Friday, February 28, 2014

ጀግናውና ከሀዲው ረዳት አብራሪ ኃይለ መድኅን አበራ

(ሠዓሊ አምሳሉ ገ/ኪዳን አርጋው)
hailemedhin

ይድረስ ለፕ/ር ጌታቸው ኃይሌ፡- በኢትዮጵያ ታሪክ ተወቃሾቹ የኦሮሞ ሕዝብና ሙስሊሙ ማኅበረሰብ ብቻ ነውን እንዴ?!

በዲ/ን ኒቆዲሞስ ዕርቅ ይሁን  - nikodimos.wise7@gmail.com
‹‹ዕርቅና ሰላም የሕይወት ቅመም፣ የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንን እንደውለታ ቢስ ለሚቆጥሩ ወገኛ ሁሉ የሚሆን መልስ እነሆ!›› በሚል ርእስ የጻፉትን ጦማር እጅግ የማክበርዎና ኢትዮጵያዊው የምሆን ወንድምዎ ደጋግሜ አነብበኩት፡፡ ፕሮፌሰር በትክክል ተረድቼዎት ከሆነ እርስዎ በጽሑፍዎ ለማስተላለፍ የፈለጉት ዋንኛ መልእክትዎ፣ አንድም ‹‹ዕርቅንና ሰላም መስበክ›› ሲሆን በሌላ በኩል ደግሞ ‹‹የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያንን እንደ ጠላት ወይም ውለታ ቢስ አድርገው ለሚቆጥሩ ወገኛ ሁሉ መልስ ይሆናል በሚል እነሆ ያሉት ጦማር እንደሆነ ነው፡፡

በኢትዮጵያ የማዕድን ሙስናን ለመሸፋፈን የሚደረገው ዘበት

ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም
ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ
በኢትዮጵያ ያለው ገዥው አካል በማዕድኑ ዘርፍ የሚያካሂደውን ሙስና በማደብዘዝ እና በመሸፋፈን ንጹህ መስሎ ለመታየት እና ዓለም አቀፋዊ ተቀባይነትን ለማግኘት በማሰብ በአምራች ኢንዱስትሪዎች የግልጽነት ተነሳሽነት(Extractive Industries Transparency Initiative (EITI)) ለተባለው ድርጅት ዕጩ አባል ለመሆን እንደገና ለሁለተኛ ጊዜ ይፍጨረጨራል፡፡ የገቢ ምልከታ ተቋም/Revenue Observation Institute የቦርድ ሊቀመንበር እና የአምራች ኢንዱስትሪዎች የግልጽነት ተነሳሽነት/EITI የቦርድ አባል የሆኑት አንቶኒ ሪቸር እንደሚሉት ከሆነ እ.ኤ.አ በ2010 ኢትዮጵያ የአምራች ኢንዱስትሪዎች የግልጽነት ተነሳሽነት/EITI አባል ለመሆን ያቀረበችው ጥያቄ ውድቅ ተደርጎ ነበር፣ ምክንያቱም የኢትዮጵያ ‘የበጎ አድራጎት እና ማህበራት ድርጅት አዋጅ (Proclamation on Charities and Societies) የሲቪክ ህዝብ ማህበራት ቡድኖች ሙሉ በሙሉ ነጻ ሆነው እና በሂደቱም ላይ ትርጉም ያለው ተሳትፎ እንዳያደርጉ የሚከለክል ደንቃራ በመሆኑ ነው የሚል ድምዳሜ ሰጥቷል፡፡

በማተብዋ ልዳኝ – ወድቃ የተነሳችው (ከስንሻው ተገኘ)

ከስንሻው ተገኘ
ወደ ትዝታ ዓለም ወደ ትዝታ ጊዜ በትዝታ ሰረገላ ልወስዳችሁ ነው። እኔ እንኳ በአጻጻፌ አበባዊ ቋንቋ አልወድድም። ለማንኛውም ግን አብረን እንድንነጉድ እጋብዛችኋለሁ። ወደ እንግሊዝ አገር! 1953 እ.አ.አ ወደ አንድ የለንደን ስብሰባ አዳራሽ እንገባለን። እንግዶች የነፃነት ታጋዮች ወደ አዳራሹ ከመግባታቸው በፊት የዌስት ኢንዲስ ተወላጅና የዓለም አቀፍ የጥቁር ሕዝቦች የነፃነት ንቅናቄ መሪ የሆነው ጆርጅ ፓድሞን በአዳራሹ ውስጥ ፕሪዚደሙን ለብቻ ይዞታል። የእኔንና የእርስዎን ቡጢ (ጭብጥ) የሚያህል ወፍራሙን ትምባሆ (ቶስካኖ) ጐርሶአል። ጐርናና ድምፁ ሰውንም አዳራሹንም የሚቆጣጠር ዓይነት ነው። ከአፉ የሚወጣው ጢስ በአካባቢው አንዳች ዓይነት ጉም ሠርቶአል። በመካከሉ የሚያሰማው ባለ ግርማ የሆነው ሳሉ ለሰውየው ተጨማሪ ክብር አሸክሞታል።

Wednesday, February 26, 2014

በጭካኔ እየተገዳደልን፣ ወዴት እየሔድን ነው? የአብዱ ሁሴን ይማም ግድያ

abdu hussien

“ግብረሰዶማውያን ከተፈጥሮ ውጪና አጸያፊ ናቸው”

ዑጋንዳ የጸረ ግብረሰዶማውያን ሕግ አጸደቀች!
musevini
ለበርካታ ዓመታት አከራካሪ ሆኖ የቆየውን የጸረ ግብረሰዶማዊነት ሕግ ትላንት ዑጋንዳ አጽድቃለች፡፡ ከምዕራቡ ዓለም እና ሰዶማዊነት የመብት ጉዳይ እንደሆነ ከሚከራከሩ ተቋማት የደረሰባትን ውትወታ ወደ ጎን በማለት ዑጋንዳ በሕግ ማጽደቋ የበርካታ ዓለምአቀፍ መገናኛ ብዙሃንን ሽፋን የሰጡበት ርዕስ ሆኗል፡፡ የሕጉን መጽደቅ አስመልክቶ ጥቂት ዑጋንዳውያን ተቃውሞ ሰልፍ የወጡ ሲሆን በርካታዎች ደግሞ ድጋፋቸውን ለፕሬዚዳንቱ ገልጸዋል፡፡

Tuesday, February 18, 2014

“ጥቁሩ ሰው” – የጥቁር ሕዝብ አባት

ከስንሻው ተገኝ
አንድ ዘመን ሥርዓተ መንግስቱ በመቆየትም ሆነ አባላቱ የአሥራ ሰባተኛው ክፍለ ዘመን የተረት ዓለም ሰዎች ስለ መሰሉን- ሁሉም ነገር ስለገለማን አዲስ ሥርዓት፣ አዲስ መሪ፣ አዲስ ዘመን መናፈቅ ይዘን ነበር። ሰዓሊ ሁሉ፣ ደራሲ ሁሉ፣ ጸሐፌ -ተውኔት ሁሉ እጁን የሚያሟሸው በቴዎድሮስ ሥዕል፣ ተውኔትና ታሪክ ሆነ። ብርሃኑ ዘሪሁን- የቴዎድሮስ እንባ -(መጽሐፍ) ከዚያ በፊት ደጃዝማች ግርማቸው ተክለሐዋርያት- ቴዎድሮስ (ተውኔት) አቤ ጉበኛ – አንድ ለእናቱ (ታሪካዊ ልቦለድ) ጸጋዬ ገብረ መድኅን – ቴዎድሮስ (ተውኔት)…ሥዩም ወልዴ -ሥዕል..ታደሰ ወ.አ….ቅርጻቅርጽ እና የሥነ ጥበባት ትምህርት ቤት ሥስት አራተኛ ተማሪዎች..የቴዎድሮስ ሥዕል ግጥም -ቅኔ- ሥዕል አለፈላት።Ethiopian king Atse Menelik
ከአሮጌና ከገለማ ሥርዓት ነፃ የሚያወጣ አመጸኛና አመጻ የሚመራ ጀግና ስንፈልግ ባጀንና ቴዎድሮስን አገኘን። ከመቶ አመት በኋላ ነው ቴዎድሮስ የተፈለገው። በአጤው ሥርዓት በአንዳንድ ደራስያንና የዘመን ታሪክን በውዳሴና በነቀፋ በሚያቀርቡ ግለሰቦች ዘንድ እንደጭራቅ ይቆጠር የነበረው መይሳው ካሣ በለውጥ መሪነት የተፈለገበት መሪ ነበር። አብዮታዊው መሪ ጓድ መንግሥቱ እንኳ፥ “ቴዎድሮስ” (ምናልባትም ዳግማዊ ቴዎድሮስ) እኔ ነኝ። የዚህን ሕዝብ አብዮት እንድመራም ከሙታን የተጠራሁ ነኝ” እስከ ማለት ደርሰው ነበር። በቴዎድሮስ መንገድ አልተጓዘም እንጂ። በተረተኞች፣ በተረበኞችና በዋልጌዎች፣ በጐታቾችና በክፍፍል በኖሩ ዘንድ ተወዳጅ ያልሆነው ሕልመኛው ቴዎድሮስ በእርግጥ ከዘመኑ አርቆና አልቆ የሚያይ ስለሆነ ከወቅቱ ደባትርና ከመሳሰሉት ጋር ስምምነት አልነበረውም።

Ethiopian (Woyane) Airlines hijacked

by Yilma Bekele
The Name is Ethiopian but that particular property belongs to our Woyane masters. It is there for the TPLF to do what it wants. It started with such promise and grew up to be such a proud achievement by both people and country. That is until Woyane showed up., Ethiopian Airlines was absorbed by the TPLF mafia and molded in its own image
That promise of building an organization that belongs to us all was nipped in the bud by Meles Ashebari Zenawi and friends. Like all other institutions, Ethiopian Airlines was absorbed by the TPLF mafia and molded in its own image. Like most other institutions created by earlier generations that the TPLF inherited, the first order of business was to clean house in the name of re organization and install cadres from one tribe.

Monday, February 17, 2014

አቡጊዳ – የዶር ያእቆብ «አሰብ የማን ናት?» መጽሃፍ ሰባት ጊዜ እንደታተመ ተገለጸ

ዶር ያእቆብ ኃይለማሪያም፣ የአሰብ ወደብን በተመለከተ የጻፉት መጽሃፍ ሰባት ጊዜ እንደታተመ ከሲ.ቢ.ኤስ ራዲዮ ጣቢያ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ገለጹ። «ይህ የሚያመለክተዉ የኢትዮጵያ ህዝብ ምን ያህል የአሰብ ጉዳይ እንደሚያንገበግበው ነዉ» ያሉት ዶር ያእቆብ፣ በአሰብ ዙሪያ ያሉትን ችግሮች በስላም መፍታት እንደሚቻልም ለማሳየት ሞክረዋል።
የኤርትራ ሕዝብና የኢትዮጵያ ሕዝብ ወንድማማች ህዝብ እንደሆኑ የተናገሩት ዶር ያእቆብ፣ ጠቡና መለያየቱ የመጣዉ በመሪዎች ችግር ብቻ እንደሆነ ይገልጻሉ። «ተለያየትን አንቀርም። አንድ ቀን ተመልሰን አንድ መሆናችህ አይቀርም» ያሉት ዶር ያእቆብ ፣ የአሰብ ጉዳይ በሰላም የሚፈታበትንም አራት አማራጮችን አቅርበዋል።

የፈረደበትስ የኢትዮጵያ ሕዝብ እንጂ ግንቦት 7 እና የኤርትራ መንግስት አይደሉም! (ለአቶ ተክለሚካሄል አበበ፤ ጥያቄዎች ምላሽ ቢሆን) ያሬድ ኃይለማርያም

በመጀመሪያ በአቅርቡ በተከታታይ ለአንባቢያን ያቀረብኩዋቸውን ሁለት ጽሁፎች አንብበህና ጊዜህንም ወስደህ በዝርዝር ላቀረብከው የሙግት ሃሳብ ምስጋናዮ የላቀ ነው። ለነገሩ የጽሑፌም ዋና አላማ ጉዳዩን ሕዝብ እንዲያውቀው ብቻ ሳይሆን በተነሱት ነጥቦችም ዙሪያ በአንባቢዎች ዘንድ የውይይት ሃሳብንም በማጫር ጉዳዩ ተገቢውን ትኩረት እንዲያገኝም ጭምር ስለሆነ ያንተ ምላሽ እኔንም በዚሁ ጉዳይ ላይ በድጋሚ እንድመለስበት አድርጎኛል። ምንም እንኳን ባነሳሃቸው በርካታ ሃሳቦች ፍጹም የተለያየ አቋም ያለን ቢሆንም ከእንዲህ አይነቱ የውይይትና ሃሳብን ሥልጡን በሆነ መልኩ የማንሸራሸር ልምድ ከየኮምፒቱሩ ጀርባ ተደብቀው በፈረስ ስማቸው መረን የለቀቀ እና ድንቁርና የታከለበትን ስድባቸውን ለሚወረውሩት የሳይበር አርበኞች ትምህርት ሊሆን ይችላል ብዮ አምናለሁ፡፡ አንዳንዶቹ ከእኔም አልፈው የኢትዮጵያን ሕዝብ ጭምር ጸያፍ በሆነ መልኩ ለመዝለፍና ለማንቋሸሽ ሞክረዋል።

“ከኛም ቤት እሣት አለ !!” (ይፍሩ ኃይሉ )

“ለወደቀ ዛፍ ምሣር ይበዛብታል” እንደሚሉ ሆኖ ነው መሰል አገራችንን እትዮጵያንና ሕዝቧን ከያቅጣጫው የገጠማቸው ችግር ከመቼውም የበለጠ የሚያስደነግጥና፤ ሊታመንም በማቻልበት ሁኔታ በጆሮ ለመስማት እንኳ የሚቀፍና የሚዘገንን ነው። በአባቶቻቸን፤ በአያቶቻችንና በቅድመ አያቶቻቸን ደም ፍሳሽና አጥንት ክስካሽ ተፈርቶና ተከብሮ የነበረው ዳር ድንበሯ ዛሬ “የምትፈግ ገብተህ እግርህን ዘርግተህ ተዝናንተህ ፈንጪበት፤ ሁሉም በጅህ ሁሉም በደጅህ ይሁንል” የተባለ ይመስላል። የቤልጅየምን የቆዳ ስፋት የሚበልጥ ለም የኢትጵያ መሬት፤ ከግማሽ ጎንደር እስከ ጋንቤላ ድረስ ለሱዳን መንግሥት በገጸበከትነት ከመሰጠቱም በላይ እንደገና በዚሁ ባልታደለ አካባቢ የሚገኝ ለም መሬት፤ ከነዋሪው አርሶ አደርና አርብቶ አደር ሕዝብ፤ ያለ ፈቃዱና፤ለተነጠቀው ንብረቱና ሃብቱ ያለምንም የዋጋ ክፍያ፤ ለዘመናት ከኖረብት ከአያት ቅድ መአያቱ ቀዬ እየተፈናቅለ፤ በሱ ቦታ ዛሬ በአንድ ጀንበር ለተፈለፍሉ የወያኔ ቱጃሮችና፤ ለአረብ፤ለሕንድና ለሌሎች የውጪ አገር ባለሃብቶች እጅግ በሚገርምና በማይታመን ዝቅ ባለ ዋጋ እየተቸረቸረ ይግኛል።

የህወሓት ሰማዕታት አጭር ማስታወሻ (ናይ ህወሓት ሰማአታት ሐፂር መዘካከሪ)

1
ሰላሳ ዘጠኝ ዓመታት ወደኋላ…
“የአብዮቱ ደወል እየተደወለ ነው
ሕዝቦች ሆይ ተነሱ
ስለመብቶቻችሁም ቁሙ
ጠመንጃችሁን አንሱ
ጨቋኞቻችሁንም ታገሉ”
ይህ የመጀመሪያው የህወሓት መዝሙር ለ16 ዓመታት ያህል በሺ በሚቆጠሩ የትግራይ ወጣቶች አንደበት በሰሜን ኢትዮጵያ ተራራና ሸለቆዎች መካከል ተዘምሯል፡፡ የካቲት 11 ቀን 1967 ዓመተ ምህረትም እፍኝ የማይሞሉ ወጣቶች ማንም ቢሆን ‹ያደርጉታል› ብሎ ያላሰበውን ረዥሙን የትግል ምዕራፍ አንድ ብለው የጀመሩበት ዕለት መሆኑ አይዘነጋም፡፡ ርግጥ ነው እነዚህ መስራቾች ብዙሃኑን ለትግል ከቀሰቀሱበት አጀንዳ ባሻገር የትግራይ ሕዝብን የማይወክል ድብቅ ፖለቲካዊ ፍላጎት የነበራቸው መንደርተኞች ስለመሆናቸው ‹‹ከትግራይ ሪፐብሊክ›› እስከ ‹‹ቋንቋ ተኮር ፌደራሊዝም›› ድረስ የተሻሻሉ ፕሮግራሞቻቸውን ጨምሮ በርካታ ማሳያዎችን መጥቀስ ይቻላል፡፡

Thursday, February 13, 2014

ልፋ ያለው በሕልሙ ዳውላ ይሸከማል! ጠርናፊና ተጠርናፊ

ፕ/ር መስፍን ወልደ ማርያም
logopresentation
ሰሞኑን እንደአዲስ ሆኖ የሚወራው ስለጥርነፋ ነው፤ ጥርነፋ ከዲያብሎስ ፋብሪካ የወጣ የክፋትና የጭቆና መሣሪያ ነው፤ ሰዎችን በመጨቆንና በማሰቃየት፣ ምቾትና እንቅልፍ በማሳጣት፣ ፍርሃትንና ስጋትን በማሰራጨት ሕዝብን ለጥ-ጸጥ አድርጎ ለመግዛት የሚፈልጉ ጠርናፊዎች፣ አምባ-ገነኖች፣ ጨቋኞች፣ አፋኞች፣ ዘራፊዎች፣ ወሮበሎች፣ ምድራዊም ሆነ ሰማያዊ ሕግ የማይገዛቸው፣ አምላካቸው አድርገው የሚያገለግሏቸው ሎሌዎችን በሆዳቸው ገዝተው የሚያሰልፉ ናቸው፤  እንኳን የገጠር ልጆችና አኛም የአዲስ አበባዎቹ መሰንከል ምን እንደሆነ እናውቃለን፤ እንስሳትን (በቅሎዎችንና አህዮችን፣ አንዳንዴ በገግና ፍየልም) የፊት እግር ከኋላ እግር ጋር በአጭር ገመድ እያሰሩ እንደልባቸው እንዳይንቀሳቀሱ ማድረግ ነው፤ ሀብት በመሆናቸው ቢጠፉ ባለቤቶቹ ይጎዳሉ፤ ስለዚህ በየአካባቢያቸው ያለውን እየጋጡ ችለው እንዲኖሩ ለማድረግ ቀላሉ ዘዴ መሰንከል ነው፡፡

ሰው ለሆኑ ሰዎች በሙሉ! (በጋዜጠኛ ውብሸት ታዬ፤ ከዝዋይ ማረሚያ ቤት)

የነገሮች ሁሉ መድረሻ እስር ቤቶች እየሆኑ መጥተዋል፡፡

‹‹ይህንን ስለመሳሰሉ ጉዳዮች መወያየት ክልክል ነው፡፡›› በማለት በተንጎላጀጀ ድምፅ ጠባቂው ተናገረ፡፡ ቀጠል አደረገናም ‹‹መነጋገር የምትችሉት ስለቤተሰብ ጉዳዮች ብቻ ነው›› በማለት ተናገረ፡፡ ይህን ከላይ ያለውን ሐሳብ የሚመለከት ማንኛውም አንባቢ፣ ጉዳይ የተፈፀመው እዚህችው እማማ ኢትዮጵያ ሰማይ ስር ባሉ አጃኢበኛ እስር ቤቶች፣ ቤተሰብ መጠየቂያው እንደሆነ መጣራቱ አይቀርም፡፡

የጤፍ ምርትን ለውጭ ገበያ፣ ይቁም ሊባል የሚገባ!

አሰግድ ኣረጋ (ኮለምበስ – ኦሃዮ)
ሰሞኑን ስለጤፍ ምርታችን የባዕዳኑ ብዙሃን መገናኛ አጀብ እያሉን ነው፤ ለዘመናት የተደበቀው የዘሩ ገመና መጋለጡን እየነገሩን ነው፤ ስለያዘው ንጥረ ነገር፣ ስለጤናማነቱ፣ በምዕራቡ ገበያ ስለመፈለጉ፣ ከሁለም በላይ ስለ ውጭ ምንዛሪ ምንጭነቱ። ምግብነቱ ተትረፍርፎ የኢትዮጵያ ህዝብ ማስቀመጫ – ቦታ ያጣ ይመስል፣ የወንዙ ልጆች ጭምር ፣ ጤፍ-የጤፍ ዘር፣ እንጀራ ፣ ብሰኩት፣ ኬክ ሆኖ ምግብ በዝቶበት ለሚቀናጣው ለውጭ ገበያ እንዲነጉድ ከምዕራባውያኑ ጋር አብረን ከበሮ እየደለቅን ነው፤ አደብ ልንገዛ ይገባል።