አዛዦችን ባጠቃላይ አስቸኳይ ስብሰባ ጠርቷል። በተለይም የሰሜኑና የምስራቁ እዝ አዛዦች ላይ ትኩረት ያደረገዉ ይህዉ ድንገተኛ ጥሪ የጦርነት ነጋሪትን ለመጎሰም ይመስላል ይላሉ መረጃዉን የላኩልን ግለሰብ።

Wednesday, August 26, 2015

አሁንም ኢትዮጵያዊያን መሰደዳቸውን አላቋረጡም፡፡

በኢትዮጵያዋ የድንበር ከተማዋ መተማ አሁንም ኢትዮጵያዊያን መሰደዳቸውን አላቋረጡም ሲል ዘጋርዲያን ዘገብዋል።
መንግስት ጥበቃውን አጠናክሮ በአካባቢው ብዙ ሰራዊት ቢያሰማራም በቀን ከ100 እስከ150 የሚሆኑ ኢትዮጵያዊያን ስደተኞ ድንበር አቋርጠው ይሰደዳሉ። መተማ ከተማ ወደ መቶ ሽህ የሚገመት ነዋሪዎች ያላት ስትሆን የኢትዮጵያ፣ ኤርትራና ሶማሌ ስደተኞች መተላለፊያ ናት።

የትግራይ ነጻ ዓውጭ ድርጅት ወያኔ የተባለ ወሮበላ ቡድን፥ በአማራ ሕዝብ ላይ የሚፈጽመው በደል ያስመረረው የሰሜን ጎንደር ሕዝብ የሚያሰማው በምስል የተደገፈ የድረሱልን ጥሪ፥

ጎንደርን ከትግራይ በሰሜን በኩል የሚለየው የተፈጥሮ ወሰን፣ የተከዜ ወንዝ፣
በምዕራብ ከሱዳን የሚለየው የተፈጥሮ ወሰን የ ጓንግ ወንዝ መሆኑ ይታወቃልና፥ ከዚህ እውነታ ንቅንቅ ማለት በምንም መንገድ የማይሞከር ነው፥
እርስታችንን የማስከበርና ድንበራችን የመከላከል ሃላፊነት ዓለብን እያለ ነው ገበሬው፥ ስለዚህ ይህ እኩይ የወያኔ ዓላማ ዓገራችንን ወደከፋ የእርስበርስ እልቂት እንዳይወስዳት ሁላችንም በዓንድነት የወያኔን ሥርዓት በቃ ልንለው ይገባል፥
ዓማራን ዓጥፍቶ ኢትዮጵያን ለመበታተንና ታላቋን ትግራይ ለመመስረት የሚያደርገው ከንቱ ምኞት በቸልተኛነት የማይታይ ዓይን ያወጣ ወረራ ነው፥
በተለይም በሸዋ፣ በወሎ፣ በጎጃምና በጎንደር ዓማራ ሕዝብ ላይ የተያዘው የማፈናቀልና የዘር ማጥፋት ዘመቻ፥ ደረጃውን ከፍ ዓድርጎ በሰሜን ጎንደር ክፉኛ እየሰሩበት ይገኛል፥

አንተ የምትተኛ ንቃ!

አንባገነኖችን የበለጠ አንባገነን፡ ጨካኞችን የበለጠ ጨካኝ ያደረገውን አስተሳሰባቸውን ዛሬ በተቃውሞ መልክ ወደ ህዝብ እያወረዱ ይገኛሉ። ሆነ ብለው በታቀደና በተጠና መልኩ የተጠበቡበትን ከግብር እና ከእንጀራ አባቶቻቸው ከፋሽስቶች የተማሩትን የከፋፍለህ ግዛ እስትራቴጂ በመጠቀም በቅድሚያ የኢትዮጵያዊነት ተቀዳሚ አቅንቃኝ የነበሩትን አማራንና የኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስትያንን የመቆጣጠርና የማዳከም ስራ ጨረሱ፡፡ የኦሮሞን ህዝብ በአማራው ላይ በጠላትነት እንዲነሳና በሁለቱ ታላላቅ ህዝቦች መካከል የጠላትነት መንፈስን ለመፍጠር ሰሩ፡ በዚህም የፈለጉትን ያህል ፍሬ አፈሩ። ቀጥሎም ሙስሊሙን ከክርስትያኑ ለማጋጨት በሙስሊሞች ስም ብዙ ቤተ መቅደሶችን አቃጠሉ። ብዙ ክርስቲያኖችን ገደሉ።

ሰምተሃል ኮካ

ድመት አይጥ እንዲይዝ ተብሎ ችቦ አይበራለትም! 
ከዕለታት አንድ ቀን አንድ ጠበቃ ይሞትና ወደ ሰማይ ቤት ይሄዳል፡፡ በገነት በራፍ ላይ ቅዱስ ጴጥሮስ ያገኘዋል፡፡ ቅዱስ ጴጥሮስ የሁሉም ሰው ኃጢያት መዝገብ በእጁ ነውና የጠበቃውን ስም ፈልጎ ያገኘዋል፡፡ ከዚያ የሰራውን ኃጢያት ዝርዝር ያያል፡-
1ኛ. አንድን ከአየር መበከል ጋር ተያይዞ የተከሰሰን ሰው በመከላከል ጥብቅና ቆሟል
2ኛ. ደህና ገንዘብ ይከፈልሃል ስለተባለ ብቻ በግልፅ በነብስ ግድያ የተከሰሰን ነብሰ ገዳይ በመከላከል ጥብቅና ቆሟል፡፡ 
3ኛ. አብዛኛዎቹን የጥብቅና ደምበኞቹን ከልኩ - በላይ አስከፍሏል፡፡
4ኛ. አንዲትን የዋህ ሴት ለሌሎች ወንጀለኞች ጥፋት ማምለጫ ሰበብ እንድትሆን በመፈለግ፤ እንዲፈረድባት አድርጓል፡፡ 

አንዱ በአንድ ወቅት

አንዱ በአንድ ወቅት ቢራ አትጠጡ የቴዲን ሙዚቃ አትስሙ በማለት ከፖለቲከኛነት ወደፓስተርነት ተቀይሮ ህዝቡንም ከህወሀት ባርነት ሳይሆን ከሐጢያት ባርነት ለማውጣት ሲታትር ከሸፈ።
አሁን ደግሞ "የፕሮፌሠር መስፍን ወልደማርያምን መፅሐፍ በማቃጠል የኦሮሚያን ህዝብ ነፃ እናወጣለን" በሚል የተዘጋጀ ታላቅ ህዝባዊ ስብሰባ በኦነግ አዘጋጅነት ተካሄደ የሚል ዜና ከOMN እየጠበኩኝ ነው።
እመኑኝ ኦነግ የሚባል ድርጅት በህይወት የለም። በተለያዩ የአለማችን ክፍሎች የኦነግ አባል ነን እያሉ የሚደሰኩሩት ኦሮመኛ ተናጋሪ የህወሀት ሰዎች ናቸው።

በሓወልቲ ሰማእታት ለምትገኘው ኣቶ Daniel Berhane

፩) ኣብዛኞቹ የቀበሌና ወረዳ ተወካዮች፣ የሴቶችና የገበሬዎች ማህበራት ተወካዮች፣ ማንበብና መፃፍም እንደማይችሉ ማረጋገጥ ከፈለግክ የተሰጣቸው ማስተወሻ በእጃቸው መኖሩና ኣለመኖሩ ለማየት ሞክር
፪) ኣቶ ኣባይ ወልዱ የኮሚቴው ኣባል መሆን ኣይጠበቅባቸውም። በሳቸው ስር ወይም ኔትወርክ ያሉ ሌሎች ኣባላት የኮሚቴው ኣባል ሁነው ኣስፈፅመዋል።
ይህም የሃገራዊ ምርጫ ልምድ መቅሰም ትችላለህ። እንደ የኣዲስ ኣበባው ኣንጃ ቅስቀሳና ፍላጎት ቢሆንማ ማንም ኣባይ ወልዱ በስልጣን እንዲቆይ ኣይፈልግም ነበር።

‹‹ወራዳ! አሁንም እደግመዋለሁ ወራዳ!›› ያለው ማን ነበር?

አቶ መለስ ናቸው! እውነታቸውን ነው፡፡ መንግስት ተብየው፣ ህወሓት/ኢህአዴግ ወራዳ ነው!
ዛሬ የእሳቸውን አባባል ልጠቀም ነው፡፡ ‹‹መንግስት›› የሚባለው ወራዳ ነው፡፡ እደግመዋለሁ ተቃዋሚዎችን ለማጥቃት ደህንነትና አባላቱን የሀሰት ምስክርነት አስጠንቶና አደራጅቶ ፍርድ ቤት የሚልከው ኢህአዴግ ወራዳ ነው! ወራዳ!

የደኢህዴን አመራር የህዝብ ቁጣ ላይ እሳት እየጨመረ እንደሚገኝ ርዕሰ መስተዳደሩ ተናገሩ

የደኢህዴን አመራር የህዝብ ቁጣ ላይ እሳት እየጨመረ እንደሚገኝ ርዕሰ መስተዳደሩ ተናገሩ
‹‹በአመራሩ መካከል ትርምስና ጥርጣሬ ተፈጥሯል››
‹‹ሰማያዊና መድረክ ማሸነፍ ይችሉ ነበር›› አቶ ደሴ ዳልኬ
በቅርቡ ታደለ ቱፋ የተባለ ግለሰብ በጋሞ ብሄር ላይ የጻፈውን መፅሃፍ አስመልክቶ በደኢህአዴን አመራሮች መካከል የተፈጠረውን ውጥረት ለማርገብ በተደረገ ሚስጥራዊ ስብሰባ ላይ የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ ደሴ ዳልኬ የደኢህዴን አመራር የህዝብ ቁጣ ላይ እሳት እየጨመረ ነው ሲሉ መግለፃቸውን ለነገረ ኢትዮጵያ የደረሰው የድምፅ ማስረጃ አረጋገጠ፡፡
የጋሞ ጎፋ ዞን በተለይም የአርባ ምንጭ የደኢህዴን አመራር በፌደራል ደረጃ በጥርጣሬ እንደሚታይ የገለፁት አቶ ደሴ ዳልኬ የጋሞ ጎፋ ዞን የደኢህዴን አመራሮች ከመጽሐፉ ፀሐፊ ጀርባ አሉ በሚል አመራሩ እርስ በእርስ ጥርጣሬ ውስጥ እንደሚገኝም ነገረ ኢትዮጵያ እጅ የገባው ድምፅ አረጋግጧል፡፡ በዚህም ምክንያት በክልሉ ርዕሰ መስተዳደርና በሌሎች አመራሮች መካከል ግልፅነት እንደሌለ ገልጸው ‹‹እናንተ ለእኔ ግልፅ ሁኑ!›› ሲሉ ተደምጠዋል፡፡

በኢትዮጵያ በተለያዩ ክልሎች ተከስቶ ያለው ድርቅ

በኢትዮጵያ በተለያዩ ክልሎች ተከስቶ ያለው ድርቅ የምግብ ፈላጊዎች ቁጥር እየጨመረ እንዲሄድ ማድረጉን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አስታወቀ። የአስቸኳይ የምግብ እርዳታ ተረጂዎች ቁጥር መጨመርን ተከትሎም የኢትዮጵያ መንግስት የተጨማሪ የ230 ሚሊዮን ዶላር እርዳታ ጥሪ ማቅረቡን ሮይተርስ ዘግቧል ።
ለምግብ እጥረት አደጋ ሊጋለጡ ይችላሉ ተብለው ከተገመቱ 14 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን መካከል 4.5 ሚሊዮን የሚሆኑት በተያዘው አመት አስቸኳይ የምግብ እርዳታን እንደሚፈልጉ የተባበሩት መንግስታት ድርጅት መረጃን ዋቢ በማድረግ ሮይተርስ በዘገባው አመልክቷል። በሀገሪቱ የተከሰተው የዝናብ እጥረት አደጋ ከተተነበየው የከፋ ነው ያሉት የተባበሩት መንግስታት ድርጀት ሀላፊዎች በምግብ እጥረቱ የሚጎዱ ሰዎች ቁጥርም እየጨመረ መምጣቱን ይፋ አድርጓል ።

ጥቂት ትዝታ ዶ/ር ነጋሶ ቤት ከነበረኝ ቆይታ

ዳንኤል ተፈራ
ትናንት አንድ ቀጠሮ ይዘን ነበር….. አዎ!... ይሄው በቀጠሯችን መሰረት ከች፤ የመብራቱ መኖርና ‹‹የኢንተርኔት ኮኔክሽን›› መከሰት ታክሎበት በትናንትናው ዕለት ከዶ/ር ነጋሶ ጋር ስለነበረኝ ቆይታና ትዝታ ጥቂት ለማለት በቃሁ፡፡
ዶ/ር ነጋሶ የሚኖሩት ብስራተ ገብርኤል አካባቢ በመንግስት ቤት ነው፡፡ ያውም ፖለቲካው ላይ ሲያከሩ ቂመኛው ህወሃት/ኢህአዴግ ‹‹ልቀቁ!›› እያለ እያንገራገራቸው ነዋ! ለአዛውንቱ ፕሬዘዳንት ግርማ በየወሩ 400 ሺ ብር ሆጭ እያደረገ የሚያቀማጥለው ገዥ ፓርቲ ለዶ/ር ነጋሶ ዞሮ መግቢያ ጎጆ ሊከለክላቸው ይፈልጋል፡፡ የመለስ/ኃይለማሪያም አገዛዝ በስልጣን ዘመናቸው የነበራቸውን መኪና ነጥቆ በእግራቸው ከህዝብ ጋር እየተጋፉ ሲሄዱ እየተመለከተ መሳቅ ያምረዋል - ጥርስ የለውም እንጅ፡፡ ነገርግን ዶ/ር ነጋሶ ከህዝብ ጋር በመሆናቸው ከበሩ እንጅ እንደጠበቁት አልተዋረዱም፡፡

ሰበር መረጃ ውጥረቱ እያገረሸ መሆኑ ተሰማ

መከላከያ ሰራዊቱ ጥቃት ወይም ወረራ ለማድረግ ከፍተኛ ሰራዊት እያከማቸባቸዉ በሚገኙት በሰሜኑ አካባቢዎች አለመረጋጋት ነግሰዋል።
በትናንትናዉ እለት አንድ ጓድ መሪ 9 የሰራዊት አባላትን ከመመሪያ ዉጭ ይዞ በመንቀሳቀሱ እርሱን ለመከተል ፍለጋ ላይ የነበረ አነስተኛ የጦር ክፍል የኤርትራን ቀጠና አልፎ በመሄዱ ተደምስሷል።

አዲሱ ለገሰ በድጋሚ ተሰናበቱ

ብአዴን ባደረገው ጠቅላላ ጉባኤ አቶ አዲሱ ለገሰ በድርጅቱ የመተካካት መርህ መሰረት የነበራቸውን ሃላፊነት አስረክበው በክብር ስለ መሰናበታቸው ተሰምቷል።
አስገራሚው ነገር የቀድሞው ምክትል ጠ/ሚ/ር ከዚህ በፊት ለመተካካቱ ግምባር ቀደም አርአያ በመሆን በክብር ስለ መሰናበታቸው ተነግሮ ነበር።የሄዱት አዲሱ በሌላ ሀላፊነት ብቅ በማለት የተሰናበቱትን ፖለቲካ ተቀላቀሉት።አሁን ደግሞ በብአዴን ጠቅላላ ጉባኤ ፊት ቀርበው መሰናበታቸው ተነግሯል።

በአዲስ አበባ የሚኖሩ የትግራይ ባለ ሃብቶች ሀብታቸውን እያሸሹ ነው


በአዲስ አበባ ከተማ የሚኖሩ የትግራይ ባለ ሃብቶች በትግራይ ክልል ኢንቨስት እንዲያደርጉ የተደረገላቸው ቅስቀሳ በክልሉ ውስጥ ያለው ስር የሰደደ ብልሹ የአስተዳደር ሁኔታመጀመሪያ ይስተካከል ማለታቸውን ተገለፀ።
በምንጮቻችን መረጃ መሰረት- በአዲስ አበባ ከተማ ውስጥ የሚኖሩ የትግራይ ተወላጅ ባለሃብቶች ያላቸውን ሃብት በትግራይ ክልል እንዲያሰማሩ ይርዳው በተባለ ከፍተኛ የህወሃት ካድሬ ነሓሴ 3/2007 ዓ/ም በተካሄደው ቅስቀሳ የተሞላበት ስብሰባ በብልሹ አሰራራችሁ የተጨማለቀውን አሰራራችሁ ካልተስተካከለ ገንዘባችንና ግዚያችንን አናባክንም ብለው እንደተቃወሙ ታወቀ።

የህውሃት አሽከር የሆነው ብአዴን

የህውሃት አሽከር የሆነው ብአዴን አሽከር ደመቀ መኮነን አማራው ተገፍቷል ተፈናቅሏል ይህን ህገ ወጥ ተግባር ደግሞ ብአዴን ብቻ ሳይሆን ሁሉም የመንግስት ድርጅቶች ሃላፊነቱን መውሰድ አለባቸው ብሎ መናዘዝ መጀመር ከምን የመነጨ ይሆን? ይህ ነገር ውጫዊ ተፅእኖው ምን ያህል እንደበረታባቸው ማሳያና የተገፋውን የተገደለውን የተባረረውን አማራ አለንልህ ችግርህን የምንፈታልህ እኛው እና እኛው ብቻ ነን ሌሎች የሚሉህን አትስማ ብሎ የከሰረ ፖለቲካ የመስራት የታሰበች ቧልት መሆኗን 100%( ቅርጫ ቦርድ ይህ የእኛ ነው ለምን ተጠቀምህ እንደማትሉኝ ተስፋ አለኝ) አውቀናል ነቅተናል። 

ቴዲ አፍሮን ከፋሽስት ርዝራዦች ጥርስ እናስለቅቅ!

አስደንጋጭ መረጃ ስለ ቴዲ አፍሮ!
ከዛሬ ወር በፊት አንድ የህወሃት ሰላይ እንዲህ አለኝ፡፡ የቴዲ አፍሮን አዲሱን ዜማ እየሰማሁ ሳለ አምልጦት ነው መሰል እንዲህ አለኝ ከዚህ በኋላ በምንም ተዓምር የቀድሞ ዝናውን አያገኝም፡፡ ለምን ስለው ለሱ የታሰቡ ነገሮች አሉ አለኝ፡፡ ምንድንነው ስለው ሀገር ቤት ለሚገኙ ማንኛውም ድርጅት ለቴዲ አፍሮ የሙዚቃ ኮንሰርቶች ስፖንሰር እንዳይሆኑ ያለበለዚያ የንግድ ፈቃዳቸው እንደሚቀማ የተነገራቸውም አሉ፡፡ ከዛስ አልኩት እንደውም እየሰራ የሚገኘውን አዲሱን አልበም በዱርዬዎች ለማሰረቅ ሀሳብ ቀርቦ ነበር፡፡ በዚህም እሱን በኢኮኖሚ ማዳከም ስለሚያስፈልግ ብሎ ጨመረልኝ፡፡ እስካሁን ከቁም ነገር አልቆጠርኩትም፡፡

ከ4 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር በላይ አስቸኳይ የገንዘብ እርዳታ ያስፈልጋል ተባለ

1796634_222183061305326_875283870_n
በኢትዮጵያ 4 ነብ 5 ሚሊዮን ሕዝብ አስቸኳይ የምግብ እርዳታ እንደሚያስፈልጋቸው መንግስትና የተባበሩት መንግስታት ድርጅት አጋር የሰብዓዊ እርዳታ ድርጅቶች ዛሬ በጋራ በሰጡት መግለጫ አስታውቀዋል። በተያዘው አመት 2 ነጥብ 7 ሚሊዮን ኢትዮጵያውያን አስቸኳይ እርዳታ እንደሚያስፈልጋቸው ታስቦ የነበረ ቢሆንም፤ የተረጅዎች ከግምት ውጪ ላሻቀበው የተረጅዎች አሀዝ ብቻ 230 ሚሊዮን ዶላር ወይም ከ 4 ነጥብ 7 ቢሊዮን ብር በላይ እንደሚያስፈልግ በጋራ መግለጫው ላይ የተመለከተ ሲሆን፤ከዚህ መካከል መንግስት 33 ሚሊዮን ዶላር ያህሉን መመደቡና ቀሪው 200 ሚሊዮን ዶላር በአስቸክይ ከውጭ ለጋሾች የሚጠበቅ መሆኑ ተገልጿል።

በኦጋዴን ነጻ አዉጭ በአርበኞች ግንቦት 7 እና በጥምር ሐይሎች በሁለት አቅጣጫዎች ከፍተኛ ጦርነት ተቀሰቀሰ


በኦጋዴን ነጻ አዉጭ በርበኞች ግንቦት 7 እና በጥምር ሐይሎች በሁለት አቅጣጫዎች ከፍተኛ ጦርነት ተቆስቁሶ ነገር ግን የመጨረሻ የማጥቃት እርምጃ ለመዉሰድ ታግደናል እየተደበደብን ነዉ፤፤
ይላል የወያኔ መንግስት የሰሜኑ እና የምስራቁ እዝ።
ዛሬ ለሊት ከ23፡00 ሰአት ጀምሮ በሰሜን ጎንደር ልዩ ኮዱ 13.274645/ 37. 878478 በሰሜን ኦጋዴን ጋላዲ ጠረፍ አካባቢ ከባድ ዉጊያ ገጥሞናል በተለይ ሰራዊታችን በአየር ሐይሉ ላይ ምንም እምነት የለዉም፤፤
ዞሮ ሁሉ ሊደበድበን ይችላል ቃኘዉ አየር ሐይል በረራዎችም እያመጡ ያለዉ መረጃ ምንም የትም የማያደርስ ነዉ።

የደኢህዴን አመራር የህዝብ ቁጣ ላይ እሳት እየጨመረ እንደሚገኝ ርዕሰ መስተዳደሩ ተናገሩ

‹‹በአመራሩ መካከል ትርምስና ጥርጣሬ ተፈጥሯል››
‹‹ሰማያዊና መድረክ ማሸነፍ ይችሉ ነበር›› አቶ ደሴ ዳልኬ
በቅርቡ ታደለ ቱፋ የተባለ ግለሰብ በጋሞ ብሄር ላይ የጻፈውን መፅሃፍ አስመልክቶ በደኢህአዴን አመራሮች መካከል የተፈጠረውን ውጥረት ለማርገብ በተደረገ ሚስጥራዊ ስብሰባ ላይ የደቡብ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ ደሴ ዳልኬ የደኢህዴን አመራር የህዝብ ቁጣ ላይ እሳት እየጨመረ ነው ሲሉ መግለፃቸውን ለነገረ ኢትዮጵያ የደረሰው የድምፅ ማስረጃ አረጋገጠ፡፡

በሽብር ክስት ታስረው የነበሩት እነ ኣብራሃ ደስታ ዛሬ ጥዋት ከእስር ተፈቱ።

11035502_771235849624393_3401706099381023667_n
ጀግኖቹ እነ ኣብራሃ ደስታ ዛሬ ጥዋት ሓሙስ 14 / 12 / 2007 ዓ/ም ከእስር በነፃ ተፈቱ።
ከዓመት በፊት በሽብር ክስት ታስረው የነበሩት ጀግኖቹ የሰለማዊ ትግል ጀግኖች ከተከሰሱበት የፈጠራ ክስ ነፃ ተብለው ተፈትተዋል።
፩) ኣብራሃ ደስታ ከዓረና
፪) ሃብታሙ ኣያሌው ከኣንድነት
፫) የሺዋስ ኣሰፋ ከሰማያዊ
፬) ዳኑኤል ሺበሺ ከኣንድነት
ከተከሰሱበት የሽብር ክስ በነፃ ተሰናበቱ።

የህወሓት 12ኛ ጉባኤ መካሄድ ተከትሎ የሊቀ መንበርነት ስልጣን ሽኩቻ እየተካሄደበት ይገኛል።

የህወሓት 12ኛ ጉባኤ መካሄድ ተከትሎ የሊቀ መንበርነት ስልጣን ሽኩቻ እየተካሄደበት ይገኛል። ኣብዛኛው የትግራይ የፌስቡክ ኣክትቪስቶች፣ ወጣቶችና ሙሁራን የህወሓት ኣባላት፣ ሌሎች ለውጥ ፈላጊ ኣክትቪስቶችና ሌሎች ፖለቲከኞች በጉጉት እየጠበቁት ይገኛሉ። የኣርከበ በድምፅ በጉባኤው መሳተፍ ለብዙዎች የኣዲስ ኣበባው ኣንጃ ወደ ኣሸናፊነት የተጠጋ ቢመስላቸውም ጉዳዩ ሌላ ነው። ኣርከበ ተመልሶ የማይወዳደር መሆኑ ስላረጋገጡ የትግራዩ ኣንጃም እንዲሳተፍ በኣንድ ለ ኣምስት ኔትወርክ ታስረው የመጡት የወረዳ ተሳታፊዎች(ማንበብና መፃፍ የማይችሉ የሚገኙባቸው ሴቶችና ገበሬዎች የሚገኙባቸው የኣባይ ወልዱ ታማኞች ) እንዲፈቅዱለት ኣድርገዋል።

ብአዴን በተለያዩ ክልሎች እና በውጭ አገር የሚገኙ የአማራ ተወላጆችን ለማደራጀት ያደረገው ሙከራ መክሸፉን አስታወቀ።

ድርጅቱ በ11ኛው ድርጅታዊ ጉባኤ ላይ እንደገለጸው፣ ለረጅም ጊዜ በአመራርነት ቆይቶ ስልጣኑን በመተካካት ሂደት ባስረከበውና ቁልፍ ስልጣኑን በተረከበው መካካል የመግባባት ችግር መኖሩን ገልጿል። ነባሩ አመራር ሁሉንም ሃላፊነት አስረክቦ ድርጅቱን የመልቀቅና ራሱን ገለል አድርጎ ለመኖር ይፈልጋል ያለው ብአዴን፣ በዚህም ላይ ነባሩ አመራር በአዲሱ አመራር እንደማይረካና ተደጋጋሚ ቅሬታ እንደሚያቀርብም ገልጿል። ቁልፍ ስልጣን የተረከበው አዲሱ አመራርም የራሱን አቅም የማያውቅ፣ ስልጣኑን ካስረከበው ነባር አመራር ለመማር ፍላጎት የሌለው ነው ብሎአል። በአዲሱ እና በነባሩ አመራር በኩል ለታየው አለመግባባት ምንጩ ዲሞክራሲያዊ ትግል አለመጎልበት፣ አድባርይነት ፣ ፊት ለፊት ለመታገል አለመፈለግ፣ ድክመቶችን ለመቀበል ፍላጎት አለመኖር፣ ሂስና ግለሂስን አለመቀበልና የድርጅቱን አሰራሮችን በተግባር ለማዋል ፍለጎት አለማሳየት ናቸው ብሎአል።

ትኩረት ፍለጋ.... ለኔ፣ እኔ፣ የኔ

ትኩረት ፍለጋ Attention seeking በሽታ ነው።
ሆኖም ይህ ክፉ ባህሪ አደገኛ የአዕምሮ በሽታ መሆኑን ስለማናውቅ በደፈናው "ትኩረት ሽቶ/ሽታ ነው" እንላለን። ብዙ ጊዜ ሕፃናት ላይ የሚታየው ትኩረት ፍለጋ እድሜ ሲጨምር እየለቀቀ የሚመጣ ቢሆንም አንዳንድ ሰዎች ላይ ከበጎው ትኩረት መሻት መስመር ያልፍና የእኔነት ደዌ ይጣባል።
ባህሪው በአዋቂዎች ላይ ሲሆን የሕይወትን ዋጋ እስከመክፈል እንደሚያደርስ በሥነልቡና ዘርፍ የተሰማሩ የጤና ባለሞያዎች ይገልጻሉ። የሌሎችን ትኩረት ለመሳብ ሲሉ የትኛውንም፣ ማንኛውንም ዋጋ ይከፍላሉ። ሊዋሹ ይችላሉ፣ ወይም ለትኩረት ሲሉ ብቻ ገንቢ የሆኑ ሥራዎችን በመስራት ለስኬታማነት ይደክማሉ።

አንድ አሜሪካዊ ወደ ትልቅ

አንድ አሜሪካዊ ወደ ትልቅ እና ቆንጆ ሬስቶራንት ከምታምር
ሚስቱ ጋር ይገባል ፡፡ ሬስቶራንቱ በሰው ተሞልቷል ...... ወደ
ሬስቶራንት እንደገባ ጥግ ላይ ብቻውን የተቀመጠ ጥቁር
አፍሪካዊ ያያል ፡፡ ይህ አሜሪካዊ ጥቁር በጣም ይጠላ ነበርና
"አስተናጋጅ "ብሎ ጮክ ብሎ ተጣራ.... አስተናጋጁም በፍጥነት
መጣ ፡፡ የኪስ ቦርሳውን አወጣና እዚህ ሬስቶራንት ላሉት
በሙሉ ከዛ ጥቁር ሰው ውጭ ( ወደ አፍሪካዊው እየጠቆመ )
የሚበላ ምግብ ታዘዛቸው አለው ፡፡ ይህን ይከታተል የነበረው
አፍሪካዊ በፈገግታ አሜሪካዊውን አየው ፡፡

ነባር ታጋይ

ፈትለወርቅ ይባላሉ። ነባር ታጋይ ናቸው። የህወሀት ማህክላዊ ኮሚቴ አባል ናቸው። የአባይ ፀሀዬ ሚስት ነበሩ። የባለሀብቱ ዳዊት ገብረእግዚያብሄር እህት ናቸው። ምን ማለት ፈልጌ ነው
፩) የህወሀት ማህከላዊ አባላት ሚስት ውሽማ አክስት ወንድም አጎት የሚሰበሰብበት የቤተ ዘመድ ስብሰባ መሆኑ ና
፪) ባላሀብቱን ጠርጥር ጠርጥር እያለኝ መሆኑን ነው።

'አስተርጓሚ'

የትናንትናው የገንዘቤ ዲባባ ቃለ መጠይቅ ላይ የነበረው ጉደኛ 'አስተርጓሚ' ተብዬ ላይ ትዝብታችንን መግለፃችንን ተከትሎ፥ የተለያዩ ወዳጆች፣ በውስጥ መልእክትም በአደባባይም፥ “ቋንቋ አለመቻል ምንም ማለት አይደለም።” “የውጭ አገር ቋንቋ ባይችል አያስወቅስም።” እና መሰል የመከላከያ ነገሮችን ተናግረዋል።
እርግጥ ነው ቋንቋ አለመቻል ምንም ማለት አይደለም። እንኳን የውጭ ቋንቋ ይቅርና፣ የቤተሰቦቹን ቋንቋ ባይችልም ምንም ማለት አይደለም። ሲጀመር ቋንቋ ክህሎት እንጂ እውቀት አይደለምና ባይችሉ አያሳፍርም። መቻሉም ቢያስደንቅ እንጂ፥ የሚያስኮፍስ ነገር አይደለም። ሰው እንደዋለበትና እንደፈለገው ልክ የትኛውንም ቋንቋ ማወቅና በአግባቡ የመጠቀም ክህሎቱን ማሻሻል ይችላል።

Tuesday, August 25, 2015

አንደንቁዋሪው ዲስኩር … “ቁዋሚ ጥቅም እንጂ ቁዋሚ ወዳጅ የለም “! ቦጋለ ካሳዬ፣ አምስተርዳም

ብርሃኑ ነጋ በርሃ ገባ! ‘አሜሪካ ተቀምጠህ የጦርነት ፉከራኽን ተወን’! እያልን ስናብጠለጥለው እነሆ በተግባር አፋችንን ዘጋው አይደለም እንዴ? ተቀብለናል አቤ ቶኪቻው…. ስላቅህ እውነትነት አለው። ሰውየው መጀመሪያ የኢህአፓ አባል ሆኖ ነበር በ17 አመቱ የሽፈተው ። ዛሬ ደግሞ ከ40 አመታት በሁዋላ የአርበኝነት ትግል ለማካሄድ አስመራ ገብቱዋል። ምንም እንኩዋን ግንቦት ፯ ኤርትራ ከመሸገ ቢሰነባብትም ብርሃኑ ጨክኖ በዚህ እድሜው በርሃ ይገባል ብዬ በግሌ አስቤ አላውቅም ነበር።
ድጋፍ
ኢሳት ሬዴዮ ይሁን ቴሌቪዢን የብርሃኑን በርሃ መግባት ተከትሎ ለአርበኞች-ግንቦት-7 ድጋፍ እንዲገኝ እየተጋ ነው። አንድ ነጻ ካልሆነ የመገናኛ ብዙሃን የሚጠብቅ ስራ ነው ። ለኢትዮጵያ ሕዝብ ግልጽ እንዲሆንለት ይመስለኛል ኢሳት የሚሰበሰበውንም ገንዘብ በብር እያሰላ እየዘገበ ነው። ሚሊዮን በሚሊዮን እየተሆነ ነው።

ኢትዮጵያ፣ እምነታችን፣ አገራችን ባንድነታችን

ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም
ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ
እራሱን ሕዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ (ህወሀት) እያለ የሚጠራው አምባገነን ወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ ለረጅም ጊዜ በኃይማኖት ላይ ስልታዊ የሆነ ጥቃት በመሰንዘር በኢትዮጵያ ለብዙ ጊዜ ሊቆይ የሚችል የኃይማኖት ቅራኔ እንዲፈጠር አድርጓል፡፡Ethiopian Muslims protest Jan 23, 2014
እ.ኤ.አ በ1991 የወሮበላ የዘራፊ ቡድን ስብስብ የፖለቲካ ስልጣን እርካብን በሕዝብ ፈቃድ ሳይሆን በጠብመንጃ ኃይል ከተቆጣጠረ በኋላ የአስመሳይነት ባህሪውን በመጠቀም በተግባር ሳይሆን በባዶ ፕሮፓጋንዳ ሌት ከቀን የሚለፈልፍለትን የይስሙላ የእኩልነት እና የመቻቻል መርሆ ሰፍኗል በማለት በኢትዮጵያ የእስልምና እምነት ተከታይ ማህበረሰብ ዘንድ እርካሽ ተወዳጅነትን ለማትረፍ ሲፍጨረጨር ቆይቷል፡፡
ወያኔው የሙስሊሙን ማህበረሰብ የእምነት ግንዛቤ አሳንሶ በመመልከት እና እኔ አውቅልሀለሁ በማለት ከእምነቱ ተከታይ ህዝብ ልቆ በመታየት የትሮጃን ፈረስ በመሆን በመጋለብ ሲዳክር ይታያል፡፡

አሸባሪነት ሲሉ – ያኔ እሰከ ዛሬ (ታሪኩ አባዳማ)

ታሪኩ አባዳማ ነሐሴ 2007
ላለፉት ሁለት አሰርት ዓመታት በላይ በወያኔ አገዛዝ ስር የጭካኔ በትር ሰለባ የሆኑ ሰላማዊ ዜጎች ቁጥር በቀላሉ የሚሰላ ባይሆንም እንበለ-ሕግ ሰብአዊ መብት ማዋረዱ መርገጡ ግን እነሆ እስከ ዛሬ አላባራም። በአዲስ አበባ የሚፈፀመውን ግፍ እና በደል ሳይውል ሳያድር በትኩሱ ለማወቅ ዕድል ቢኖርም በሌሎች የአገሪቱ ክልሎች በምስጢር እስር ቤቶች እየታጎሩ ፣ በየጉድባዎች እየተረሸኑ የሚገኙ ሰለማዊ ዜጎች እሪታቸው የገደል ማሚቶ መሆኑ ቀጥሏል። ዛሬም እሪሪሪሪ ተገፋሁ… የሚለው ኢትዮጵያዊ ድምፅ ከመቸውም ግዜ የበለጠ ጎልቶ እያስተጋባ ነው። ወያኔ ሆነ ብሎ በሚቀሰቅሰው የሀይማኖት እና የጎሳ አምባጓሮ ውድ ህይወታቸውን ያጡ ፣ ቤት ንብረታቸው የወደመ ፣ የተፈናቀሉ ምስኪን ዜጎች ቁጥር እያሻቀበ ነው።
አሸብር ዜናዊ አስታቅፎን በሄደው ‘የሽብር ህግ’ መሰረት ፍፁም ሰላማዊ የሆኑ የእስልምና ሀይማኖት መሪዎች እስከ ሀያ ሁለት ዓመት በሚደርስ እስራት ፍርደኛ ተብለው የወህኒ ኑሯቸው መራዘሙ ለዚህ አንዱ ማሳያ ነው። ባለ ‘ራዕዩ መሪ’ ለገሰ ዜናዊ ያወረሰን የተወልን ሌገሲ።

ሆዳም ቢሰበሰብ መግላሊት ኣይከፍትም

ከብርሃኑ ተስፋዬ
የሰይጣኑን ሙት ኣመት ለማክበር በሚዘጋጁበት ወቅት ወያኔዎች ሆዳም ዲያስፖራዎችን ወደ ኣዲስ ኣበባ ጋብዘው ቡራ ከረዩ የሚሉበት ሁኔታ ስለገረመኝ ነው ይህን ጽሁፍ ለንባብ የማቀርብላችሁ። በመሆኑን መልካም ንባብ።Ethiopian Diaspora
መነሻ
በመጀመሪያ የሰው ልጅ ከትውልድ ቀየው ወደ ተለያዩ ቦታ ወይም የኣለም ክፍሎች የሚሰደደው ኣንድም በሃገሩ ባለው የፖሊቲካ፣ የሶሽያልና የኢኮኖሚ ሁኔታ ኣለመመቻቸት ነው ቢባል ማጋነን ኣይሆንም። እውነቱና ሀቁም ይህ ሆኖ ሳለ የተሰደደበት ችግር በሚቀረፍበት ጊዜ ኣንድም በኣካል ኣሊያም በሃሳብ፣ ማቴሪያል፣ ወይም በገንዘብ ለሃገሩ ኣስተዋጾ ያደርጋል። ይህንን ኣይነት ሁኔታ ሊፈጠር የሚችለው ግን በተሰደደበት ወቅት የነበረው የመንግስት ስርኣት ሲቀየር የሚከተላቸው ፖሊሲዎች ዲያይስፖራውን እንደ ኣንድ ኣገር ገንቢ ኣካል ቆጥሮ በእኩልነት ማሳተፍ የቻለ እንደሆነ ነው።

የአዲሱ ህውሀት መንግስት መጥፎ አጋጣሚ! (ከኤርሚያስ ለገሠ)

ከኤርሚያስ ለገሠ (ክፍል አንድ )
1 – ደስታ እና ሀዘን
ሰሞኑን ፍቺ በፍቺ ሆነናል። የዞን ዘጠኝ ጦማሪያን ከፊል አካል ተፈታ። ደስ አለን። የተፈቱት ካልተፈቱት ያላቸው ልዩነት ለብዙዎች ግራ ቢያጋባም!…ዛሬ ደግሞ እነ ሀብታሙ አያሌው ተፈተዋል። ይህም በግለሰብ ደረጃ ደስ የሚል ዜና ነው። ቢያንስ በቅርብ የማውቀው ሀብታሙ (” ሀብትሽ!”) ክፋ ደጉን የማታውቀው ልጁ እጁ ላይ ስታንቀላፋ፣ ወደ አልጋዋ ወስዶ ሲያስተኛት፣ ከእንቅልፏ ስትነቃ አቅፎ ሊያነሳት በመቻሉ ደስ ይለኛል። እንኳን ለዚህ አበቃህም ማለት እፈልጋለሁ።Ermias Legesse former Woyane govt. employee
በሌላ በኩል ገዥው ቡድን በምክንያት እያሰረ በምክንያት የሚፈታበት ሁኔታ ለራሱ ስልጣን መቆያ ትክክል ቢሆንም ለኢትዬጲያ የፍትህ ስርአት ምን ያህል ንቀት እንዳለው የሚያሳይ ተደርጐ ሊወሰድ የሚችል ነው። ሰዎች በህውሀት ላይ አደጋ ሲጋርጡ በፓለቲካ ውሳኔ ይታሰራሉ…ህውሀታዊ ምክንያት !። ገዥው ቡድን ላይ የተጋረጠው አደጋ በሌላ ጐን ሲያጋድል ደግሞ በእጁ ይዞ የሚያሰቃያቸውን ይፈታል…ህውሀታዊ የመፍታት ምክንያት!!