Saturday, August 31, 2013

መንግስት ዘንድ ከፍተኛ መደናገጥ ተፈጥሯል!

ለዛሬ ታቅደው የነበሩ ግዙፍ የቅስቀሳ መድረኮች ተሰርዘዋል!
የሃይማቶች ጉባኤ ያዘጋጀው ነው ተብሎ በሚዲያ የተገለጸው የነገው ሰልፍ ሙስሊሙ ህብረተሰብ በነቂስ እንደሚሳተፍበት ካሳወቀ በኋላ እጣ ፈንታው ምን እንደሆነ ማወቅ አልተቻለም፡፡ ይህ ከፍተኛ ዝግጅት እና ወጪ ተደረጎለት የሰነበተውን ሰላማዊ ሰልፍ ድንገት ሙስሊሙ ህብረተሰብ በስፋት እንደሚገኝበት መታወቁን ተከትሎ በመንግስት ወገን አካባቢ ከፍተኛ ድንጋጤ በመፍጠሩ የሰልፉ እጣ ፈንታ አልተለየም፡፡ ትናንት አመሻሹ ላይ ሊካሄዱ ታስበው የነበሩ የሰልፍ ዝግጅት ግምገማዎች በዚሁ ምክንያት ሙሉበሙሉ መሰረዛቸው የታወቀ ሲሆን በወረዳና በክፍለ ከተማ አካባቢ ያሉ የመንግሰት ሀላፊዎችም ለከፍተኛ ጭንቀት ተዳርገዋል፡፡

መቶ የሚሆኑ የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ወዳልታወቀ ቦታ ተወሰዱ!

998402_581787228530546_531722766_nመቶ የሚሆኑ የሰማያዊ ፓርቲ አባላት ወዳልታወቀ ቦታ ተወሰዱ!
አክራሪነት በጣም ሲያድግ ሲያድግ ሲያድግ አሸባሪ ደረጃ ይደርሳል ተብሎ ይሰጋል፡፡ አሸባሪስ ምን ያደርጋል… አሸባሪማ እገታ ይፈፅማል፡፡ በሆነው ባልሆነው፤ ህፃን፣ አዋቂ፣ ወንድ፣ ሴት ሳይለይ ይገድላል፡፡  እኔ ያልኩት ካልሆነ ሌላው ያለው በሙሉ ነውር ነው ብሎ ይደመድማል፡፡ ስለዚህ አክራሪነት እጅግ የከፋ አደጋ ነው፡፡ እኔ በበኩሌ አክራሪነትን እቃወማለሁ፡፡ አዲሳባ ብሆን ኖሮ አክራሪነትን በሚቃወመው ሰልፍ ላይ መሳተፌ አይቀርም ነበር፡፡ (ለራሴ ሰላማዊ ሰልፍ እወዳለሁ…)
አሁን በሰማሁት ዜና መቶ የሚደርሱ የሰማያዊ ፓርቲ አባላት መንግስት አግቶ ወዳልታወቀ ቦታ ወስዷቸዋል፡፡ ታድያ ከዚህ የበለጠ አክራሪነት ከዚህ የበለጠ ሽብርስ ከየት ይመጣል፡፡ አዎ በነገው ሰልፍ አክራሪነት በትክክል መወገዝ አለበት!!!
ኢህአዴግ አክራሪነት ይቁም!!!

የሰማይዊ ፓርቲ አመራሮች በስብሰባ ላይ እንዳሉ የወያኔ ፌደራል ፖሊስ ቢሮውን በመክበብ ሁሉንም የአመራር አባላትን በመኪና ጭኖ ወደ እስር ወስደዋቸዋል።



ከምሽቱ 1:00 ላይ የሰማይዊ ፓርቲ አመራሮች አራት ኪሎ 

አካባቢ በሚገኘው ጽ/ቤታቸው በስብሰባ ላይ እንዳሉ የወያኔ 

ፌደራል ፖሊስ ቢሮውን በመክበብ ሊቀ-መንበሩን ጨምሮ 

ሁሉንም የአመራር አባላትን በመኪና ጭኖ ወደ እስር 

ወስደዋቸዋል።በውጭም በውስጥም የሚኖረው መላው 

የኢትዮጵያ ህዝብ ድርጊቱን እንዲያወግዝና ለአለም-አቀፍ 

ተቁማትም ሁኔታውን እንዲያሳውቅ ጥሪ ቀርቧል። ሞት ለወያኔ 

ትግሉ ይቀጥላል።

በረከት ስምኦን በሰማያዊ ፓርቲ ዙሪያ እየዶለቱ ነው – (ከኢየሩሳሌም አርአያ)

gf
አቶ በረከት
በዶ/ር ብርሃኑ ነጋ ሊቀመንበርንት ከሚመራው ግንቦት ሰባት ጋር በተያያዘ በሰማያዊ ፓርቲ ዙሪያ በረከት ስምኦን የሚመሩት የመንግስት አካል በምስጢር እየዶለተ መሆኑን ምንጮች ጠቆሙ። በቅርቡ በአንድ ድረገፅ ላይ የወጣውን የዶ/ር ብርሃኑን ንግግር በማስረጃነት ይዘው እየተንቀሳቀሱ ያሉት አቶ በረከትና ተከታዮቻቸው በአገር ውስጥ እየተንቀሳቅሰ የሚገኘው ሰማያዊ ፓርቲ « ከግንቦት ሰባት ጋር ግንኙነት አለው፤ ከግንቦት ሰባት የገንዘብ ድጋፍ ይደረግለታል» በሚል እነበረከት ድምዳሜ ላይ መድረሳቸውን የጠቆሙት ምንጮቹ የፓርቲውን አመራሮች «ከሽብረተኛ ቡድን ጋር በመገናኘት» ብለው ለመክሰስ ሴራ እያበጃጁ መሆኑን አስውታውቀዋል። የፓርቲው አመራሮችን ከማሰር ባለፈ «ሰማያዊ ፓርቲ በሽብርተኛ ድርጅት የሚረዳ ነው» በሚል በአገር ውስጥ የሚኖረውን የፓርቲው ቀጣይ ህልውና ለማክሰም ጭምር እየዶለቱ መሆኑን ምንጮቹ ጠቁመዋል። ከበረከት በተጨማሪ ደብረፂዮን ይህንን ሴራ በበላይነት እየመከሩበት እንደሆነ ምንጮቹ አያይዘው ገልፀዋል።

Friday, August 30, 2013

ከወራት በፊት ለኃይለማርያም ደሳለኝ፣ በረከት ስምዖን፣ የሀገሪቱ ከፍተኛ ባለስልጣናት በህንዳዊ ፕሮፌሰር ሲማሩ ነበር(ተመስገን ደሳለኝ)

“በእያንዳንዱም መንግስት የሚያድሩ ብዙ ልዩ ልዩ ነገዶች ይኖሩ ይሆናል፡፡ ስለ ሆነ መንግስት አንዱን ነገድ አጥቅቶ ሌላውን ነገድ ለመጥቀም ሥራው አይደለም፡፡ አስተካክለን ካሰብን ዘንድ መንግስት መቆሙ ለሕዝቡ ሁሉ ጥቅም ነው፡፡ ጥረቱም ህዝቡን ሁሉ በትክክል ለመጥቀም ያልሆነ መንግስት ሊቆም አይችልም፡፡ ለአንዱ ነገድ ወይም ለጥቂት ሰዎች ብቻ ማድላት ለመንግስት የሚገባ ሥራው አይደለም” ይህንን መግቢያ የወሰድኩት በልዑል የኢትዮጵያ መንግስት አልጋ ወራሽ ተፈሪመኮንን ማተሚያ ቤት የካቲት 1 ቀን 1917 ዓ.ም ከታተመው የነጋ ድራስ ገብረ ሕይወት ባይከዳኝ‹‹መንግስትና የሕዝብ አስተዳደር›› መፅሀፍ ነው፤ ዛሬም ያለንበትን ዘመን ይዋጃልና፤ በተለይ ስለ‹‹ነገድ›› የተጠቀሰውን አርቀን ሰቅለን፣ ‹‹ለጥቂት ሰዎች ብቻ ማድላት›› የምትለዋን ሀረግ በወጉ ካጤንናት ለጊዜያችን በልክ የተሰፋች መሆኗን ለመረዳት አስቸጋሪ አይደለም፡፡

Thursday, August 29, 2013

የኢህአዴግን አክራሪነት ተቃውመን እንጂ ደግፈን ሰልፍ አንወጣም!!!

ሰማያዊ ፓርቲ ግንቦት 25 ቀን 2005 ዓ.ም የተለያዩ ጥያቄዎች የተነሱበት ሰላማዊ ሰልፍ አድርጎ ነበር፡፡ በሰላማዊ ሰልፉ ላይ ስለሙስሊሙ የሐይማኖት ጥያቄ፣የሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ኮሚቴዎችና የፖለቲካ እስረኞች ባፋጣኝ እንዲፈቱ፣ስለኑሮ ውድነት ወዘተ ነበር በሰልፉ ላይ የተስተጋባው፡፡ በሰልፉ ማብቂያ ላይ እንደተነገረው እነነዚህ ጉዳዮች በ3 ወር ጊዜ ውስጥ የማይመለሱ ከሆነ እንደገና የተቃውሞ ሰልፍ እንደሚጠሩ በእለቱ ኢ/ር ይልቃል ጌትነት ተናገረው ነበር፡፡ እንደቀልድ ሶስት ወሯም አልቃ የተጠየቁትም ጥያቄዎችም ሳይመለሱ ነሃሴ 26, 2005 ቀን ደረሰች፡፡

ፓሊስ የሰማያዊ ፓርቲ አመራርን ነገ ሊያነጋግር ነው

77
ሰማያዊ ፓርቲ የፊታችን እሁድ በአዲስ አበባ መስቀል አደባባይ ለጠራው የተቃውሞ ሰልፍ ፓሊስ የፓርቲውን አመራሮች በመጥራት ለነገ ሊያነጋግራቸው ቀጠሮ መያዙን ምንጮች ለኢሳት ገለጹ፡፡
ፓርቲው በበኩሉ ሊካሄድ የታቀደውን የተቃውሞ ሰልፍ በምንም አስገዳጅ ሁኔታ ሊሰርዝ እንደማይችል በጉዳዩ ላይ ያነጋገርናቸው የፓርቲው አመራሮች ተናግረዋል፡፡ምንጮች ለኢሳት እንደገለጹት ከሆነ የአዲስ አበባ ፖሊስ ነገ ከጠዋቱ ሶስት ሰዓት ላይ የሰማያዊ ፓርቲ ፀሐፊን፣ ሊቀመንበሩንና የሰልፍ አስተባባሪዎችን ለማነጋገር ጥሪ እንዳቀረበላቸው ታውቋል፡፡

“ምስጢር ያልሆኑ ምስጢራት” ‑ ድንበር ተሻጋሪው የኢሕአዴግ ዕኩይ ፕሮፖጋንዳ

ከኢትዮጵያዊ ሙስሊም
እዚህ አሜሪካ ከዋሽንግተን ዲሲ ከተማ የሚሰራጨው የኢትዮጵያ ዳያስፖራ ራዲዮ ጣቢያ በቅርቡ የሙስሊም ኢትዮጵያውያን የሃይማኖት ነፃነትና መብትን የማስከበር ሰላማዊ ትግልን ከ‹ፖለቲካዊ እስልምና› ጋር ለማያያዝ የሚቃጣ “የራዲዮ ዝግጅት” አቅርቧል፡፡ ዝግጅቱ ዊኪሊክስ በተሰኘው ድረ‑ገፅ አምና ይፋ የተደረጉ የስቴት ዲፓርትመንት ምሥጢራዊ ሰነዶችንና ከጥቂት ዓመታት በፊት በኢትዮጵያ አንዳንድ አካባቢዎች ከተከሰቱ ግጭቶች ጋር የተያያዙ የድምፅ ግብዓቶችን በመጠቀም ወቅታዊውን የኢትዮጵያውያን ሙስሊሞች የሃይማኖት ነፃነትን የማስከበር ሰላማዊ ትግል ከ‹ፖለቲካዊ እስልምና› ጋር በማያያዝ ጭቃ ለመቀባት፣ ብሎም ሙስሊም ያልሆኑ ወገኖችን ግንዛቤ ለማዛባት ይሞክራል፡፡

በብሔርተኝነት ስም ታሪክንና የኢትዮጵዊነትን መንፈስ ማጣጣል ተቀባይነት የለውም

በፍቅር ለይኩን
በአንድ ወቅት በደቡብ አፍሪካዊቷ ከተማ በኬፕታውን የሚኖር አንድ በንግድ ሥራ የሚተዳደር  ኢትዮጵያዊ ጎልማሳ አንድ አሳዛኝ ገጠመኙን እንዲህ አጫውቶኝ ነበር፡፡ ይህን ታሪኩን ያካፈለኝ ኢትዮጵያዊ ጎልማሳ የሥራ ቦታው ላይ ከአንድ ከኦሮሞ ብሔር ተወላጅ ጋር በተነሳ ጠብ በተፈጠረ ግጭት የኦሮሞ ብሔር ተወላጅ የሆነው ጓደኛውን አንድ የፊቱን ጥርሱን በቦክስ ያወልቀዋል፡፡ የጥርሱን መውለቅ የሰሙ የዚህ ሰው ጓደኞችም ተሰባስበው ይህን ሰው ካልገደልን በማለት ሲጋበዙ ነገሩ በሰላም ያልቅ ዘንድ አንዳንድ የሚያውቋቸው ሰዎች ለሽምግልና ጣልቃ ይገባሉ፡፡
በሽምግልና ድርድር ላይ እያሉም የኦሮሞ ብሔር ተወላጅ የሆነው ጓደኛውን ጥርስ ያወለቀው ሰው የአያቱ ስም የኦሮሞ ስም ሆኖ ይገኛል፡፡ እነዛም በእንዴት ተደፍረን፣ ይህን ሰው ካልገደልን በማለት ሲዝቱ የነበሩ የኦሮሞ ብሔር ተወላጆችም፣ ይኽ ሰው ለካ ወገናችን ነው በማለት ለበቀል ያነሱትን ሰይፋቸውን ወደ ሰገባው ይመልሳሉ፡፡

“በሬ ሆይ ሳሩን አየህና ገደሉን ሳታይ” እንዳይሆን እንጠንቀቅ

ቢከፍቱት ተልባ የሆነውና ላይ ላዩን ሲያዩት ልማት የሚመስለው የወያኔ ኢኮኖሚ “ልማትና እድገት” የገንዘብ ካፒታል የሚያገኘው እንደሌሎቹ በእድት እንደሚገሰግሱ ታዳጊ አገሮች የእንዱስትሪ ሸቀጥ አምርቶ ለአለም ገቢያ አቅርቦና ሽጦ አይደለም። ተሰራ የተባለው ብልጭልጭ ነገር ሁሉ የሚሰራው የድህነት ጌቶች “Lords of Poverty” በሆኑት አለም አቀፍ ተቋሞችና ሀገሮች በሚገኝ እርዳታ ነው። ወያኔ እራሱ በፈጠሩ ችግር ተሰዶ በውጭ የሚኖረው ኢትዮጵያዊም ለወዳጅ ዘመድ የሚልከው የውጭ ምንዛሬም ሌላው የወያኔ የገንዘብ ምንጭ ነው። በዚህ ላይ የሀገሪቱ የተፈጥሮ ሀብት የሆነውን ለም መሬት በገፍ ለባዕድና ለሀገር ውስጥ የወያኔ ቤተኞች በመቸብቸብ የሚገኝ ገንዘብ አለ። መቼም ኢትዮጵያዊው በገዛ ሀገሩ የኩርማን መሬት ባለርስትና መብቱ ከተነጠቀ ቆይቷል። ዛሬ ኢትዮጵያ ዉስጥ ባለርሰተቹ ወያኔና ጉጅሌዎቹ ብቻ ናቸው።

ሰማያዊ ፓርቲ በሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ ላይ ተቃውሞ አቀረበ ፓርቲው ከ33ቱ የፖለቲካ ፓርቲዎች ስብስብ ጋር ተለያየ

በግንቦት ወር 2005 ዓ.ም. የመጀመሪያውን የተቃውሞ ሠልፍ ያካሄደው ሰማያዊ ፓርቲ፣ በመጪው እሑድ በሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ በተዘጋጀው ሰላማዊ ሠልፍ ላይ ተቃውሞ አቀረበ፡፡
ሁለተኛውንና በርካታ ሰዎች እንዳሚሳተፉበት ሲገልጽ የከረመውን ሰላማዊ ሠልፍ የሚያካሄደው ነሐሴ 26 ቀን 2005 ዓ.ም. እንደነበር ፓርቲው አስታውቆ፣ የሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ በተደራቢነት በዕለቱ ሠልፍ እንደሚያደርግ ያስተላለፈው ጥሪ ትክክል አይደለም ብሏል፡፡
yiliqalየሃይማኖት ተቋማት ጉባዔ ነሐሴ 20 ቀን 2005 ዓ.ም. ያስተላለፈውን፣ ‹‹አክራሪነትና ጽንፈኝነትን እናውግዝ›› የሚል የሠልፍ ጥሪ የተቃወመው ሰማያዊ ፓርቲ፣ ከአንድ ወር በላይ በተለያዩ መገናኛ ብዙኃን ሲያስተዋውቅና ጥሪ ሲያደርግ መክረሙን ገልጿል፡፡ ከዚህም በተጨማሪ ነሐሴ 26 ቀን 2005 ዓ.ም. ሰላማዊ ሠልፍ እንደሚያደርግ ቀድሞ ማሳወቅ ለሚገባው የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር በደብዳቤ ማስገባቱን፣ የፓርቲው ሊቀመንበር ኢንጂነር ይልቃል ጌታሁን ለሪፖርተር አስረድተዋል፡፡

ህዝብ እኮ ነው!

ከበላይ
ህዝብ ሲባል ልዕልናው፣ ህዝብ ሲባል ቻይነቱ፣ ህዝብ ሲባል ቁጣው፣ ህዝብ ሲባል ሃያልነቱ ወ.ዘ.ተ. በእሳቢያችን ሊመጣብን ይችል ይሆናል፡፡ ይህ ግን በሀገሬ ኢትዮጵያ እንደ መስከረም ሰማይ ብልጭ ድርግም የሚል ክስተት እንጂ ሁሌም ህዝብ ቻይነቱ፣ ልዕልናውና ሃያልነቱ አይስተዋልም፡፡ ህዝብ በሀገሬ... የፖለቲከኞች ንግግር ማሳመሪያና ቁማር መጫዎቻ ሲሆን እንጂ ሃያልነቱን ተጠቅሞ ፖለቲከኞችንና አምባገነን መሪዎቹን ሲገራ፣ አደብ ሲያሲይዝና በልዕልናው ተመክቶ አንገቱን ቀና አድርጎ ሲንጎማለል ማየት ብርቅ ነው፡፡

በየመድረኩ የሚናገረው፣ በየጋዜጣውና መጽሔቱ የሚጽፈው ወገኔም እንደመሪዎችና ፖለቲከኞች ባይሆንም የህዝብን ሃያልነትና ልዕልና ሲደሰኩር ይሰማል፤ ክፍተቱን አድበስብሶ በማለፍም ጊዜያዊ ሙገሳ ያተርፍበታል፤ ግልብ «ጨዋነቱንም» ያሳይበታል፡፡ እናም ህዝብን ማሞካሸት እንጂ መተቸት እንደ ነውር የተቆጠረ ይመስል እምብዛም ደፍሮ ህዝብ ሲሳሳት በህዝቡ ላይ ትችት አቅራቢ አይደመጥም፡፡ ይህም የሆነው ህዝብ አይሳሳትም ከሚል የተሳሳተ አመለካከት የመነጨ ሳይሆን አይቀርም፤ ምክንያቱም ህዝብ ስለሆነ ብቻ የሚሰራው ሁሉ ልክ ነው ተብሎ ስለሚታሰብ፡፡ 

King’s legacy in the age of Obama ,Martin Luther King video

Martin_Luther_King_Jr_NYWTS
Wednesday, August 28, 2013
By Michael Eric Dyson
Aug 28 (Reuters) – When President Barack Obama delivers a speech at the Lincoln Memorial today, on the 50th anniversary of the March on Washington, he will inevitably be compared to Martin Luther King Jr., whose oration that day framed the moral purpose of the civil rights movement.

ስለ አርከበ እቁባይ! – አብርሃ ደስታ

7c196-1001168_485348238212789_1719160956_n
አብርሃ ደስታ
አቶ አርከበ ከህወሓት ጉባኤ በኋላ ከሌሎች የህወሓት አመራር አባላት ጋራ አብሮ ለመስራት ፍቃደኛ አለመሆኑንና በ አሁኑ ሰዓት ስልጣኑንና ሀገሩ ለቆ መውጣቱ ስንፅፍ እነሱ ደግሞ አቶ አርከበ የሦስተኛ ዲግሪ ትምህርቱን በለንደን እየተከታተለ መሆኑ ነገሩን።
አቶ አርከበ ትምህርት የጀመረው ከሦስት ዓመት በፊት ነበር (ከመለስ ሞት በፊት)። ይህ ሁኖ በሀገሩ እየኖረ የሚኒስተር ዲኤታ ሐላፊነቱ በአግባቡ እየተወጣ ነበር። ስለዚህ ትምህርት መጀመሩ አዲስ ነገር አይደለም።

የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤው እስከዛሬ የት ነበር? (ድምፃችን ይሰማ )

35151fd67b1e0d781375561649
August 29, 2013
መንግስት በካድሬዎቹ የማስገደድ ዘመቻ እየፈጸመለት ያለው የፊታችን እሁድ የተጠራው ሰልፍ በሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ የተጠራ መሆኑ መገለጹ ይታወሳል፡፡ ተቋሙ የሰልፉ አላማ አክራሪነትን ለማውገዝ እንደሆነ ይናገራል፡፡ ካሁን ቀደም ሲፈጠሩ በነበሩ አገራዊ ችግሮች ላይ መፍትሄ ፍለጋ ሲንቀሳቀስ እምብዛም የማይታይ ተቋም ዛሬ በድንገት የመንግስት የፕሮፓጋንዳ ዘመቻ ቅጥያ በሆነ ድርጊት ውስጥ ዘው ብሎ መግባቱ ግን ብዙ ጥያቄዎችን እያስነሳበት ይገኛል፡፡ ከጥያቁዎቹ ጥቂቶቹን ከታች እንያቸው…Ethiopian Musilms
ከሁለት አመታት ወዲህ የመንግስት ባለስልጣናት በግልጽ በሙስሊሙ ሃይማኖት ውስጥ ጣልቃ ሲገቡ ታይተው ነበር፡፡

በሀይማኖት ጉዳይ የመጣው ችግር ጊዜ የሚሰጥ አልሆነም ሲሉ አቶ በረከት ተናገሩ

ኢሳት ዜና :- የጠቅላይ ሚ/ሩ አማካሪ አቶ በረከት ስምኦን ይህን የተናገሩት በመካሄድ ላይ ባለው የሀይማኖቶች ጉባኤ ላይ ነው።
በጉባኤው ላይ የተገኙት አንዳንድ የሀይማኖት አባቶች መንግስት “ትእግስቱን አብዝቶታል፣ እርምጃ ይውሰድልን” እያሉ መጠየቃቸውን ተከትሎ፣ አቶ በረከት ” መንግስት ሀይሉ እንዳለውና መታገሱ ጠቃሚ መሆኑን” ተናግረዋል።  “ይሁን እንጅ” ይላሉ አቶ በረከት “የተፈጠረው ችግር ጊዜ የሚሰጥ አልሆነም”።

የአዲስ አበባ መስተዳድር ሰማያዊ ፓርቲ በመጪው እሁድ ሰልፍ የሚያደርግ ከሆነ፤ሰልፉ ህገወጥ ነው አለ።

ኢሳት ዜና :- ሰንደቅ እንደዘገበው በመጪው እሁድ ነሐሴ 26 ቀን 2005 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ መስቀል አደባባይ የተጠራው ሰላማዊ ሰልፍ በማወዛገብ ላይ ነው።
ቀደም ሲል ሰማያዊ ፓርቲ በዕለቱ ሰልፍ እንደሚያካሂድ ቢያስታውቅም፤ የአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጽ/ቤት በበኩሉ ነሐሴ 20 ቀን 2005 ዓ.ም በጽ/ቤቱ በሰጠው መግለጫ በተመሳሳይ ቀን ሰላማዊ ሰልፍ መጥራቱን ይፋ አድርጓል።
ይህንን ተከትሎ በፓርቲው እና የአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ “የቀደምኩት እኔ ነኝ” በማለት በመወዛገብ ላይ ሲሆኑ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሰላማዊ ሰልፍና የስብሰባ ማሳወቂያ ጽ/ቤት በበኩሉ፤ ሰልፍ እንደሚካሄድ ቀድመው ያሳወቁት የሃይማኖት ተቋማቱ በመሆኑ በዕለቱ የሰማያዊ ፓርቲ ሰልፍ የሚካሄድ ከሆነ ህገወጥ ነው ብሏል።

የጋዜጠኝነት ሙያና ፤ በውጪ ያሉ ሚዲያዎች አገልግሎት ሲገመገም

ከደምስ በለጠ
ስለጋዜጠኝነት ስናስብ የመጀመሪያው ጥያቄ የሚሆነው ጋዜጠኝነት “journalism”
፤ ምንድነው ? ጋዜጠኝነት መቼ ተጀመረ ? እንዴትስ አደገ ? የጥሩ ጋዜጠኛ መገለጫ
ባህሪዎችስ ምንድን ናቸው? የሚለው ይሆናል :: ጋዜጠኝነት የተፈፀሙ ፤ የተደረጉ
ሁኔታዎችን ፤ በጋዜጣ ስርጭት ፤ በመፅሄት ፤ በመፅሃፍ ፤ በራዲዮ ፤ በቴሌቪዥን ፤ አሁን ደግሞ በኢንተርኔት “Internet” ፤ በብሎግ ፤እና በሞባይል ሜዲያ ፤ ለብዙሃኑ አድማጭ ውይም አንባቢ ፤ ማዳረስ ነው። በመጀመርያ ጋዜጣ የሚለው የአማርኛ ቃል እንዴት ተገኘ? ጋዜጣ “gazzetta” የሚለው ቃል ከፈረንሳይኛ የተወረሰ ቢሆንም ፤ ፈረንሳዮች ያገኙት ፤ ቨኒሲያ ከምትባለው የጣሊያን ደሴት ከተማ ነው ። በቨኒሲያ የመጨረሻዋ ቅንስናሽ ሳንቲም ወይም አንድ ሳንቲም ጋዜታ “ ” “gazzetta” ትባል ነበር ። ከተማዋ በንግድ ፤በኪነ-ጥበብና በእውቀት ፤ እጅግ በልፅጋ በነበረበት ከ15ኛው እስከ 17ኛው መዕተ-አመታት ፤ በከተማዋ በዚች ቅንስናሽ ሳንቲም የምትሸጥ የዕለቱን ወሬ ይዛ የምትወጣ ሌጣ ወረቀት ነበረች ።“gazeta de la novita” ትባል ነበር፤ የአንድ ሳንቲም ዜና እንደማለት ነው።

Wednesday, August 28, 2013

ማን ይናገር የነበረ..... የታኅሣሡ ግርግር እና መዘዙ!

(በሰልሞን ተሰማ ጂ.) http://semnaworeq.blogspot.com
Email: solomontessemag@gmail.com
ዕዴሌ አጋጣሚ፣ ሇሰው ሌጅ ስትመጣ፣
መሌካምና ክፉ፣ አሊት ሁሇት ጣጣ !!!
(ከበዯ ሚካኤሌ፣ “የዕውቀት ብሌጭታ”፤)
የታኅሣሥ 1953ቱን (ዒ.ም) “ሥዑረ-መንግሥት” ዋዜማ፣ መባቻና ማግስት
ያካተተ መጽሏፍ ታትሟሌ፡፡ የመጽሏፉ ዯራሲ፣ አቶ ብርሃኑ አስረስ ሲሆኑ፣
አሳታሚው ዯግሞ የአዱስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ፕሬስ ነው፡፡ የመጽሏፉ ርዕስ፣
“ማን ይናገር የነበረ.....፣ የታኅሣሡ ግርግር እና መዘዙ” የሚሰኝ ሲሆን፣
በ2005 ዒ.ም ሇመጀመሪያ ጊዜ አዱስ አበባ ሊይ ታትሟሌ፡፡ ይኼንን
የሚያህሌ ቁምነገረኛ መጽሏፍ በ144.00 (አንዴ መቶ አርባ አራት) ብር
ገዝቶ ቁምነገር መዝረፍ ያጓጓሌ፡፡ ገጽ በገጽ ሲገሌጡት ከ እሰከም ስሇላሇው
ነፍስን በሃሴት ያጭራሌ፡፡ አንዴ ጊዜ ብቻ አንበውት የማያሌቅ ሃተታ የያዘ
ዴንቅ ዴርሳን (Masterpiece) ነው፡፡ ዴርሳኑን ዯጋግሞ ማንበብ እውነትን
የበሇጠ ማወቅ ነው፡፡ “ዴንቅ የሆነ ዴርሳን” ነው ያሌኩት ሇማጋነን
አይዯሇም፡፡ በእርግጥም፣ ውብ ነው! እጹብ ዴንቅ ነው!....

የእኛ “መንግስት” (ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ)

“በእያንዳንዱም መንግስት የሚያድሩ ብዙ ልዩ ልዩ ነገዶች ይኖሩ ይሆናል፡፡ ስለ ሆነ መንግስት አንዱን ነገድ አጥቅቶ ሌላውን ነገድ ለመጥቀም ሥራው አይደለም፡፡ አስተካክለን ካሰብን ዘንድ መንግስት መቆሙ ለሕዝቡ ሁሉ ጥቅም ነው፡፡ ጥረቱም ህዝቡን ሁሉ በትክክል ለመጥቀም ያልሆነ መንግስት ሊቆም አይችልም፡፡ ለአንዱ ነገድ ወይም ለጥቂት ሰዎች ብቻ ማድላት ለመንግስት የሚገባ ሥራው አይደለም” ይህንን መግቢያ የወሰድኩት በልዑል የኢትዮጵያ መንግስት አልጋ ወራሽ ተፈሪመኮንን ማተሚያ ቤት የካቲት 1 ቀን 1917 ዓ.ም ከታተመው የነጋ ድራስ ገብረ ሕይወት ባይከዳኝ‹‹መንግስትና የሕዝብ አስተዳደር›› መፅሀፍ ነው፤ ዛሬም ያለንበትን ዘመን ይዋጃልና፤ በተለይ ስለ‹‹ነገድ›› የተጠቀሰውን አርቀን ሰቅለን፣ ‹‹ለጥቂት ሰዎች ብቻ ማድላት›› የምትለዋን ሀረግ በወጉ ካጤንናት ለጊዜያችን በልክ የተሰፋች መሆኗን ለመረዳት አስቸጋሪ አይደለም፡፡

የሕወሐት ባለስልጣናት የአሜሪካ ቆይታ፤ የከዱ አሉ

ከኢየሩሳሌም አርአያ
በአባይ ወልዱ የሚመራውና ሰባት ከፍተኛ የሕወሐት ባለስልጣናት የተካተቱበት ቡድን በአሜሪካ አራት ከተሞች ባካሄደው ስብሰባ በተለይ በላስቬጋስ ጠንካራ ተቃውሞ እንደገጠመው በስፍራው የተገኙ ምንጮች አስታወቁ። ቡድኑ በዋሽንግተን ኢትዮጲያ ኤምባሲ በጀመረውና በመቀጠል በላስቬጋስ፣ ሲያትልና ካሊፎርኒያ ከተሞች ባካሄደው ስብሰባ “አላማ” አድርጎ የያዛቸው ጉዳዮች እንደነበሩ የጠቆሙት ምንጮች፣ እነሱም፥ “የመለስ ፋውንዴሽን፣ የአባይ ግድብና የ40/60 የቤቶች ግንባታ.” ሲሆኑ፣ ለነዚህ ማስፈፀሚያ “ገንዘብ አዋጡ” የሚለው ዋናው ግብ እንደነበር አስረድተዋል።

ድሬዳዋና ሞቃዲሾ ሁለት የኢትዮጵያ አውሮፕላኖች ተከሰከሱ


የኢትዮጵያ ሚሊታሪ አቪየሽንና የኢትዮጵያ ኤየር ሀይል ከሁለት ሳምነት በፊት ድሬዳዋና ሞቃዲሾ የወደቁትን ሁለት አውሮፕላን አደጋዎችን እየመረመሩ እንደሆነ ለሪፖርተር የውስጥ አዋቂወች አስታዎቁ፡፡ ከኢትዮጵያ ሚሊታሪ አቪየሽንና ከኢትዮጵያ አየር ሀይል የተመረጡ የአደጋው ምክንያት አጣሪዎች አደጋው ወደተከሰተበት ቦታ መላካቸውም ተጠቅሷል፡፡
የመጃመሪያው አደጋ ኦገስት 6 ሲ130(ኤል100) የተባለ የጦር አውርፕላን ድሬዳዋ አለም አቀፍ አየር መንገድ ላይ ሲከሰት ሁለቱ ተሳፋሪዎችም ቀላል አደጋ አጋጥሟቸዋል፡፡ የአውሮፕላኑ ፓይለት የነበሩትም ኮሎኔል ሰለሞን ሲሆኑ የተጎዱት ሁለቱ ተሳፋሪዎች አዲስ አበባ በሚገኘው ጦር ሁይሎች ሆስፒታል ህክምና እየተደረገላቸው ይገኛል፡፡

ህዝበ-ሙስሊሙን ያለአግባብ በስጋት መፈረጅ፤ ማዋከብና መግደል በአፋጣኝ ይቁም!

የነፃነት ጐህ
የኢትዮጵያ ህገ-መንግስት አንቀጽ 11 ቁጥር 3 ”መንግስት በሀይማኖት ጉዳይ ጣልቃ አይገባም፤ ሀይማኖትም በመንግስት ጉዳይ ጣልቃ አይገባም ” ይላል፡፡በሀገራችን ከንጉሱ ዘመን ጀምሮ በወታደራዊው ደርግ እንዲሁም አሁን ስልጣን ላይ ባለው ወያኔን ጨምሮ ሁሉም ሀይማኖቶች ከመንግስት ጣልቃገብነት ነፃ ሆነው አያውቁም። ፍትህ፣ ነጻነት፣ እኩልነት እና አንድነት ለብዙ ሀይማኖቶች መሰረታዊ እሴቶች ናቸው፡፡ እነዚህ እሴቶች ላለፉት 22 ዓመታት በዘረኛው የወያኔ መንግስት እየተሸረሸሩ እና እየተመናመኑ ዛሬ ከነአካቴውም ለመጥፋት ተቃርበዋል፡፡ ስለመሰረታዊ የሰው ልጅ መብት እና ነጻነት እንዳይወራ የወያኔ የጥይት አፈሙዞች በእያንዳንዱ ሰው እና የህዝብ አገልግሎት መስጫ ተቋማት ላይ ተደቅኗል፡፡የእምነት ቦታዎችንም ሳይቀር በመድፈር ህዝበ-ምዕመኑ የኔ የራሴ የሚለው የአምልኮ ቦታ እና የአምልኮ ስርዓት እንዳይኖረው እያደረገ ነው።

የዱርየው ወያኔ መንግሥት የውሸት አምራች ፋብሪካዎች ይዘጉ

ተሾመ ደባለቄ
‘የሌባ ዓይነ ደረቅ መልሶ ልብ ያድርቅ’ ሲል የሀገሬ ሰው ሀገር ያወቀውን ፀሐይ የሞቀውን ሌባ ጨዋ ለማስመሰል የሚያጋጋው ውሸት ሲያሰለች ነው። እንደዚሁም መንግሥት ነኝ ተባዩ ወያኔም የውሸት ጋጋታው ሰውን አሰልችቶት እውነትም ቢናገር እነኳን የሚያምነው አጥቶ ሙጥኝ የያዛቸው መዋቅሮች ‘ውሸታም’’ ና  ‘ሌባ’ የሚል ስም አትረፈዋል።
ውርደት ያተረፈው ወያኔ የውሸት ጋጋታው አልበቃ ብሎት ለምን እውነት ተነገረ ብሎ ድርጅት መዘጋት ባልደረቦችን ማሳደድ፣ ማሰርና  እስከመግደል ደረጃ ደርሷል። በራሱ ውሸት ያበደው ወያኔ በአካባቢው ከሚያጎበድዱለት ጉጅሌዎቹ መሃል አብደሃል በሙስና ተዘፍዝፈሃል የሚለው ጠፍቶ እንደመሸበት ሰካራም ቤቱ ጠፍቶት በየሰዉ ቤት እያንኳኳ በራሱ ውሸት ተሸብሮ ህዘብን ማሸበሩን ቀጥሎበታል።

አቶ አርከበ ወዴት ናቸው?! abraha desta

ባለፈው የህወሓት ጉባኤ ባለስልጣናቱ በሁለት እንደተከፈሉና በነአባይ ወልዱ የሚመራው የትግራይ ቡድን በነአርከበ (ወይ ደብረፅዮን) ለሚመራው የአዲስ አበባው ቡድን ማሸነፉ ጠቅሼ ነበር። የነአርከበ ቡድን በህወሓት አመራር ምርጫ ቅሬታ ነበረው።

አንድነት በሮቤ ከተማው ሰላማዊ ሰልፍ እንግልት ገጠመኝ አለ

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት) በባሌ ሮቤ ከተማ ሰላማዊ ሰልፍ ለማድረግ ባቀደው ፕሮግራም ላይ ከፍተኛ እንግልት እንደገጠመው ገለፁ።
ፓርቲው ባወጣው መግለጫ ነሐሴ 13/2005ቱ ሰላማዊ ሰልፍ ቀስቃሾች ፖስተር እና በራሪ ወረቀት በሚለጥፉበት ወቅት መታገዳቸውን ገልጿል። እንደ መግለጫው ከሆነ ቀስቃሾቹ ነሐሴ 18 ቀን 2005 ዓ.ም ጀምሮ እስከ 19 ቀን 2005 ዓ.ም ድረስ ከነመኪናቸው ከቆሙበት እንዳይንቀሳቀሱ ተደርጓል። ከዚህ በተጨማሪም የሀገር ሽማግሌዎች እኛን ሳታነጋግሩና ሳንፈቅድላችሁ ሰላማዊ ሰልፍ ማድረግ የለባችሁም እንዳሏቸው ገልፀዋል።

አንድነት ፓርቲ በአሜሪካ ኤምባሲ ቅር መሰኘቱን ገለፀ

በዘሪሁን ሙሉጌታ

አንድነት ለዲሞክራሲ ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) በኢትዮጵያ የአሜሪካ ኤምባሲ ላይ ቅር መሰኘቱን ገለፀ። ፓርቲው በኤምባሲው ላይ ቅሬታውን የገለፀው የፓርቲው የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊና የስራ አስፈፃሚ አባል የሆነው ወጣት ዳንኤል ተፈራ ለፓርቲው የስራ ጉዳይ ለአንድ ወር ወደ አሜሪካ እንዳይሄድ በመደረጉ ነው።
የፓርቲው ሊቀመንበር ዶ/ር ነጋሦ ጊዳዳና ወጣት ዳንኤል ተፈራ በጋራ ለሰንደቅ ጋዜጣ እንደተናገሩት ኤምባሲው ቪዛ በመከልከሉ የፓርቲውን ስራ መስተጓጎሉን ተናግረዋል።
ወጣት ዳንኤል ወደ ዋሽንግተን ለማቅናት ግብዣ የቀረበው አሜሪካን ሀገር በሚገኙ የፓርቲው ድጋፍ ሰጪ ቻፕተሮች አማካኝነት ሲሆን በቅርቡ ፓርቲው የጀመረው ‘‘የሚሊዮኖች ድምፅ ለነፃነት’’ የተባለውን ሕዝባዊ ንቅናቄ በአሜሪካን ተገኝቶ ገለፃ እንዲያደርግና ድጋፍ የማሰባሰቡን ተግባር ለማጠናከር ነበር።

በመስቀል አደባባይ የተጠራው ሰላማዊ ሰልፍ እያወዛገበ ነው ‘‘ቀድመን ሰልፍ የጠራነው እኛ ነን’’ ሰማያዊ ፓርቲ


‘‘የቀደምነው እኛ ነን’’

የአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ
‘‘ሰማያዊ ፓርቲ በዕለቱ የሚያካሂደው ሰልፍ ህገ-ወጥ ነው’’
የአ.አ ከተማ አስተዳደር የሰላማዊ ሰልፍ፣ የስብሰባና የማኀበራት ፈቃድ ጽ/ቤት

በዘሪሁን ሙሉጌታ

በመጪው እሁድ ነሐሴ 26 ቀን 2005 ዓ.ም በአዲስ አበባ ከተማ መስቀል አደባባይ የተጠራው ሰላማዊ ሰልፍ በማወዛገብ ላይ ነው። ቀደም ሲል ሰማያዊ ፓርቲ በዕለቱ ሰልፍ እንደሚያካሂድ ቢያስታውቅም፤ የአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ ጽ/ቤት በበኩሉ ነሐሴ 20 ቀን 2005 ዓ.ም በጽ/ቤቱ በሰጠው መግለጫ በተመሳሳይ ቀን ሰላማዊ ሰልፍ መጥራቱን ይፋ አድርጓል።
ይህንን ተከትሎ በፓርቲው እና በአዲስ አበባ የሃይማኖት ተቋማት ጉባኤ መካከል የቀደምኩት እኔ ነኝ በማለት በመወዛገብ ላይ ሲሆኑ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የሰላማዊ ሰልፍና የስብሰባ ማሳወቂያ ጽ/ቤት በበኩሉ፤ ሰልፍ እንደሚካሄድ ቀድመው ያሳወቁት የሃይማኖት ተቋማቱ በመሆኑ በዕለቱ የሰማያዊ ፓርቲ ሰልፍ የሚካሄድ ከሆነ ህገወጥ ነው ብሏል።

የወያኔ መንግስት የግንቦት 7 ቡድን አባላት ናቸው ብሎ የጠረጠራቸው ላይ ክስ መሰረተ

የግንቦት 7 አሸባሪ ቡድን አባላት ናቸው በሚል የተጠረጠሩ 10 ግለሰቦች ክስ ተመሰረተባቸው ።
ተከሳሾቹ ዘመኑ ካሳ በዕውቄ የግንቦት ሰባት ልዩ ሃይል ታጣቂ ፣ አሸናፊ አካሉ አበራ ፣ ደህናሁን ቤዛ ስመኝ ፣ ምንዳዬ ለማ ፣ አንሙት የኔዋስ አለኽኝ ፣ሳለኝ አሰፋ ወንድምአገኝ ፣ የአማራ ክልል የማረሚያ ቤት ረዳት ሽፍት መሪ ምክትል ኢንስፔክተር ሙሉዬ ማናዬ ረታ፣ፀጋው ካሳ እንየው ፣ የአለም አካሉ አበራ እና ሙሉ ሲሳይ መቆያ የተባሉ ተጠርጣሪዎች  ናቸው ።

ግልጽ ደብዳቤ ለሰማያዊ ፓርቲ አመራር አባላት – አማኑኤል ዘሰላም

ለተከበሩ ኢንጂነር ይልቃል፣ ለክቡራን ከፍተኛ የሰማያዊ ፓርቲ አመራር አባላት፣ በቅድሚያ ሰላምታዬ ባላችሁበት ቦታ ይድረሳችሁ! ጤና ይስጥልኝ።
ለሰማያዊ ፓርቲ አድናቆት አለኝ። የግራዚያኒ ሃዉልትን በመቃወም ያደረጋችሁት ሰልፍን ተከታትያለሁ። በብዛት ግን ሰው ያወቃችሁ፣ በአዲስ አበባ በጠራችሁት ሰላማዊ ሰልፍ ነዉ። ያኔ ትልቅ ሥራ ነው የሰራችሁት። አኩርታችሁኛል። ብዙ ደጋፊዎችም በአጭር ጊዜ ዉስጥ አግኝታቹሃል።
ያኔ የጠራችሁትን ሰልፍ አብዛኞቻችን ብንደግፈውም፣ ሌሎች ድርጅቶችን ሳታማክሩ ፣ ሰልፉን በችኮላ መጥራታችሁ ግን ብዙዎችን ደስ አላሰኝም ነበር። ነገር ግን «ማንም ይጥራዉ፣ ማንም ፣ ትግሉን እስከጠቀመ ድረስ መተባበር ያስፈልጋል» የሚል አቋም በርካታ የአንድነት ፓርቲና መኢአድ አመራር አባላት በመያዝ ድጋፍ ሰጧችሁ።

Tuesday, August 27, 2013

መንግሥት ለተፈጠረው ችግር በአስቸኳይ ማስተካከያ እንዲያደርግ እንጠይቃለን!!!!

መንግሥት ለተፈጠረው ችግር በአስቸኳይ ማስተካከያ
እንዲያደርግ እንጠይቃለን!!!!
ከሰማያዊ ፓርቲ የተሰጠ መግለጫ
ፓርቲያችን ሰማያዊ በህገ መንግሥቱ በተደነገገው ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ መብቱን ተጠቅሞ ለመንግሥት ጥያቄዎችን በማቅረብ ግንቦት 25/2ዐዐ5 ዓ/ም. ታላቅ ህዝባዊ ተቃውሞ ሰልፍ በተሳካ ሁኔታ አድርጓል፡፡
መንግሥት ላቀረብናቸው ጥያቄዎች በሦስት ወር ውስጥ መልስ የማይሠጥ ከሆነ በተጠናከረና በተደራጀ መልኩ ጥያቄያችንን በድጋሚ በህዝባዊ ተቃውሞ ሰልፍ እንደምናቀርብ በግንቦት 25/2ዐዐ5 ዓ/ም. በተደረገው ሠልፍ ላይ ለህዝብ ቃል በገባነው መሠረት ነሃሴ 26/2ዐዐ5 ዓ/ም. በድጋሚ ሰልፍ ጠርተን አስፈላጊውን ዝግጅት እያደረግን መሆኑን ለህዝብ በልዩ ልዩ መገናኛ ዘዴዎች ገልፀናል፡፡
ከዚህ በተጨማሪም ለሰልፉ በሰላም መጠናቀቅ አስፈላጊው ትብብር እንዲደረግልን አዋጁ በሚጠይቀው መሠረት ለአዲስ አበባ መስተዳድር ስብሰባና ሰላማዊ ሰልፍ ማሰወቂያ ክፍል ጉዳዩን እንዲያውቀው አድርገናል፡፡

የመብት ህጎች እና ድንጋጌዎች የተቆለሉባት ግን የቤት ስራዋ የደቆሳት ሃገር

ምንሊክ ሳልሳዊ 

ታዋቂነታችን በድርቅ በድህነት ብሎም በጭፍጨፋ ደሞ በሰብኣዊ መብት ጥሰት
የሕወሓት መራሹ ጁንታ ወደ ስልጣን በጠበንጃ ሃይል ከመጣ ጀምሮ በአለም አቀፍ ደረጃ የተደነገጉ የሰባዊ መብት ህጎችን ካለምንም ማርቅርቅ እና ድካም ከሌሎች በመገልበጥ በወረቀት ላይ ከማስፈሩም በተጨማሪ ጥናቶች እንደሚጠቁሙት በአለም ላይ የሰው አገር ህግን እና አለማቀፍ ድንጋጌን ከሃገራችን ሁኔታ ጋር ሳይገናዘቡ በስፋት በደመነፍስ ለፍጆታ የተጻፈበት ሃገር ኢትዮጵያ ብቻ ሲሆን በየትኛውም አለም ሃገራት ያልተከሰተ የአለም አቀፍ ህጎችን ግልባጭ በከፊል በህገመንግስት እንዲሁም የገዢ ፓርቲን የፖለቲካ ፕሮግራም በከፊል ደባልቆ በጋር እንደ አውራ ህግ የወጣባት ሃገር ብትኖር ኢትዮጵያ ብቻ ናት::ኢትዮጵያ በታሪኳ ታይቶ በማይታወቅ ደረጃ የመብቶች ሕጋዊነት በተጨበጨበለት ሁኔታ እና ይህ በማይባል ደረጃ የተደነገጉባት አገር ነች፡፡ እንግዲህ ይህ ሆኖ እያለ ነው በአገሪቱ የመብቶች ጥሰት ጉዳይ ከአገሪቱ ብሔራዊ አነታራኪ ፖለቲካዊ አጀንዳነት አልፎ ዓለም አቀፍ አጀንዳ ሆኖ ተገኝቷል፡፡

የአቶ ተኮላ ጽሁፍ ትችት ወይንስ ሽሙጥ

ከሳᎀኤል ሽፈራው/ዳላስ
አቶ ተኮላ መኮነን በአቶ ነሲቡ የመጽሀፍ ትችት ላይ ላቀረቡት ሽሙጥ አስተያየት ለመስጠት ነው።ግለሰቡ ለነሲቡ ከመጀመሪያው አረፍተነገር ነበር ትችታቸውን የጀመሩት። እኔ የሳቸውን ሽሙጥ ከመጨረሻ መደምደሚያ አረፍተነገር እጀምራለሁ። አቶ ተኮላ “ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር” ብለው በነሲቡ ላይ የወረወሩትን ሽሙጥ ዘጉ። እኔም ይህ መዝጊያ ቃላቸውን ሳይ በግርምት ይህን አስተያየቴን ለማቅረብ ተገደድሁ።
ለዚህ መጣጥፍ መነሻ የሆነኝ አቶ ነሲቡ ለራሳቸው ለተወረወረባቸው ሽሙጥ መልስ ያጣሉ ብዬ ሳይሆን። በሰሞኑ ተከታታይ በወጡ መጻሕፍት፤ ለፅሀፊወቹ ምስጋና ይግባቸውና በዚህ መንግስት ደጋፊወች ከመጽሀፍቱ በጣም ትንሹን ክፍል አጉልተው ለማሳየት ያደረጓቸው ሙከራወች ሁሉም ሰው ተገንዝቦ መልስ እንደሚገባቸው ስላሳሰበኝ የግል አስተያየቴን ለመስጠት ነው። እናም የአቶ ተኮላ መኮነንን “ትችት” እንደኔ ሽሙጥም የዚሁ የሕወሐት/ኢሕአዴግ ደጋፊወች ሰሞነኛ ተግባር አካል በመሆኑ፤ ቃል በቃል አስተያየት ለመስጠት ሳይሆን ጠቅለል ባለ መልኩ ለማመላከት አሰብሁ። አቶ ተኮላ በተለያዩ የሕወሐት/ኢሓዴግ ስብሰባወች በዳላስ አካባቢ የተደረጉትን በመሪነትና አስተናባሪነት የሚያገለግሉ ሲሆኑ።

4 ለ 3 በጸረ ሽብርተኝነት አዋጅ ላይ የተደረገ ክርክር

አንድነት ፓርቲ የጸረ ሽብርተኝነት አዋጁን በህዝብ ድጋፍና ጥያቄ ለማሰረዝ የጀመረው ህዝባዊ ንቅናቄ የሚፈለገውን ግብ ለመምታቱ በገዢው ፓርቲ ቁጥጥር ስር የሚገኘው ኢቴቪ በአዋጁ ዙሪያ የፓርቲዎችን አቋም የሚያንጸባርቅ መድረክ ማዘጋጀቱ ማሳያ ነው፡፡ኢህአዴግ ካድሬዎቹ አዋጁን በማንበብ አንድነቶች ለሚያነሱት መከራከሪያ ምላሽ ለመስጠት እንዲችሉ ትዕዛዝ ማውረዱም ሌላኛው የአደባባይ ድል ነው፡፡
በነቢብ የህዝብ በገቢር የኢህአዴግ ልሳን የሆነው ኢቴቪ በአዋጁ ላይ ያላቸውን አቋም እንዲያንጸባርቁ የጋበዛቸው የፖለቲካ ፓርቲዎች መድረክ በአቶ በቀለ ነጋዓ፣አንድነት በሃብታሙ አያሌው፣ኢዴፓ በሙሼ ሰሙ፣ሰማያዊ በይልቃል ጌትነት፣ ኢህአዴግ በሽመልስ ከማል፣በጌታቸው ረዳና በኢቴቪው ጋዜጠኛ ተወክለዋል፡፡

ሰበር ዜና “ወልቂጤ በፌደራል መንግስት ቁጥጥር ስር ዋለች”

“ወልቂጤ በፌደራል መንግስት ቁጥጥር ስር ዋለች”
የወልቂጤ ከተማ ፍትሕና ፀጥታ ቢሮ እና የከተማችን ደህንነት ቢሮዎች የህዝበ ሙስሊሙን ሰላማዊ የመብት ጥየቃ ጉዞን መግታት አልቻላቹምበሚል እጃቸውን እንዲያወጡ ተደርጎ በአሁኑ ሰዓት በሙስሊሞች ወቅታዊ ጉዳይ ክትትል ሙሉ በሙሉ ለፌደራል ደህንነቱ አቶ “ከድር ሽኩር” ለተባለው ግለ ሰብ መተውና ከፌደራሉ ዋና መስራያ ቤት በተላኩለት ፌደራል ወታደሮች በመታገዝ የከተማችንን ሙስሊም ወጣቶች እያሰሰ ወደ ወህኔ እየጣለ ይገኛል ።

ከወራት በፊት ለኃይለማርያም ደሳለኝ፣ በረከት ስምዖን፣ የሀገሪቱ ከፍተኛ ባለስልጣናት በህንዳዊ ፕሮፌሰር ሲማሩ ነበር(ተመስገን ደሳለኝ)

“በእያንዳንዱም መንግስት የሚያድሩ ብዙ ልዩ ልዩ ነገዶች ይኖሩ ይሆናል፡፡ ስለ ሆነ መንግስት አንዱን ነገድ አጥቅቶ ሌላውን ነገድ ለመጥቀም ሥራው አይደለም፡፡ አስተካክለን ካሰብን ዘንድ መንግስት መቆሙ ለሕዝቡ ሁሉ ጥቅም ነው፡፡ ጥረቱም ህዝቡን ሁሉ በትክክል ለመጥቀም ያልሆነ መንግስት ሊቆም አይችልም፡፡ ለአንዱ ነገድ ወይም ለጥቂት ሰዎች ብቻ ማድላት ለመንግስት የሚገባ ሥራው አይደለም” ይህንን መግቢያ የወሰድኩት በልዑል የኢትዮጵያ መንግስት አልጋ ወራሽ ተፈሪመኮንን ማተሚያ ቤት የካቲት 1 ቀን 1917 ዓ.ም ከታተመው የነጋ ድራስ ገብረ ሕይወት ባይከዳኝ‹‹መንግስትና የሕዝብ አስተዳደር›› መፅሀፍ ነው፤ ዛሬም ያለንበትን ዘመን ይዋጃልና፤ በተለይ ስለ‹‹ነገድ›› የተጠቀሰውን አርቀን ሰቅለን፣ ‹‹ለጥቂት ሰዎች ብቻ ማድላት›› የምትለዋን ሀረግ በወጉ ካጤንናት ለጊዜያችን በልክ የተሰፋች መሆኗን ለመረዳት አስቸጋሪ አይደለም፡፡

የኢህአዴግ ስውር ሴራ በሮቤ ከተማ ተጋለጠ!!! ሐገሪቷን የሚያስተዳድራት ማነው? የባሌ ሮቤ ሰላማዊ ሰልፍ ለምን ተደናቀፈ? -አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትሕ ፓርቲ (አንድነት)

ከአንድነት ለዲሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ (አንድነት) የተሰጠ ማብራሪያ
የሚሊየኖች ድምፅ ለነፃነት ንቅናቄ በአራቱም የኢትዮጵያ ማዕዘናት የነፃነት ድምፅ ማስተጋባት ከጀመረ እንሆ ዛሬ ስልሳ ሰባተኛ(67) ቀኑን ይዟል፡፡ ፓርቲያችን በእዚህ ታላቅ ሕዝባዊ የነፃነት ንቅናቄ መሪር የሆነ ውድ ዋጋ እየከፈለ ድምፅ አልባ ለሆኑት ሚሊዮኖች ኢትዮጵያውያን ድምፅ በመሆኑ ታላቅ ደስታ ይሰማዋል፡፡
ላለፋት ስምንት ዓመታት ሰቆቃ እና ግፍ በገዢዎቻችን ሲፈፀምበት የኖረው የገጠሩም ሆነ የከተማው ታላቁ ህዝባችን ‹አንድነት ፓርቲአችን አስትንፋሳችን› በማለት አንድነት ፓርቲ ባመቻቸለት ህዝባዊ ስብሰባዎች እና ሠላማዊ ሠልፎች በነቂስ በመውጣት የታፈነ ብሶቱን በግልፅ በአደባባይ ላይ በማሰማቱ ኢህአዴግ እና ህዝቡ ዛሬም ድረስ ተለያይተው እንዳሉ አንድነት ፓርቲ በማያወላዳ ሁኔታ በሚሊዮኖች ድምፅ ንቅናቄ በህዝባችን መሀል በመገኘት አረጋግጧል፡፡

የአንድነቶች ሰላማዊነት ጽናት በባሌ ሮቤ እና በፍቼ ኦሮሚያ!

ግርማ ሞገስ (girmamoges1@gmail.com)
ሰኞ ነሐሴ 20 ቀን 2005 ዓ.ም.
“አንድነት ፓርቲ ሳይገድል እየሞተ ህገ-መንግስቱን የማስከበር ሰላማዊ ትግሉን አጠንክሮ ዛሬም ወደፊትም ይቀጥላል፡፡” የሚለውን መርሃቸውን አንድነቶች ካስተዋወቁን ከርመዋል። ባለፈው ሳምንት በባሌ ሮቤ እና በፍቼ ኦሮምያ የተተከሉት መረን የለቀቁ አምባገነን አስተዳደሮች እና ደህንነቶች የፈጸሙባቸውን ወደር የለሽ የአንደበት፣ የሳይኮሎጂ እና የአካል ጥቃት በፈገግታ በመቀበል እየሞቱ ሳይገድሉ በሰላማዊ ትግል ህገ-መንግስቱን ለማስከበር ያላቸውን ጽናት ደግመው አሳይተውናል አንድነቶች። አንድነቶች የሚሰብኩትን የሚፈጽሙ መሆናቸውን ኢትዮጵያ እንደገና ባለፈው ሳምንት ተመልክታለች። የባሌ ሮቤ እና የፍቼ አምባገነን አስተዳዳሪዎች እና ደህንነቶች አረመኔነት አሳፋሪ ነበር። በፍጹም የስልጣኔ አየር የነፈሰባቸው አይመስሉም። ዘመናዊ አስተሳሰብ ለአንድ ቀንም የጎበኛቸው አይመስሉም። ይባስ ብሎ የባሌ ሮቢ እና የፍቼ አስተዳዳሪዎች እና ደህንነቶች ከህጋዊ የመንግስት መዋቅር ውጪ ጸረ-ነፃነት ወረበሎች (ቦዘኔዎች) ያደራጁ ይመስላሉ። ይኽ ጉዳይ ጥናት ሊደረገበት ይገባል።

መንግስት ለመጪው እሁድ ሰልፍ ጠራ! (ድምፃችን ይሰማ)

ለተሳታፊዎች ዳጎስ ያለ አበል ተዘጋጅቷል!
የግል ድርጅት ሀላፊዎች ከእነ መኪናቸውና ሰራተኞቻቸው በሰልፉ እንዲገኙ ግዳጅ ተጥሎባቸዋል!
መንግስት በመጪው እሁድ ሰልፍ ሊያካሄድ ነው፡፡ መንግስት በክልሎች ሲያካሄድ ያቆየውን ይህንኑ የግዳጅ ሰልፍ በአዲስ አበባ ለማድረግ ለወራት ከፍተኛ ዝግጅት ሲያካሄድ ቆይቷል፡፡ የፊታችን እሁድ በአዲስ አበባ ለማካሄድ የታሰበው ሰልፍ በዋነኝት ሙስሊሙ ህብረተሰብ ያነሳውን የእምነት መብት ጥያቄ በክራሪነት ለመወንጀልና ‹‹ሕዝቡ መንግስት እርምጃ ይውሰድልን›› አለ በሚል ለሚዲያ ፍጆታ ለመጠቀም ነው፡፡Ethiopian Musilms
በዚህ ሰልፍ በርካታ ሰው እንዲገኝ ለማድረግ ያስችል ዘንድ የመንግስት ሰራተኞች፣ የፓርቲ አባላት፣ የሴቶች ሊግ፣ የወጣቶች ሊግ እንዲሁም በጥቃቅን እና አነስተኛ የተደራጁ ማህበራት አባሎች፣ በኮብል ስቶን የሰለጠኑ ወጣቶች እንዲገኙ የግዳጅ መመሪያ ተላልፏል፡፡ እነዚህ የተጠቀሱ ሁሉ በሰልፉ ላይ ለመገኘት ፊርማቸውን እንዲያኖሩ በዚሁ ሳምንት ሊጠየቁ እንደሚችሉ ምንጮች ጠቁመዋል፡፡

ኢሕአዴግ እሁድ በአ.አ ሰላማዊ ሰልፍ ጠራ፤ ድምጻችን ይሰማ “መንግስት ሙስሊሙን እየዘለፈ ነው” አለ

 (ዘ-ሐበሻ) የኢትዮጵያ ቴሌቭዥን ዛሬ እንደዘገበው “አክራሪዎች በእምነት ስም የህዝብን ሰላም ለማደፍረስ የሚያደርጉትን እንቅስቃሴ በመቃወም እሁድ ነሃሴ 27/2005 ሰላማዊ ሰልፍ እንደሚያደርግ የአዲስ አበባ የሀይማኖት ተቋማት ጉባኤ ገለፀ” ብሏል። በሌላ በኩል ድምጻችን ይሰማ “አክራሪነትን ለመዋጋት ተብለው በተዘጋጁ ስብሰባዎች ጸረ እስልምና የሆኑ ዘለፋዎች እተበራከቱ ነው!” ሲል ተቃውሞውን አሰማ።
ኢሕአዴግ የፊታችን እሁድ በአዲስ አበባ የጠራው ሰልፍ ሁሉም የሀይማኖት ተከታዮች በሰላም አብሮ ለመኖር ያላቸውን ቁርጠኝነት ማሳያ ነው ሲል ድምጻችን ይሰማ በበኩሉ “ለእስልምና ጥላቻ ያላቸው የመንግስት ሃላፊዎችና ካድሬዎች አጋጣሚውን የእስልምናን ሃይማኖት ለማራከስ ተግባር እያዋሉት ነው” ብሎታል።

ኢሕአዴግ ሆይ፤ በህግ አምላክ! ሕግ ይግዛክ!!

ቀጥሎ የሚታዩዋቸው ግለሰብ የመ/አ መሰቦ ማዳልቾ ይባላሉ፡፡ በደቡብ ክልል ጋሞ ጎፋ ዞን ከቁጫ ሕዝብ ጥያቄ ማለትም ከፍትህ/ከመልካም አስተዳደር፤ ከማንነት/ከብሔር እና ከልማት ጥያቄ ጋር በተያያዘ ዛሬ በአርባ ምንጭ ወህኒ ቤት ይገኛሉ፡፡
1185279_556267574441149_1239414489_n
እርሳቸውን በሚያውቁት ዘንድ ተወዳጅ፤ ከማያውቁት ዘንድ ቶሎ ተግባቢ፤ በአጠቃላይ በአቀራረባቸው ትሁቱ፤ በባሕርያቸው መካሪና አስታራቂ፤ እንዲሁም ደግና ለተቸገሩት ደራሽ ባለ ሀብት እንደሆኑ ይነገርላቸዋል፡፡ በተለይ መለያቸውም ይህ ነው፡፡ ባለሀብቱ የቁጫዎችን ጥያቄ በሚመለከት ከአሜሪካ ሬዲዮ (VOA)፤ ከጀርመን ሬዲዮ (DW)፤ እና ከሌሎች የፕሬስ የሚዲያዎች ጋር ቃለ-ምልልስ አድርገሃል፤ በዚህም “ሕዝብን ለአመጽ አነሳስተሃል”፤ በሚሉና በተያያዥ ክሶቸ የጋሞ ጎፋ ዞን ፖሊስ በቁጥጥር ሥሩ የዋሉት ባለፈው ቅዳሜ ነሐሴ 11ቀን 2005 ዓ.ም  ማለዳ ላይ ነበር፡፡ በነገራችን ላይ እንደሰማሁት ከሆነ፤ ፖሊሶች ግለሰቡን ለማሠር የፈለጉበት ምክንያት ምንም ይሁን ምን በቁጥጥር ሥር ለማዋል የተከተሉት መንገድ የሕግ አግባብነትን የተከተለ ነበር የሚል ድምዳሜ አለኝና ለሠራዊቱ አባላት ምስጋናዬ ይድረሳቸው፡፡

ጽንፈኞቹ (2)

ውድ አንባቢያን እንደተለመደው ዛሬም ወደዋናው ርዕሴ ከመግባቴ በፊት ትንሽ ስለ ጎንደር ስለ ጀግናው የአጼ ቴዎድሮስን ሀገር ትንሽ ልበላችሁ ጎንደር የነአጼ ፋሲልም ሀገር ነው። ዛሬ ትንሽ ስለጎርጎራ ልንገራችሁና ወደፊት ስለ ጎንደር ከተማ እናወጋለን፡፡ መኪናዎትን እያሽከረከሩ ጎንደር ሊደርሱ ጥቂት ሲቀርዎት የጎንደርን የአጼ ቴዎድሮስን አየር ማረፊያ አጥር እንደጨረሱ አዘዞ ከተማ ሳይገቡ ወደ ግራ ይታጠፋሉ። ከዚያም ቅድም ከበላይዎ የነበረው አየር ማረፊያ ከበታችዎ አርገው ዳገቱን እየገፉ የባህር ዳር ሌላኛው ገጽታ (the other face of Bahirdar) ወደ ጎርጎራ ያቀናሉ። ሁለት ኪ/ሜ የማትሞላውን ዳገት ከጨረሱ በሁዋላ ለጥ ያለውን የመኪና መንገድ ይዘው ቆላ ድባን ጯሂትን አልፈው ጎርጎራ ይገባሉ።

ጎርጎራ ጣና ሀይቅ ከአጠገቡዋ ተኝቶ ሲያዩት እና ከዚህ ከጣና ሀይቅ የሚመጣው ቀዝቃዛ አየር አጠገበዎ ዳረሶ ሲነካዎ ሲያስደስት ግሩም ነው። በዚህ በጎርጎራ ደርግ ሰርቶታል የሚባለው የመዝናኛ ቦታ በአሳዛኝ ሁኔታ አልጋዎቹ ፈራርሰው ሲያዩ በእጅጉ ያዝናሉ ያለቅሱማል። በጎርጎራ የመዝናኛ ቦታ በርካታ የስፖርት ሜዳዎች አሉ፡፡ ግራውንድ ቴኒስ፣ የቅርጫት ኩዋስ መጫዎቻ፣ የመረብ ኩዋስ መጨወቻ፣ የእጅ ኩዋስ መጫወቻና የመሳሰሉት ያሉ ሲሆን ግን ደርግ ስለሰራቸው ሊሆን ይችል የሆናል አገልግሎት ግን አይሰጡም፡፡ በአሁኑ ሰዓት የአያያዝ ጉድለት ችግር ቢኖርም ነገር ግን የግልና የጋራ የእንግዳ ማረፊያዎችም በጎርጎራ መዝናኛ ቦታ አሉ።

በአዕምሮ ሁከት የተለከፈችው እህት በጅዳ! በትዞራለች… ትዞራለች… ሲደክማት ታርፈና አሁንም ትዞራለች!

ነቢዩ ሲራክ
አንድ ወዳጀ መሃመድያ ተብሎ በሚጠራው የጅዳ ከፍል ከኢትዮጵያ አለም አቀፍ ትምህር ቤት አካባቢ ይህችን በፎቶው ላይ የምታዩዋትን እህት አግኝቶ ሊያነጋግራት ቢሞክርም ፈቃደኛ አልነበረችም። ከየት ነው የመጣሽ ? ስትባል” ከመቀለ ” ከማለት ባለፈ ስሟንና የሆነችውን አትናገርም ። ብዙ ሊያግባባት ሞክሮ ያልተሳካለት ይህ ወዳጀ ይህች እህት ያደፈና የተቀደደ ጥቁር “አባያ” ለብሳና መናኛ ነጠላ ጫማ የተጫማችው እህት የአዕምሮ ሁከት እንዳለባት የተረዳው ብዙ ለማነጋገር ሞክሮ በሰጠችው አንዳንድ ምላሽ እንደሆነ ገልጾልኛል! ልጁን ትምህርት ቤት ሊያስመዘግብ በሔደበት አጋጣሚ በጠራራው ሜዳ ስትንከራተት በማየቱና ምንም መርዳት ባለመቻሉ ያዘነው ወዳጀን መረጃ ይዠ የጅዳን ቆንስል ሃላፊዎች ስልክ በመደዎል ይህችን እህት በመጠለያው አምጥተው ሌላው ቢቀር ካሉት የአዕምሮ በሽተኞች ጋር ቀላቅለው ከመኪና እና ከመሳሰሉት አደጋዎች አንዳትጋለጥ ይሰበስቧት ዘንድ ለማሳወቅ ያደረግኩት ሙከራ አልተሳካም!

በወያኔን “ያደገችዋን” ኢትዮጵያ ዓለም እንዴት ያያታል?

ዶ/ር ዘላለም ተክሉ
ነሐሴ 25 2013
በዚህ ሳምንት መጨረሻ በኢሳት የቀረበውን “ የእሁድ ወግ” ፕሮግራም ሳዳምጥ ነበር:: በዚሁ ፕሮግራም ከቀረቡት ዋና ዋና መወያያ ርዕሶች ውስጥ ሟቹ ጠቅላይ ሚኒስትር መለስ ዜናዊ ለኢትዮጵያ ህዝብ አጎናጸፉት እየተባለ ስለሚደሰኮረው ዕድገት የተሰጡት አስተያየቶች ትኩረቴን ስበውኝ ነበር:: በተለይ ሰውዬው (ከሳቸው የተማርኩት አባባል ስለሆነ ይቅርታ) ህዝቡን ጥጋብ በጥጋብ አደረጉት፣ ብዙ ሃብታም ገበሬዎችን ፈጠሩ፣ሚሊዮኖችን ከድህነት አረንቋ አላቀቁ ስለሚባለው አቶ ሲሳይ አጌና የሰጠው ምላሽ በጥሩ ትንተና የተደገፈ መሆኑ ያስደሰተኝ ሲሆን በዚች ትንሽ መጣጥፍ የበለጠ ማጠናከሪያ በመስጠት ፕሮፓጋንዳውን ለመሞገትና ምስኪኑ ህዝባችንም እውነታውን ራሱ ፈትሾ እውነቱን እንዲያውቅ ፈለኩ::
አቶ ሲሳይ ሙግቱን (argument) ሲያስረዳ፣ በእውነት የፕሮፓጋንዳ ማሽኖቹ በተደጋጋሚ እደሚነግሩን በእርሳቸው መጀን ኢኮኖሚያችን አድጎዋል ከተባለ ከ 80 በመቶ በላይ የሆነው ገበሬው ህዝባችን ኢኮኖሚው አድጓል ማለት ነው:: የገበሬዎች ገቢ ደግሞ አደገ ከተባለ ያ ሊሆን የቻለው ያመረቱቱትን ብዙ ምርት ወደገበያ አውጥተው ሸጠው ጥሩ ገቢ ሰብስበዋል ማለት ነው::

መንግስት የሙት ዓመትና ተዝካር ማሇት ትቶ ትኩረቱን ሇሀገራዊ መግባባት ቢሰጥ

ግርማ ሠይፉ ማሩ
ሙት ዓመትና ተዝካር የሚያወጣ መንግሰት ያየሁት የኛው ጉዴ የሆነው በስሌጣን ሊይ ያሇው ፓርቲ መሆኑን መጠራጠር ያሇብን
አይመስሇኝም፡፡ ፋውንዳሽኑ እንጂ የመንግሰት አይዯሇም የሚሌ ማምታቻ እንዯማይሰራ ከዚሁ ማሰጨበጥ ያስፈሌጋሌ፡፡ ሌክ ነው
የአንዯኛ ዓመት መታሰቢያ በአንዴ አዲራሽ ቢታሰብ ክፋቱ አይታየኝም፡፡ ነገር ግን ሁለም የመንግስት መዋቅር የ”ሕዝብ” ተወካዮች
ምክር ቤቱን ሰራተኞቹን ጨምሮ የሙት ዓመት ሇማክበር የመንግሰት ሰራ አቋርጠው ችግኝ ተከሊ ወይም የሻማ ማብራት ሰነ ስርዓት
ሊይ መገኘት ተገቢም ትክክሌም አይመስሇኝም፡፡ ከሁለም የሚገርመው በሙት ዓመት ሊይ ሇመገኘት ወዯ ሀገራችን የመጡት መሪ
ተብዬዎች እና ተወካዮች ናቸው፡፡ እርግጥ ነው የሱዲኑ ፕሬዝዲንት ከሸሪክ አንባገነን ሀገሮች ውጭ መሄዴ ስሇማይችለ የእርሳቸው ጉዞ
በእውነቱ አጋጣሚውን ተጠቅሞ ወጣ ሇማሇት ብሇን በቅንነት ሌንወስዯው እንችሊሇን፡፡ የሚያሳዝነው ይህን ጉዲይ ብሇው የመጡ
መሪዎችን ሇመቀበሌና ሇመሸኘት በሚዯረግ ሸብ-እረብ ዜጋው የገጠመው ሰቃይ ነው፡፡ ሁለም እንዯሚረዲው የአዱሰ አበባ ከተማ
በአጭሩ ሉቃሇሌ በማይችሌ የትራንስፖርት አገሌግልት ቅርቃር ውስጥ ትገኛሇች፣ በዚህም ሊይ በተሇያየ የመንገዴና የባቡር ግንባታ
ምክንያት ከፍተኛ የትራፊክ ፍሰት ችግር አሇ፡፡ እዚህ ሊይ ነው እንግዱህ ሰራ ፈት መሪዎች ሙት ዓመት ብሇው መጥተው ከተማዋ ሊይ
ጫና ፈጥረው በእንቅርት ሊይ ጆሮ ዯግፍ ያሰኙን፡፡

የእኛ “መንግስት”

ተመስገን ደሳለኝ
“በእያንዳንዱም መንግስት የሚያድሩ ብዙ ልዩ ልዩ ነገዶች ይኖሩ ይሆናል፡፡ ስለ ሆነ መንግስት አንዱን ነገድ  አጥቅቶ ሌላውን ነገድ ለመጥቀም ሥራው አይደለም፡፡ አስተካክለን ካሰብን ዘንድ መንግስት መቆሙ ለሕዝቡ  ሁሉ ጥቅም ነው፡፡ ጥረቱም ህዝቡን ሁሉ በትክክል ለመጥቀም ያልሆነ መንግስት ሊቆም አይችልም፡፡ ለአንዱ  ነገድ ወይም ለጥቂት ሰዎች ብቻ ማድላት ለመንግስት የሚገባ ሥራው አይደለም”
ይህንን መግቢያ የወሰድኩት በልዑል የኢትዮጵያ መንግስት አልጋ ወራሽ ተፈሪመኮንን ማተሚያ ቤት የካቲት 1  ቀን 1917 ዓ.ም ከታተመው የነጋ ድራስ ገብረ ሕይወት ባይከዳኝ‹‹መንግስትና የሕዝብ አስተዳደር›› መፅሀፍ ነው፤
ዛሬም ያለንበትን ዘመን ይዋጃልና፤ በተለይ ስለ‹‹ነገድ›› የተጠቀሰውን አርቀን ሰቅለን፣ ‹‹ለጥቂት ሰዎች ብቻ ማድላት›› የምትለዋን ሀረግ በወጉ ካጤንናት ለጊዜያችን በልክ የተሰፋች መሆኗን ለመረዳት አስቸጋሪ አይደለም፡፡

Monday, August 26, 2013

ከመላው ኢትዮጵያ አንድነት ድርጅት /መኢአድ/ ለኢትዮጵያ ህዝብ የተላለፈ መልዕክት

xx
ለተከበረው የኢትዮጵያ ህዝብ በሙሉ
በኢትዮጵያ ሀገራችን የአገር አንድነት ከተናጋና የዜጎች መብት ከተደፈጠጠ አነሆ 22 ዓመታትን አስቆጥረናል።
ዜጎች ከቦታ ቦታ ተንቀሳቅሰው ሀብትና ንብረት እንዳያፈሩ አስቸጋሪ የሆነ ሁኔታ ተፈጥሮባቸዋል። ካፒታልና እውቀት ከቦታ ቦታ በመዘዋወር ዜጎችን እንዳያገለግሉ በክልል ድንበር ታግደዋል። ዜጎችም ለብዙ ዓመታት ከሰፈሩበት ቦታ አገርህ አይደለም በሚል ሰበብ የዘር ግንዳቸው መነሻ ወደሆነው ክልል እንዲሜለሱ ይገደዳሉ። በዚሁ መሰረትም በዚሁ ዓመት ብቻ በብዙ ሺህ የሚቆጠሩ የአማራ ልጆች ከቤንሻንጉልና ከጉራፈርዳ በኢሀዴግ ካድሪወች ተፈናቅለዋል። ሃብት ንብረታቸውም ተዘርፈዋል። የአፋርና የጋንቤላ ልጆችም መሬታቸው ለባዕድ ስለተሸጠባቸው የመኖር መብታቸው ተገፏል፣ ለስደትም ተዳርገዋል።

የዕርቁ ካርድ እንዳይባክን!! የተደበቃችሁ ተገለጡ!!

(ርዕሰ አንቀጽ)





“ከፍትህ ጋር ተቀነባብሮ ያልተፈጸመ ዕርቅ ዘላቂነት የለውም፤ ሁላችንም ሰላም እንዲሰፍን ተስፋ የምናደርግ ብንሆንም የምንመኘው ሰላም በፍትህና በሕግ ላይ የተመሠረተ መሆን ይገባዋል እንጂ በተገኘው ሁኔታ ይሁን የምንለው መሆን የለበትም” የቀድሞ የፊሊፕንስ ፕሬዚዳንት ኮራዞን አኪኖ፡፡
ወደ ሥልጣን የተጠጉና ለመጠጋት የሚያስቡ ፓርቲዎችና ግለሰቦች እንዲሁም ሥልጣንን የተቆጣጠሩ ወዘተ በአገራችን ዕርቅ እንዲመጣ ሲመኙ፣ ሲያቅዱ፣ ፕሮግራም ሲያወጡ፣ ዲስኩር ሲሰጡ፣ … ቢያንስ አራት አሥርተ ዓመታትን አስቆጥረናል፡፡ “ብሔራዊ ዕርቅ፣ አገር አቀፋዊ ዕርቅ፣ … ” እየተባለ ሲነገር የሰማነው አሁን አይደለም፡፡ እስኪሰለቸን ሰምተናል። እርቅን ያህል ታላቅ ጉዳይ “የፖለቲካ ሃይሎጋ ሆ” አስመስለው ሲጫወቱበት የቆዩ፣ አሁንም ድረስ “ባገር ሽማግሌነት” ስም የሚቆምሩ የትውልድና ያገር “ችግር ቁልፍ ተወናዮች” እንዳሉ ህዝብ ያውቃል። ለይቶ በስም ይጠራቸዋል።

ትዞራለች … ትዞራለች … ሲደክማት ታርፈና አሁንም ትዞራለች!



በአዕምሮ ሁከት የተለከፈችው እህት በጅዳ!
11-e


አንድ ወዳጄ መሃመድያ ተብሎ በሚጠራው የጅዳ ከፍል ከኢትዮጵያ አለም አቀፍ ትምህር ቤት አካባቢ ይህችን በፎቶው ላይ የምታዩዋትን እህት አግኝቶ ሊያነጋግራት ቢሞክርም ፈቃደኛ አልነበረችም። ከየት ነው የመጣሽው? ስትባል”ከመቀለ” ከማለት ባለፈ 11ስሟንና የሆነችውን አትናገርም። ብዙ ሊያግባባት ሞክሮ ያልተሳካለት ይህ ወዳጀ ይህች እህት ያደፈና የተቀደደ ጥቁር “አባያ” ለብሳና መናኛ ነጠላ ጫማ የተጫማችው እህት የአዕምሮ ሁከት እንዳለባት የተረዳው ብዙ ለማነጋገር ሞክሮ በሰጠችው አንዳንድ ምላሽ እንደሆነ ገልጾልኛል!
ልጁን ትምህርት ቤት ሊያስመዘግብ በሔደበት አጋጣሚ በጠራራው ሜዳ ስትንከራተት በማየቱና ምንም መርዳት ባለመቻሉ ያዘነው ወዳጄን መረጃ ይዤ የጅዳን ቆንስል ሃላፊዎች ስልክ በመደወል ይህችን እህት በመጠለያው አምጥተው ሌላው ቢቀር ካሉት የአዕምሮ በሽተኞች ጋር ቀላቅለው ከመኪና እና ከመሳሰሉት አደጋዎች አንዳትጋለጥ ይሰበስቧት ዘንድ ለማሳወቅ ያደረግኩት ሙከራ አልተሳካም!

ግብረ ሰዶም (Homosexual) በኢትዮጽያ

ግብረ ሰዶም የሚለው መጠሪያ የተገኘው ከመፅሐፍ ቅዱስ ነው:: የሰዶም ስራ እንደ ማለት ነው:: ሰዶም እና ገሞራ በመፅሐፍ ቅዱስ ታሪክ ውስጥ ያሉ መንደሮች ናቸው:: በዚያም ጊዜ በነዚህ መንደር ወንድ ከወንድ: ሴት ከሴት ይዳራ ነበር: አንድ ሴት ከብዙ ወንዶች ጋርም ወሲብ ትፈፅም ነበር:: እግዜርም በዚህ ተበሳጭቶ ከተማዋን በእሳት አጠፋት:: ከዛ ጊዜ ጀምሮ ወንድ ከወንድ ጋር ሴት ከሴት ጋር ሚዳሩት ግብረ ሰዶማዊያን:: ነገሩን ደሞ ግብረ ሰዶም መባል ጀመረ:

ግበረ ሰዶማውያን በኢትዮጽያ በጣም የተወገዙ ናቸው:: እራሳቸውን ደብቀው የሚኖሩ(አሁን አሁን ግን በስብሰባ አደዳራሽ በግልፅ መሰብሰብ ጀምረዋል) እንደሌላው አለም ‘I AM A GAY’ ብሎ ባደባባይ ‘ሚደነፋ እኛ ሃገር ላይ የለም (የወደፊቱን ባናቅም) እንደውም ግብርሰዶማዊነቱ ከታወቀ ወይ ከተጠረጠረ ያሰው ይገለላ:: እንደሰው ሳይሆን ‘ሚቆጠረው እንድ አውሬ ነው::

ሰሞኑን አንድ ታስሮ የተፈታ አብሮ አደጌ ስለ እስር ቤት ቆይታው ሲያጫውተኝ ስለ ግብረ ሰዶማዊያን አነሳሁበት:: ግብረሰዶማዊያን በእስር ቤት ውስጥ ያላቸውን የህይወት መስተጋብር ባጭሩ እንዲህ አብራራልኝ “አንድ ሰው ቡሽቲነቱ ከታወቀ ማንም ወደሱ አይጠጋም:: ከማንም ጋር አይቀላቀል:: የሚተኛውም ለብቻው ሽንት ቤት አጠገብ ነው:: ከሱው ጋር የታየ ሰው በቃ አለቀለት ያሰው ጌ ነው ተብሎ በሰፊው ይወራበታል ወደ እሱ የተጠጋ ሰው የልጁ አይነት እጣፈንታ ስለሚገጥመው ወደሱ ማንም ዝር አይልም::” 

Corruption in the Ethiopian JUST US Sector

For the past several months, I have been commenting on the findings of the World Bank’s “Diagnosing Corruption in Ethiopia”, a 448-page report covering eight sectors (health, education, rural water supply, justice, construction, land, telecommunications and mining). In this my sixth commentary, I focus on “corruption in the justice sector”. The other five commentaries are available at my blog site.A glossy “diagnosis” of corruption in the Ethiopian justice sector
Talking about corruption in the Ethiopian “justice sector” is like talking about truth in Orwell’s 1984 Ministry of Truth (“Minitrue”).  The purpose of Minitrue is to create and maintain the illusion that the Party is absolute, all knowing, all-powerful and infallible. The purpose of the Ministry of Justice in Ethiopia is to create the illusion that the ruling regime under the command and control of the Tigrean People’s Liberation Front (TPLF) masquerading as the Ethiopian People’s Democratic Front (EPDRF) is absolute, all knowing, all-powerful and infallible.

ለእምነት ነፃነት የምናደርገውን ትግል ለሰብዓዊ መብቶች መከበር፣ ለዜግነት ክብር እና ለሀገር ነፃነት ከምናደርገው ትግል ጋር እናቀናጅ!!!

ትንሽነቱ በፈጠረበት ስጋት ምክንያት ሁሉንም ነገር ካልተቆጣጠረ በጉልበት የያዘውን ሥልጣን የሚያጣ የሚመስለው እና በዚህም ሳቢያ ሁሉም ነገር ውስጥ እጁን የሚነክረው ወያኔ ራሱን በገዢነት ከሾመበት እለት ጀምሮ የሃይማኖት ተቋማትን ሙሉ በሙሉ ለመቆጣጠር እንደተጋ ነው። በእኛ በኢትዮጵያዊነት ዳተኝነት ታግዞም ትጋቱ ውጤት እያስገኘለት ነው።
ወያኔ፣ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክህነትን ከፓትሪያርክ ጀምሮ እስከ ደብር አለቆች ድረስ ያለው መንፈሳዊ ሹመት ተቆጣጥሯል። አሁን የቀየረው የቤተክርስቲያኒቷን ሃይማኖታዊ ቀኖናን መቀየር ነው። ወያኔ በሥልጣን ላይ ከቆየ ይህንንም ከማድረግ የማይመለስ መሆኑን በእስልምና እምነት ላይ ተግባራዊ እያደረገ ካለው መገንዘብ ይቻላል።
ልክ እንደ ክርስትናው ሁሉ ወያኔ የኢትዮጵያ እስልምና ጉዳዮች ጠቅላይ ምክር ቤትን (መጅሊስ) በራሱ ካድሬዎች ሞልቶት ሙሉ በሙሉ ተቆጣጥሮታል። እስልምና ላይ ግን የሃይማኖት ተቋማትን ከመቆጣጠር አልፎ በቀኖና ጉዳይ በመግባት የራሱን “ምርጥ እስልምና” እያስተዋወቀ ነው። ዛሬ በሙስሊሞች ላይ የመጣው ነገ በክርስቲያኖችም ላይ የሚመጣውን አመላካች ነው።

መንግስት ለመጪው እሁድ ሰልፍ ጠራ! (ድምፃችን ይሰማ)

ለተሳታፊዎች ዳጎስ ያለ አበል ተዘጋጅቷል!
የግል ድርጅት ሀላፊዎች ከእነ መኪናቸውና ሰራተኞቻቸው በሰልፉ እንዲገኙ ግዳጅ ተጥሎባቸዋል!
መንግስት በመጪው እሁድ ሰልፍ ሊያካሄድ ነው፡፡ መንግስት በክልሎች ሲያካሄድ ያቆየውን ይህንኑ የግዳጅ ሰልፍ በአዲስ አበባ ለማድረግ ለወራት ከፍተኛ ዝግጅት ሲያካሄድ ቆይቷል፡፡ የፊታችን እሁድ በአዲስ አበባ ለማካሄድ የታሰበው ሰልፍ በዋነኝት ሙስሊሙ ህብረተሰብ ያነሳውን የእምነት መብት ጥያቄ በክራሪነት ለመወንጀልና ‹‹ሕዝቡ መንግስት እርምጃ ይውሰድልን›› አለ በሚል ለሚዲያ ፍጆታ ለመጠቀም ነው፡፡

በሚኒሶታ ለአባይ ቦንድ ሽያጭ የተጠራው ስብሰባ ሳይጀመር ተበጠበጠ

21
(ዘ-ሐበሻ) በሴንት ፖል ሚኒሶታ የአባይን ቦንድ ለመሸጥ የኢትዮጵያ መንግስት አዳራሽ ተከራይቶ ለዛሬ ኦገስት 25 ቀን 2013 ዓ.ም ከ ቀኑ 2 ሰዓት እስከ ምሽቱ 8 ሰዓት ስብሰባ የጠራ ሲሆን ስብሰባው ከመጀመሩ አንድ ሰዓት በፊት ብጥብጥ ተነሳ።
በርከት ያሉ ኢትዮጵያውያን “ወያኔን አናምንም፤ 2 ሰዓት ብሎ ጠርቶ ስብሰውን ቀድሞ ሊጀምርና ሊነሳበት የታቀደውን ተቃውሞ ሊያከሽፍ ይችላል” በሚል ገና ከጠዋቱ ስብሰባው ይደረግበታል የተባለበት አዳራሽ በር ላይ ሲጠባበቁ ቆይተዋል። ልክ ስብሰባው ሊጀመር 1 ሰዓት ሲቀረው አንድ የስርዓቱ ደጋፊ የሆነ ሰው ካሜራ ይዞ “ከአባይ በፊት ሰብአዊ መብት ይከበር፤ የታሰሩት ይፈቱ” በሚል ለተቃውሞ የተሰባሰበውን ሕዝብ ሊቀርጽ ሲጠጋ ሕዝቡ “ሃገር ቤት ቪድዮ የቀረጻችሁት ሳያንስ እዚህ ልትቀርጹ ነው ወይ?” በሚል ልጁን ክፉኛ ከደበደቡት በኋላ ካሜራውን ሰባብረውበታል ያሉት የአይን እማኞች ወዲያውም ከ20 የሚበልጡ የሴንት ፖል ከተማ ፖሊስ መኪናዎች አካባቢውን በመክበብ ብጥብጡን አርግበውታል።

Sunday, August 25, 2013

የደህንነትና የፖሊስ ሀላፊዎች የሙስሊሙን ህብረተሰብ የመብት ጥያቄ ለማዳፈን እንደሚሰሩ ገለጹ!

‹‹መንግስት መስጂዶችን ከአክራሪዎች ቀምቶ ለእኛ ሊሰጠን ይገባል›› የመንግስታዊው ሃይማኖት አቀንቃኝ ግለሰብ
የደህንነትና የፖሊስ ሀላፊዎች የሙስሊሙን ህብረተሰብ የመብት ይከበር ጥያቄ ለማኮላሸት መስራታቸውን እንደሚቀጥሉ አስታወቁ፡፡ ሀላፊዎቹ ይህን የገለጹት ለሁለት ቀናት በተካሄደ ስብሰባ ላይ ነው፡፡ ረቡእና ሐሙስ በአዲስ አበባ ስድስት ኪሎ በሚገኘው የስብሰባ ማእከል በተደረገው በዚህ ስብሰባ ህዝብ ያወረዳቸው የመጅሊስ ሹመኞች፣ የመስጂድ ኮሚቴዎች፣ በአዲስ አበባ የሚገኙ ኢማሞች፣ ሙአዚኖች እና የመንግስታዊው ሃይማኖት አቀንቃኞች የተገኙ ሲሆን ዋነኛ አጀንዳውን ያደረገውም ‹‹አክራሪነት በመከላከልና ጸጥታን በማስፈን›› ርእሰ ጉዳይ መሆኑ ታውቋል፡፡

ኢንጂነር ተስፋሁን ጨመዳ በቃሊቲ እስር ቤት ሕይወቱ አለፈ

(ዘ-ሐበሻ) ታዋቂው የሰብአዊ መብት ታጋይና መንግስትን ለመገልበጥ አሲረዋል በሚል ሕይወቱን በሙሉ በእስር ቤት እንዲያሳልፍ የተፈረደበት ኢንጂነር ተስፋሁን ጨመዳ በቃሊቲ እስር ቤት ሕይወቱ ማለፉን የዘ-ሐበሻ ምንጮች ዘገቡ።
እንደዘ-ሐበሻ ምንጮች ዘገባ ኢንጂነር ተስፋሁን ሕይወቱ ያለፈው ትናንት ሲሆን ለሕይወቱ ማለፍ የተገለጸ ምክንያታዊ በሽታም ሆነ ሌላ ነገር አልቀረበም።

የግብፅና ኢትዮጵያ መጪው ዘመን ምን ሊመስል ይችል ይሆን?

ግብፅ (ምስር) እንደሃገር ከምትታውቅበት ማለትም ከፈሮኦኖች ዘመን ጀምሮ ፤ የታሪኳም ሆነ የህልውናዋ መሰረት አባይ ነው። አባይ ባይኖር የግብፅ የቆየና ጥንታዊ ታሪኳ የለም ፤ የፈርኦኖች ታሪክ የለም፤ አባይ ባይኖር የክሊዮፓትራ ታሪክ የለም ። ባጠቃላይ አባይ ባይኖር ግብፅም ታሪኳም፤ጥንታዊ ስልጣኔዋም፤ የአለማችንን እውቅ የታሪክ ምርምር መፃህፍት ገፆች ባላጣበቡ ነበር ። ታላቁ የግሪክ የታሪክ ሰው ሄሮዶቱስ ግብፅ የአባይ ስጦታ ነች ያለውም ለዚህ ነበር ። ታላቁ አሌክሳንድር ከግሪክ ተነስቶ መካከለኛው እስያ የሚባለውን ምድር ወርሮ ወረራውን በጊዜው ታላቅ አገርና አስፈሪ ጦር የነበረውን ፐርሽያን በዛሬው አጠራር ኢራንን ድል አድርጎ ወደ ህንድ ድንበር ከተጠጋ በሁዋላ በድንገት አረፈ።

መንግስት የሙት ዓመትና ተዝካር ማለት ትቶ ትኩረቱን ለሐገራዊ መግባባት ቢሰጥ – ግርማ ሠይፉ ማሩ

ሙት ዓመትና ተዝካር የሚያወጣ መንግሰት ያየሁት የኛው ጉዴ የሆነው በስሌጣን ሊይ ያሇው ፓርቲ መሆኑን መጠራጠር ያሇብን አይመስሇኝም፡፡ ፋውንዳሽኑ እንጂ የመንግሰት አይዯሇም የሚሌ ማምታቻ እንዯማይሰራ ከዚሁ ማሰጨበጥ ያስፈሌጋሌ፡፡ ሌክ ነው የአንዯኛ ዓመት መታሰቢያ በአንዴ አዲራሽ ቢታሰብ ክፋቱ አይታየኝም፡፡ ነገር ግን ሁለም የመንግስት መዋቅር የ”ሕዝብ” ተወካዮች ምክር ቤቱን ሰራተኞቹን ጨምሮ የሙት ዓመት ሇማክበር የመንግሰት ሰራ አቋርጠው ችግኝ ተከሊ ወይም የሻማ ማብራት ሰነ ስርዓት ሊይ መገኘት ተገቢም ትክክሌም አይመስሇኝም፡፡

ትንሽ ስለ ‘መለሲ-ዝም’: ከኢህአዴጎች የምስማማበት ነጥብ .Abraha Desta

ሳስበው ሳስበው ስለ ‘መለሲዝም’ ሰበካ የተጀመረ ይመስለኛል። በመለስ ማመናቸው ችግር የለብኝም። ግን መለስ ፈጣሪያቸው መሆኑ እየነገሩን ነው። ብዙ ነገሮች በሱ ስም እየተሰየሙ ናቸው። እነሱ እንደሚነግሩን ከሆነ የኢህአዴግ ፖሊሲ የመለስ ነው፣ መለስ ወታደራዊ መሃንዲሳቸው ነበር፣ መለስ አንቀሳቃሽ ሞተራቸው ነበር፣ የኢህአዴግ ሓሳብና ተግባር የመነጨው ከመለስ ነበር፣ ባጠቃላይ መለስ ሁለመናቸው ነበር።