Thursday, January 29, 2015

በኢትዮጵያ መንግስት በጥብቅ የሚፈለጉ 3 አርቲስቶች

Kibebeew geda

ከሮቤል ሔኖክ
እንዳለመታደል ሆኖ ኢትዮጵያ ውስጥ ሃሳብን በነፃነት ያለመግለጽ መብት አለመከበሩ ያጠቃው ጋዜጠኞችን ብቻ አይደለም። አርቲስቶችም ጋዜጠኞች ከሚከፍሉት መስዋእትነት ያልተናነሰ ትግል እያደረጉ ይገኛሉ። ኢትዮጵያ ውስጥ እንዳለመታደል ሆኖ የሃሳብን የመግለጽ ነጻነት በመገደቡ ዛሬ እንደ ታላቁ ጋዜጠኛ እስክንድር ነጋ፣ ርዕዮት ዓለሙና ተመስገን ደሳለን ያሉ ጋዜጠኞች ያልሆነ ክስ ተልጠፎባቸው በእስር ላይ ይገኛሉ። የእነዚ ታላላቅ ጋዜጠኞች ‘ወንጀል’ መንግስት እንደሚለው ሳይሆን የሕዝብን በደልና ብሶት ማሰማታቸው ብቻ ነው።
ዛሬ ዛሬ ደግሞ ላለፉት 23 ዓመታት ሃሳባቸውን በነጻነት ከሚገልጹት ጋዜጠኞች ባልተናነሰ በመንግስት ጥርስ እየተነከሰባቸው የሚገኙት የጥበብ ባለሙያዎች እየሆኑ ነው።
እንደሚታወቀው በስደት ዓለም ከ150 በላይ ጋዜጠኞች እንዳሉ ሁሉ ዛሬ ቁጥራቸው በዛ ያሉ አርቲስቶችም በስደት ይህንን ስርዓት በመሸሽ በስደት ላይ ይገኛሉ። ከነዚህ መካከልም የኢትዮጵያ መንግስት እንደታላቁ እስክንድር ነጋ አስሮ ለማሰቃየት ከሚፈልጋቸው ታላላቅ አርቲስቶች መካከል 3ቱ ዋነኞቹ ሲሆኑ ሌሎቹ ሁለቱ ደግሞ ገና መንግስት እያጎበጎበባቸው በመሆኑ የ3ቱን ገድል አሳይቻችሁ የሁለቱን እንስት አርቲስቶችን ማንነት አስተዋውቃችኋለሁ።

ትግሬ ብሎ ነገር…

አንዳንዶቻችን ኢህአዴግ ያጠፋውን ጥፋት ለትግሬና ለትግራይ ጠቅልላችሁ ለምን እንደምታስረክቡ አይገባኝም፡፡አንዳንዶቻችሁማ ብሶባችኃል ትንሽ ዕድልና ብዙ ሃይል ብታገኙ መታወቂያ እያያችሁ ይሄን ህዝብ ብትረፈርፉት ደስታችሁ መሆኑን ትሰብካላችሁ፡፡ወንድሞቼ ኢህአዴግ ከመላው ብሄረሰቦች የተውጣጡ እንከፎች የመሰረቱት ማህበር እንጂ ትግሬና ትግሬያዊያን የፈጠሩት ክስተት አይደለም፡፡
የአማራ መሬት ምርጥ ሰዎችን እንደማፍራቱ አዲሱ ለገሰ፣ታምራት ላይኔ፣አለምነው መኮነንን የመሰሉ በሰው ደም ሻወር የሚያምራቸው ሰዎችን አፍርቷል፡፡የኦሮሞ ህዝብ ታሪክን በብርሃን ያደመቁ ጀግኖችን እንደመውለዱ አባዱላ ገመዳ፣ሙክታር ከድር፣ግርማ ብሩን የመሰሉ አስረፍራፊዎችን ለኢህአዴግ አዋጥቷል፡፡ጉራጌ ካሱ ኢላላን፣ሲዳማ ሽፈራው ሽጉጤን፣ወላይታ ሃይለማሪያምን አሳድጓል፡፡ሶማሌ ፣ጋምቤላ ፣ሀረር ውስጥ ለተፈጠሩ እልቂቶች ምላጭ ሳቢዎቹ ፣አሰቃዮቹ ራሳቸው በአከባቢው ተወልደው ያደጉ ሳዲስቶች አልነበሩም?

Monday, January 26, 2015

የፍትህና የነፃነት ጥያቄያችን ደም በማፍሰስ አይቀለበስም!!!

ከአንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ የተሰጠ መግለጫ
====================================
ፓርቲያችን አንድነት ገዥው ፓርቲ፣ ምርጫ ቦርድና የገዥው ፓርቲ ልሳን በመሆን እያገለገሉ ያሉ ሚዲያዎች በመተባበር ከምርጫ ለማስወጣትና ተለጣፊ አንድነት ለመፍጠር የሚደረገውን ጥረት በመቃወም የተቃውሞ ሰልፍ መጥራቱ የሚታወቅ ነው፡፡
የተቃውሞ ሰልፉን ጥር 17 ቀን 2007 ዓ.ም እንደምናከናውን ለአዲስ አበባ መስተዳድር ብናሳውቅም መስተዳድሩ በ12 ሰዓት ውስጥ በፅሁፍ ምላሽ መስጠት ባለመቻሉ ሰልፉ እውቅና አለው፡፡ መስተዳድሩ ግን የተጣለበትን ሃላፊነት ከመወጣት ይልቅ ወደ ጎን በመግፋት የተወሰኑና የማይታወቁ ግለሰቦች ፔቲሽን ተፈራርመው አምጥተዋል በማለት ብዥታ ለመፍጠር ሞክሯል፡፡ ፓርቲያችን ህጉን ጠብቆ ህጋዊ የሆነ ሰልፍ ለማካሄድ ቢሞክርም አሁንም ሃላፊነት በጎደለው ሁኔታ የፓርቲያችን ከፍተኛ አመራሮች፣ አባላትና ደጋፊዎች ጭካኔ በተመላበት ሁኔታ ከፍተኛ ድብደባ ተፈፅሞባቸዋል፡፡ በተደጋጋሚ እንዳየነው ፖሊስ ደንብ ማስከበር ሲገባው አድሎ ለፈፀመው አካል በመወገን ድብደባ መፈፀሙ ከወገንተኝነት ያልፀዳ መሆኑን እንድናረጋግጥ አድርጎናል፡፡

ጥቁር ሽብር …በኢትዮጵያ ምድር!

ዳዊት ከበደ ወየሳ
January 26, 2015
(ኢ.ኤም.ኤፍ) በኢትዮጵያ ውስጥ በመንግስት ድጋፍ የሚደረገው የአሸባሪነት ተግባር እንደቀጠለ ነው። በከተሞች አካባቢ በህግ ሽፋን ዜጎች በአሸባሪነት ተፈርጀው ይታሰራሉ። ወደ ገጠር ስንሄድ ደግሞ፤ ኢትዮጵያውያን ያለምንም ጥያቄ በጠራራ ጸሃይ ተገድለው፤ ለአስከሬናቸው እንኳን ክብር ሳይሰጥ በአደባባይ ህዝብ እንዲያያቸው እና እንዲሸማቀቅ ይደረጋል። ይህ በኢትዮጵያ ታሪክ ውስጥ እጅግ ዘግናኝ የሆነ ጥቁር ሽብር እየተከናወነ ያለው፤ በዜጎች ላይ ነው። በፍርድ ቤት የሞት ፍርድ ተፈርዶባቸው ሳይሆን፤ የኢህአዴግ ደጋፊዎች ነን በሚሉ ሰዎች ድጋፍ የሚከናወን ነው – እንዲህ ያለው ግድያ።
በመንግስት የተደገፈ ጥቁር ሽብር በኢትዮጵያ
ከላይ በፎቶው ላይ የምታዩት አረመኔአዊ ተግባር በህወሃት የተፈጸመ ጥቁር ሽብር ነው:: የደርግን ቀይ ሽብር ያስታውሰናል::
አብዛኛው ግድያ ከመፈጸሙ በፊት ዜጎች ተደብድበው እና ተሰቃይተው ነው – የሚሞቱት። ለምሳሌ በዚህ ፎቶ ላይ የሚታየው ከተማ ውበቱ የተባለው ሰው ኢህአዴግን በመቃወሙ ነው የተገደለው። ሆኖም የታጠቀ ለማስመሰል ከገደሉት በኋላ ጠመንጃ እንዲያነግት ተደርጓል። ጠመንጃውም ሆነ አብሮት ያለው ዝናር ወይም ቦንብ ግን የከተማ ውበቱ ሳይሆን የራሳቸው የወያኔ ሰዎች ንብረት ነው። እንዲህ አይነቱ የቦንብ እና የባትሪ መያዣ በራሳቸው በወያኔ ሰዎች በእጅ እየተሰፋ የሚዘጋጅ፤ ሲሆን በፎቶው ላይ በሟች ከተማ ውበቱ ላይ ያንጠለጠሉት መሳሪያ እና የትጥቅ መያዣም የህወሃት ሰዎች መገልገያዎች ናቸው።

ያለ ነጻ ሚዲያ – ምርጫ ወይስ ቁማር?

የሰብዓዊ መብት ድርጅት ሰሞኑን ሥጋቱን ይፋ ሊያደርግ ነው!
hrw media freedom

ኢህአዴግ አሸነፈ፤ ፋና መሰከረ!

ምርጫ ያለ ነጻ ሚዲያ ተግባራዊ ሊሆን እንደማይችል ዓለምአቀፉ የሰብዓዊ መብት ተመልካች (Human Rights Watch) በያዝነው ሳምንት ማገባደጃ አካባቢ በኢትዮጵያ የሚዲያ ነጻነትን አስመልክቶ አጠቃላይ ዘገባ እንደሚያወጣ ተሰማ፡፡
ለጎልጉል፡ የድረገጽ ጋዜጣ መረጃውን ያቀረቡና ከዘገባው ጋር ተዛማጅነት ክፍሎች እንደተናገሩት የሰብዓዊ መብት ድርጅቱ ይህንን ዘገባ ያጠናቀረው በተጨባጭ ከሚዲያ ጋር በተያያዘ ሰለባ የሆኑትን በሚዲያው መስክ የተሰማሩትን በማነጋገርና የመጀመሪያ ደረጃ መረጃ በመሰብሰብ እንደሆነ ለማወቅ ተችሏል፡፡

የደደቢት ጉዞ መዘዝ፤ ከሰራዊት ፍቅሬ እስከ ታገል ሰይፉ

ክንፉ አሰፋ

በመጀመርያ ዶክተር ደብረ ጽዮን ገብረ ሚካኤል የህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ (ህወሃት) ደጋፊና ተደጋፊ የኪነጥበብ ባለሙያዎችን በሙሉ ጠሯቸው። ሰበሰቧቸው። እንዲህም አሏቸው። “ወደ ደደቢት አብራችሁን ትሄዳላችሁ፤ እዛ እንደደረሳችሁም አመጣጣችንንና አካሄዳችንን በደንብ አድርጋችሁ ታጤናላችሁ። ከዚያ ስትመለሱ ሁሉንም ነገር ለህዝቡ ትናገራላችሁ።…” Ethiopian puppet artists
በምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ማዕረግ የሃገር መሪ ሆነው የሚሰሩት እኝህ ሰው መልዕክታቸውን በዚህ አላበቁም። አይናቸውን ፈጠጥ፤ ጉሮሯቸውንም ጠረግ-ጠረግ አደረጉና ንግግራቸውን ቀጠሉ “ስለረጅሙና መራራው ትግላችን፤ ከጅምራችን እስከ አያያዛችን የታዘባችሁትን ሁሉ ንገሩን። ጥሩውንም ይሁን መጥፎውን ነገር ሳትደብቁ ተናገሩ።…”
ድምጻዊው በዝማሬ፣ ጸሃፊው በድርሰት፣ ተዋንያኑ በተውኔት ስለ ህወሃት የአርባ አመት ጉዞ እንዲመሰክሩ የተሰጠች ትእዛዝ መሆንዋ ነው። አጭር፣ ግልጽ እና ቀጭን መልዕክት ነበረች።

”የቃሊቲ ማጎሪያ ውስጥ የታሰሩ ተማሪዎች፣ ጋዜጠኞች፣ ፖለቲከኞች፣ የሃይማኖት መሪዎች፣ ንጹሃን ዜጎች፣ ስቃይ አሁንም ከፊቴ አለ፤ የሚሞቱት ሰዎች ሊረሱኝ አይችሉም” የስዊድን ጋዜጠኛ ማርቲን ሺብዬ

“በማዕከላዊ እስር ቤት ውስጥ ቶርቸር (አካላዊ ስቃይ) የሚፈጸምባቸው ጩኸታቸው ይሰማኛል፡፡ የቃሊቲ ማጎሪያ ውስጥ የታሰሩ ተማሪዎች፣ ጋዜጠኞች፣ ፖለቲከኞች፣ የሃይማኖት መሪዎች፣ ንጹሃን ዜጎች፣ ስቃይ አሁንም ከፊቴ አለ፤ የሚሞቱት ሰዎች ሊረሱኝ አይችሉም፤ የእስር ቤቱ ጠረንና ሽታ ይከተለኛል፤ በአካል ደህና ብመስልም አእምሮዬ ግን አሁን ድረስ ሰላም የለውም” በማለት የስዊድን ጋዜጠኛ ማርቲን ሺብዬ በተለይለጎልጉል የድረገጽጋዜጣ ተናገረ፡፡
ዮሐን ፔርሶን ኦጋዴን በረሃ
አንድ ዓመት ከሁለት ወር (14 ወራት) ከሥራ ባልደረባው ዮሐን ፔርሶን ጋር ኢህአዴግ አስሮት የነበረው ጋዜጠኛ ሺብዬ ለጎልጉል የአውሮጳ ዘጋቢ ይህንን የተናገረው በዖጋዴን ክልል የተፈጸመውን ጭፍጨፋ የሚያጋልጥ ዘጋቢ ፊልም መሰራጨቱን ተከትሎ ለቀረበለት ጥያቄ መልስ በሰጠበት ወቅት ነው፡፡

“ጋዜጠኝነት ወንጀል አይደለም”

journalism-620x310
ጎልጉል ድረገጽ ጋዜጣ
የሰብዓዊ መብት ጠባቂ የሆነው ድርጅት (ሂዩማን ራይትስ ዎች) “ጋዜጠኝነት ወንጀል አይደለም” በሚል ርዕስ ያወጣል ተብሎ የተጠበቀውን ዘገባ ማምሻው ላይ ይፋ አድርጓል፡፡ ከጥቂት ቀናት በፊት ጎልጉል የድረገጽ ጋዜጣ “ያለ ነጻ ሚዲያ – ምርጫ ወይስ ቁማር?” በሚል ርዕስ ባተመው ዜና ላይ ዘገባው እንደሚወጣ በተናገረው መሠረት ባለ 76 ገጽ ሪፖርቱ በሚዲያ አፈና ዙሪያ ዝርዝርና ወቅታዊ መረጃዎችን አውጥቷል፡፡
ኢህአዴግ በሚያደርስባቸው ስልታዊ አፈና፣ ማስፈራሪያ፣ ህይወት የማጥፋት ዛቻ፣ … ምክንያት በአሁኑ ጊዜ በትንሹ 22 የሚሆኑ ጋዜጠኞች በእስር ላይ እንደሚገኙ፤ ከ30 በላይ የሚሆኑ ደግሞ አገር ጥለው መኮብለላቸውን በዘገባው ተጠቁሟል፡፡ እንዲህ ያለው ገለልተኛ ሚዲያን የሚያፍን እና ከሜዳው የሚያስወጣ አሠራር ከወራት በኋላ ይካሄዳል ከሚባለው “ምርጫ” አኳያ የውድድሩን ሜዳ ከማጥበብ አልፎ እንዳይኖር እንደሚያደርገው የዘገባው ሃተታ ያስረዳል፡፡

Tuesday, January 20, 2015

ሥርዓቱ የምርጫ ካርድ ያልወሰዱትን ስኳር በመከልከል ማስፈራራት ጀምሯል

(ነገረ ኢትዮጵያ) በምስራቅ ጎጃም ዞን አነደድ ወረዳ የቦቀል ቀበሌ ነዋሪዎች የምርጫ ካርድ ስልልወሰዳችሁ ስኳር አይሰጣችሁም መባላቸውን ለነገረ ኢትዮጵያ ገለጹ፡፡ በአካባቢው ስኳርን ጨምሮ ሌሎች አቅርቦቶች በስፋት እንደሚጠፉ የተናገሩት ነዋሪዎቹ ዛሬ ጠዋት የቀበሌ ካድሬዎች በድምጽ ማጉያ ‹‹ዛሬ ስኳር ስለመጣ ቀበሌ ድረስ መጥታችሁ እንድትወስዱ፡፡ የመጣው ስኳር ውስን በመሆኑ ሊያልቅ ስለሚችል ዛሬውኑ መጥታችሁ እንድትወስዱ እናሳስባለን፡፡ ከዛሬ ውጭ ላታገኙ ትችላላችሁ፡፡›› እያሉ ሲለፉ እንዳረፈዱ ተናግረዋል፡፡

የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ነፃነትን የማስመለስ ትግሉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገለጸ

ዜጎች የምርጫ ካርድ እንዲያወጡ ጥሪ አቅርቧል
• ‹‹ምህዳሩ ካልተስተካከለ ምርጫው አንድ ቀን ሲቀረውም ቢሆን ከምርጫ ልንወጣ እንችላለን››
(ነገረ ኢትዮጵያ)
የ9ኙ ፓርቲዎች ትብብር ‹‹በነፃነት ለፍትሓዊ ምርጫ›› ዘመቻው ነፃነትን የማስመለስ ትግሉን አጠናክሮ እንደሚቀጥል ገለጸ፡፡ ትብብሩ ዛሬ ጥር 12/2007 ዓ.ም በሰጠው ጋዜጣዊ መግለጫ ኢህአዴግና ምርጫ ቦርድ አፈና እና ጫና እያደረጉ ቢሆኑም ነፃነትን ለማስመለስ የያዘውን ግብ ለማሳካት ወደኋላ እንደማይል ገልፀዋል፡፡
‹‹የኢህአዴግ ጨካኝነትና የምርጫ ቦርድ አጋፋሪነት ሊቀጥል ይችላል›› ያሉት የትብብሩ ሊቀመንበር ኢንጅነር ይልቃል ጌትነት ሆኖም የትግሉ አላማ ኢህአዴግን ማጋለጥ በመሆኑ የሚያስፈልገውን መስዋዕትነት እየከፈሉ ትግሉን እንደሚቀጥሉ ገልጸዋል፡፡ በተመሳሳይ ‹‹ህዝቡ ካርድ እንዲያወጣ ጥሪ ስናደርግ የፖለቲካ ምህዳሩ ተስተካክሏል እያልን አይደለም፡፡ እኛ አሁንም እያነሳን ያለነው የትግል ጥያቄ ነው›› ያሉት የትብብሩ ም/ል ሊቀመንበር አቶ ኤርጫፎ ኤርዴሎ የትብብሩ የትግል አላማ ይህን የተዘጋ ምህዳር ማስከፈት መሆኑን አብራርተዋል፡፡
semayawi party
ትብብሩ ‹‹የትግሉ ቀዳሚና ዋነኛ ባለቤት የሆንከው መራጩ ህዝብ ነጻነትና ክብርህን ለማስመለስ በምናደርገው ትግል በንቃት እንድታሳተፍ፣ ዛሬውኑ በመመዝገብ የሥልጣን ባለቤትነትህን የምታረጋግጥበትንና ይህን አምባገነናዊ ሥርዓት የምትቀጣበትን ትጥቅ ‹‹የምርጫ ካርድህ››ን በእጅህ እንድታስገባ›› ሲል ጥሪ ያቀረበ ሲሆን በአሁኑ ወቅት እንዲሻሻሉ የሚጠይቃቸው ጥያቄዎች የማይመለሱ ከሆነ እና ምህዳሩ ካልተስተካከለ ምርጫው አንድ ቀን ሲቀረውም ቢሆን ከምርጫ ልንወጣ እንችላለን ብሏል፡፡

ብአዴን ‹‹ሰለሞናዊ›› ስርወ መንግስት!? – (ሊያነቡት የሚገባ የአደባባይ ምስጢር)


የብርሐኔ አበራ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ቤተሰብ አባላት አቶ በረከት እና አዲሱ
የብርሐኔ አበራ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ቤተሰብ አባላት አቶ በረከት እና አዲሱ
በአንድ ወቅት ዜጋ መጽሔት ላይ ታትሞ የነበረና ለግንዛቤዎ ይጠቅምዎታል ብለን እንደገና ለዘ-ሐበሻ አንባቢዎች አቅርበናል።
በአንዳንድ የአገዛዝ ሥርዓቶች በሀብት፣ በመደብ፣ ወይም ዴሞክራሲያዊ ምርጫ፣ አልያም በዘር የተዋቀረ ሥርዓት ይኖራል፡፡ ለምሳሌ በአፄ ኃይለ ስላሴ ጊዜ የነበረው የስልጣን ፍልስፍና ከሰለሞን ስርዎ መንግስት የሚመዘዝ የዘር ሀረግ ባለቤት መሆንን ይጠይቅ እንደነበረ ሁላችንም የምናስታውሰው ነው፡፡ ከሰለሞን ስርዎ (Solomon Daynasty) መንግስት ውጭ ላሉና በዚያ የስልጣን ዘር ሀረግ ውስጥ ያሉ ሆነው በጉልበትም ይሁን በብልሃት ስልጣን ላጡት ስልጣን የሚሰጣቸው በጋብቻ ትስስር እንደነበረ ለማስታወስ የአፄ ኃይለስላሴ ልጆች ከማንና የት ተጋብተው እንደነበረ ማስታወሱ በቂ ምሳሌ ነው፡፡

ብአዴን ‹‹ሰለሞናዊ›› ስርወ መንግስት!? – (ሊያነቡት የሚገባ የአደባባይ ምስጢር)


የብርሐኔ አበራ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ቤተሰብ አባላት አቶ በረከት እና አዲሱ
የብርሐኔ አበራ ኃላፊነቱ የተወሰነ የግል ቤተሰብ አባላት አቶ በረከት እና አዲሱ
በአንድ ወቅት ዜጋ መጽሔት ላይ ታትሞ የነበረና ለግንዛቤዎ ይጠቅምዎታል ብለን እንደገና ለዘ-ሐበሻ አንባቢዎች አቅርበናል።
በአንዳንድ የአገዛዝ ሥርዓቶች በሀብት፣ በመደብ፣ ወይም ዴሞክራሲያዊ ምርጫ፣ አልያም በዘር የተዋቀረ ሥርዓት ይኖራል፡፡ ለምሳሌ በአፄ ኃይለ ስላሴ ጊዜ የነበረው የስልጣን ፍልስፍና ከሰለሞን ስርዎ መንግስት የሚመዘዝ የዘር ሀረግ ባለቤት መሆንን ይጠይቅ እንደነበረ ሁላችንም የምናስታውሰው ነው፡፡ ከሰለሞን ስርዎ (Solomon Daynasty) መንግስት ውጭ ላሉና በዚያ የስልጣን ዘር ሀረግ ውስጥ ያሉ ሆነው በጉልበትም ይሁን በብልሃት ስልጣን ላጡት ስልጣን የሚሰጣቸው በጋብቻ ትስስር እንደነበረ ለማስታወስ የአፄ ኃይለስላሴ ልጆች ከማንና የት ተጋብተው እንደነበረ ማስታወሱ በቂ ምሳሌ ነው፡፡

*** የምርጫ ሥነ-ምግባር ደንብ ፈርሙ ድራማ ምክንያቱ ግለጽ ነው፡፡ ***

ዋናው መመሪያና አቋም ይህና አብዮታዊ ዴሞክራሲ ሆኖ ሳለ ታዲያ ከምን ሥነ-አመክንዮ (logic) ወይም ምክንያት ተነስቶ ነው ወያኔ የምርጫ ሥነ ምግባሩን ፈርሙ የሚለው፡፡ እረ እንዲያውም ምርጫ ማካሄድስ ለምን ያስፈልጋልል? እዚህ ላይ ተረስተው ከሆነ ማስታወስ ያለብን ቁም ነገሮች አሉ፡፡ በ1997 ዓም ምርጫ ወቅት እኮ በኢህአዴግና በተቃዋሚ ፓርቲዎች መካከል የምርጫ ሥነ ምግባር ሰነድ ተፈርሞ ነበር፡፡ ምርጫውን በፍፃሜው ከታየው ቀውስ አላዳነውም እንጂ፡፡ በ2ዐዐ2 ዓም ምርጫ ወቀትም የሥነ ምግባሩን ደንብ ከፈረሙት ፓርቲዎች መካከል ዘግይቶም ቢሆን ደንቡን መፈረሙ ከችግር ስለአላዳነው መኢአድም ከስምምነቱ እራሱን ማግለሉ ይታወቃል፡፡ እንዲያው ለነገሩ ሁለትን አጋጣሚዎች አነሳሁ እንጂ የአገሪቱ ሕጎች ሁሉ የበላይ የሆነው ሕገ መንግሥት ላለፉት ሃያሶ ስስት ዓመታት እንደተፈለገው እየተጣሰ አይደለም ወይ? በቅን መንፈስ (in-good-faith) ለአገር፣ ለሕዝብ፣ ለታሪክ ታምነን ካልሰራን በስተቀር በአሁኑ ጊዜ ምንም ዓይነት ሰነዶች ቢፈረሙ ከወያኔ ጥቃት ያድናሉ ማለት ሞኘነት ብቻ ሳይሆን ወያኔንም አለማወቅ ማለት ነው፡፡

Friday, January 16, 2015

አንዳርጋቸው ጽጌ (ይናገራል ፎቶ)

ይህ ታሪካዊ ፎቶ የተገኘው ከጋዜጠኛ መሳይ መኮንን ነው:: አንዳርጋቸው ጽጌን ከነወታደር ልብሱ በረሃ ላይ ያሳየናል:: ፎቶው ታሪካዊ ከመሆኑ አኳያ ሊቀመጥ የሚገባው ነው:: ለዚህም ነው ይናገራል ፎቶ ብለን ያቀረብነው:: ፎቶውን ካሳየን አይቀር ታዋቂው ጸሐፊ ጸጋዬ ገብረመድህን አረአያ ከፎቶው በታች “አንዳርጋቸው ጽጌ ልዩ የኢትዮጵያ አፈር” ሲል በአውስትራሊያ ለሚታተመው አሻራ መጽሔት ላይ የጻፉትን ታሪካዊ ትንታኔም ዘ-ሐበሻ አስተናግዳዋለች::
andargachew Tisge
አንዳርጋቸው ጽጌ ልዩ የኢትዮጵያ አፈር
ከጸጋዬ ገብረመድህን አረአያ
በ1950 ዓ.ም. ደብረብርሀን በሚገኘው የሀይለ ማርያም ማሞ ሁለተኛ ደረጃ ትም ህርት ቤት ስገባ የዓጼ ዘርአ ያዕቆብ አንደኛ ደረጃ ትምህርት ቤት ዳይሬክተር የነበሩ ት አቶ ጽጌንና ባለቤታቸውን በየቀኑ አያቸው ነበር። ወይዘሮ አልታዬ ዘወትር በቀኝ እጃቸው እየደገፉት እሱ ድክ ድክ የሚልም ትንሽ ልጅ አይረሳኝም። የየዕለቱ ትርኢት ስለነበር . . . . ብዬ አልፌዋለሁ።

የፖለቲካ ምኅዳሩ እንዳይጠብ ጥንቃቄ ይደረግ!

የአንድ አገር ሉዓላዊነት ባለቤት ሕዝብ ነው፡፡ ይህ ማለት ደግሞ ከምንም ነገር በላይ የአገር የሥልጣን ባለቤት ሕዝብ ነው ማለት ነው፡፡ እንደ እኛ ባለ አገር መቼም ቢሆን ምርጫ ሲከናወን የሥልጣን ባለቤት ሕዝብ መሆኑ ተክዶ አያውቅም፡፡
9f82c54a890bb560467ea1718ee4a9e5_Lነገር ግን ሕዝብ ወሳኝ ሊሆንባቸው በሚገባ የምርጫ ሒደቶች ውስጥ ከሕዝቡ ይልቅ ጎልተው የሚታዩት የፖለቲካ ፓርቲዎች ናቸው፡፡ ምንም እንኳ የሕዝብ ድጋፍ ያላቸው የፖለቲካ ፓርቲዎች መሆናቸው ቢታመንም፣ በትንሽ በትልቁ በሚደረጉ ክርክሮችና ውዝግቦች የሕዝቡ ድምፅ ዝቅተኛ ሆኖ በጉልህ የሚሰማው የፓርቲዎች ድምፅ ነው፡፡ ሕዝብ ዳር ቆሞ ተመልካች ሳይሆን ወሳኝ መሆኑ አጽንኦት ሊሰጠው ይገባል፡፡

አንዳርጋቸው ጸጌ በህወሀት የሸፍጥ የምርመራ ወጥመድ ውስጥ

ከፕሮፌሰር አለማየሁ ገብረማርያም
ትርጉም በነጻነት ለሀገሬ
አንዳርጋቸው ጽጌ በህወሀት ወንድሞች ቡድናዊ የሸፍጥ ከበባ ስር
ቮልቴር (ፍራንኮይስ ማሬ አሮት) እንዲህ በሚለው ምልከታቸው በስፋት ይታወቃሉ፣ “አንድ ሰው ከሚሰጣቸው ምላሾች ይልቅ በሚያቀርባቸው ጥያቄዎች ምንነቱ ይገመገማል፡፡“
andargachew Tsege
ቮልቴር ብልህነትን በተላበሰ መልኩ እንዲህ የሚል ምልከታም በተጨማሪ አካሂደዋል፣ “ጥሩንባቸውን እየነፉ እጅግ ብዛት ያለውን ህዝብ ካስጨረሱ ገዳዮች በስተቀር ሁሉም ህይወትን ያጠፉ ነብሰ ገዳዮች ይቀጣሉ፡፡“ ይኸ ነገር እንዴት ያለ እውነታ ነው እባካችሁ! አሁን በህይወት የሌለው መለስ ዜናዊ እና እራሱን ህዝባዊ ወያኔ ሀርነት ትግራይ (ህወሀት) እያለ የሚጠራው የወሮበላ ቡድን በሺዎች የሚቆጠሩ ኢትዮጵያውያን/ት ወገኖቻችንን በመግደል ከምዕራቡ ዓለም የሚደረግላቸውን እርዳታ በመቀበል ፌሽታ እና ደስታ በማድረግ ከህዝብ እልቂት ሰይጣናዊ ወንጀሎቻቸው ለማምለጥ ላይ ታች በማለት በመንፈራገጥ ላይ ይገኛሉ፡፡

ከሆቴሉ ጀርባ… በወላፈኑ ውስጥ የሚታየው – ፍጹምዘአብ አስገዶም ማን ይሆን?

ሰሞኑን የኢትዮጵያ ጥንታዊ ቅርስ የነበረው ጣይቱ ሆቴል በእሳት ወደመ:: ከዚሁ ጋር ተያይዞ ታዲያ “አቃጠሉት” እና “አቃጠሉበት” የሚሉት ድምጾች በርክተዋል:: “አቃጠሉበት” የሚለውን የጨዋታ ክር መምዘዝ ከጀመርን; የቤቱ ባለቤት ፍጹምዘአብ ጋር ያደርሰናል:: ፍጹምዘአብ የትግራይ ተወላጅ ነው:: ግን ደግሞ የትግራይ ተወላጅ ስለሆነ ከስልጣን ዙፋን ላይ አልተቀመጠም:: ይልቁንም በዘመነ ኢህአዴግ ከ6 አመታት በላይ የወያኔን እስር ቤትን ቀምሶ የወጣ ሰው ነው::
አሁን በተቃጠለው የጣይቱ ሆቴል ምክንያት ስለቃጠሎውም ሆነ ስለእቴጌ ጣይቱ ሆቴል ብዙ እየተባለ ነው:: ከዚህም በላይ ብዙ ሊባል ይችላል:: ምንም ተወራ ምን – ቢያንስ መሰረቱን እውነት ያደረገ ወሬ ይመረጣል:: ፍጹምዘአብ የትግራይ ተወላጅ ሆኖ የህወሃት ደጋፊም ተቃዋሚም ስላልሆነ እንደማንፈርድበት ሁሉ – የነጻ ፕሬስ ተጋድሎውን ብዙ በመታሰር እና ባለመታሰሩ ኢትዮጵያዊነቱን ልንለካው አንችልም:: እንደ’ውነቱ ከሆነ; ዘ ሞኒተር ጋዜጣን በሳምንት ሶስቴ ከመታተም አልፎ በየቀኑ የሚታተም የመጀመሪያ እንግሊዘኛ ጋዜጣ እንዲሆን አድርጓል:: ጋዜጣው ከዘመኑ ጋር እንዲሄድ ብቻ ሳይሆን የራሱ ማተሚያ ቤት እንዲኖረው ማድረጉ በራሱ፤ መጋነን ባይገባውም በነጻው ፕሬስ ታሪክ ውስጥ ስፍራ ሊሰጠው ይገባል::

ወያኔን ሁለት ግዜ እንገድለዋለን!!! -ከ-ከተማ ዋቅጅራ

ወያኔና ንብ ከአፋቸው ማር  ከሆዳቸው መርዛማነት አላቸው።
rtምርጫ ሊደርስ በወራቶች የሚቆጠር ግዜ ቀርቶታል ልዩ ምልክቱ ንብ ስሙ TPLF ስራው ጥፋት። ንብ የመረጡት ሰራተኛ ነኝ ለማስባል በሆዳቸው ያለውን መርዝ መናገር የማይወዱ ግን መርዘኝነታቸውን ህብረተሰቡ የተረዳቸው በዲሞክራሲ ስም አደናቋሪ የግን ሞት (ግንቦት) ምርጫ እየደረሰ ነው።በግን-ሞት (በግንቦት) ምርጫ ንብ ይዘው ማሯን ሳያሳዩ መርዟን ታቅፈው ሳይመረጡ ተመረጥን ሳይሾሙ ተሾምን ሳይፈለጉ ተፈለግን የሚሉበት ግዜ እየተቃረበ ነው። ወያኔ ከህዝቡ ልቦና ከወጣ ህዝቡም አንቅሮ  ከተፋው ቆይቷል። በመርዝ የተለወሰ የጣፈጠ የሚመስል ወሬ ለአለም መንግስታት በተቆጣጠረው  ሚዲያ እና በተለያዩ አገራት በሚጋበዘው መድረክ ላይ ዲሞክራሲ፣ ልማት፣ የህዝቦች እኩልነት፣ እያለ በሚደሰኩረው ዲስኩር ካደጉ አገራት እርዳታን በመለመን እና ብድራትም በመሰበሰብ እራሱን በማደለብ አገሪቷን እና  ህዝቧን ደሃ በማድረግ ሊቆይ የሚችልበትን የጥፋት ስራውን ሽር ጉድ ማለት ከጀመረ  ውሎ አድሯል። ወያኔ  በመርዝ የተለወሰ  ማር በየግዜው በማቅረብ በሆዱ ያለውን መርዝ መሸፈኛ አድርጎ  በምርጫ ሸፍኖ ቆይቷል። እስቲ ንብና ወያኔን እንዴት እንደተስማሙ እናያለን።

ወያኔ ኢትዮጵያን አፍርሶ ወደ ጉሬው ለመግባት የመጨረሻ መሠናዶውን እያደረገ ነው

  • የትግሬ-ወያኔዎች ከተለያዩ ጎሣዎች እና ነገዶች ሰዎችን መልምለው እና አደራጅተው፣ እንዲሁም የወታደራዊ፣ የደህንነት፣ የአደረጃጀት፣ የአመራር እና የቁጥጥር ሥራ የሚሠሩ የትግሬ-ወያኔዎች መድበው በከፍተኛ ሚሥጢር ኢትዮጵያን የማፈራረስ ሤራ እየተዶለቱ መሆኑን በተጨባጭ መረጃዎች አረጋግጠናል።
የትግሬ-ወያኔ የመጨረሻ ግብ ኢትዮጵያን በመበታተን፣ የትግራይ ረፑብሊክ መመሥረት መሆኑን በ1968 ዓ.ም. ይፋ ባደረገው ፕሮግራሙ መሠረት ላለፉት ፵(አርባ) ዓመታት ያደረገው ጉዞ ያሣያል። በጉዞው የኢትዮጵያን የረጅም ዘመን ታሪክ ክዶ በመቶ ዓመት መገደቡን፣ የትግሬ-ወያኔ መሪዎች እና አባሎች በተደጋጋሚ በጻፉዋቸው መጻሕፍት እና በየአጋጣሚው ባደረጉዋቸው ንግግሮች ለሕዝብ ይፋ ማድረጋቸው ይታወቃል። «ኤርትራ በኢትዮጵያ በቅኝ ግዛትነት የተያዘች ናት፤ ስለሆነም ሻዕቢያ የሚያካሂደው የመገንጠል እና የነፃነት ጥያቄ ተገቢ እና ትክክል ነው።» ብለው፣ ከሻዕቢያ በላይ ሻቢያ ሆነው፣ የትግራይን ልጆች የጦር ማገዶ በማድረግ ኤርትራን ማስገንጠላቸው ማንም ሊያስተባብለው የማይችለው ሃቅ ነው።

ወገንተኛ ከሆነ የምርጫ ኮሚሽን ነጻና ፍትሃዊ ምርጫ አይጠበቅ – ሸንጎ


shengoህወሓት/ኢህአዴግ  አሁንም  እንደገና  በሀገሪቱ  ምርጫ ሂደት ብቻውን ሮጦ  ብቻውን ለማሸነፍ እንዲችል አስከፊ አፈናውንና እመቃውን  አጠናክሮ ቀጥሏል።  ተፎካካሪ የሆኑ የፖለቲካ ድርጅቶችን ከፖለቲካው በተለይም ከምርጫው ሂደት ተገፍትረው እንዲወጡ ለማድረግ ሳይታክት እየሰራ ነው። በሰሞኑም በአንድነት፣ በመኢአድና በሰማያዊ ፓርቲ ላይ የምርጫ ቦርድ ተብየውን በመጠቀም የሚደረገው ማዋከብ ህወሓት/ኢህአዴግ በምርጫው ሂደት ውስጥ ብቻውን ከራሱ ጋር እንዲቀር ለማድረግ የሚያደርገው ጥረት አንድ ክፍል መሆኑ የማይታበል ነው። በመሆኑም የኢትዮጵያ ሕዝብ የጋራ ትግል ሸንጎ ( ሸንጎ) ይህ የወያኔ/ ኢህአዴግ ቀኝ እጅ የምርጫ ቦርድ ተብየ እየወሰደ ያለውን አይን ያወጣ የአድሎ እርምጃ በጥብቅ ያወግዛል።

ባለጌና ውሻ በቤቱ ይኮራል

ነፃነት ዘለቀ (nzeleke35@gmail.com)
የመጻፍ ፍላጎት በጭራሽ አልነበረኝም፡፡ ይሁን’ይ ዛሬ እንደወትሮው አላስችልህ አለኝ፡፡ መጻፍ የማልፈልገው መጻፍን በመጥላት ሣይሆን የሀገራችን ችግር ከመጻፍም፣ ከማንበብም፣ ከመመልከትና እጅን አጣምሮ በመቀመጥ በቁጪት ከመብከንከንም በእጅጉ ያለፈ በመሆኑ ነው፡፡ አዎ፣ ጊዜው የወሬና የሀተታ ሣይሆን የተግባር መሆን ይገባዋል – ልብ ላለው(2)፡፡ ብዙዎች – እኔንም ጨምሮ – ላለፉት ሃያ ምናምን ዓመታት በከንቱ ኃይላችንን መጨረሳችንን ሳስበው ይገርመኛል፡፡ እነሱ ላይሰሙ ጆሯቸውን እንደዘጉና ዐይናቸውን እንደጨፈኑ፣ እኛም መለያየታችንና ሥልትአልባነታችን ላያርመን በግትርነት እንደተጓዝን ግማሽ ምዕተ ዓመት ሊጠባ የቀሩት በጣት የሚቆጠሩ ዓመታት ብቻ ናቸው – ሚሌኒየማዊ ከፍተኛው ዕድለቢስነት፡፡
wendimagegn Gashu
ዛሬ ያለመናገር የራስ በራስ ማዕቀቤን ያስነሣኝ በወንድማገኝ ጋሹ ቤተሰብ ላይ በወያኔ የተወሰደው “ለስላሳ” እርምጃ ነው፡፡ የሕጻናቱ አምላክ ጠብቋቸው እንጂ ወያኔን ምንም ነገር ከማድረግ የሚያግደው አንዳች ምድራዊ ሕግ የለም፡፡ ይህ የታወቀ እውነት ይመስለኛል፡፡ ወያኔ የበቀል አባት፣ የክፋት አቅማዳ፣ የመድሎና ዘረኝነት አጋፋሪ፣ የጭካኔ ምንጭና የውሸት ንጉሠ ነገሥት ነው፡፡ ሰሞኑን እንኳን ስንትና ስንት ወያኔያዊ ሀገርና ሕዝብ የማጥፋት “ጀብድ” እየፈጸመ አይደለምን? ደናቁርቱና ነገን ፈጽሞ የማያዉቁት የወያኔ ጭፍራዎች በፍርደኛ ወታደራዊ መኮንኖች ላይ ሣይቀር ግድያና የእሥረኞች ጠለፋ ያካሄዱት በዚህ ሰሞን ነው፤ ከትግሬነት በዘለለ ራሳቸውን ትንሽ ከፍ አድርገው ማየት የተሣናቸው ፍጹማዊ ደንቆሮና ዕውር ወያኔዎች ላልተወሰነ ጊዜ ጋብ አድርገውት የነበረውን የኢትዮጵያን ቅርሦች ማቃጠላቸውን የቀሰቀሱት በዚህ ሰሞን ነው፤ … ስለሆነም የወንድማገኝ ቤተሰቦች በፈረንጅኛው አጠራር ፓስፖርታቸው ላይ “ዲፖርት” ተብሎ ተመትቶባቸው ከሀገራቸው መባረራቸው እንደጽድቅ የሚቆጠር እንጂ ወያኔ ሊኮነንበት አይገባም ብል ብዙም አላገነንኩም፡፡

Wednesday, January 14, 2015

የቃጠሎው መንስዔ ምንም ይኹን ምን ጣይቱ ሆቴል ወደቀደመ ይዞታው ይመለስ!!!

የቃጠሎው መንስዔ ምንም ይኹን ምን ጣይቱ ሆቴል ወደቀደመ ይዞታው ይመለስ!!!
በ1898 ዓ.ም የጣይቱ ሆቴል ተመሠረተ። ከቤት ውጪ ምግብ በገንዘብ ገዝቶ መመገብ እንደ ትልቅ ነውር በሚቆጠርበት በዚያ ዘመን ሆቴል ለማቋቋም ማሰብ የሩቅ ዓላሚ ሰው ሥራ ነው። ዳግማዊ ምኒልክ ይኼን ሆቴል ከፍተው መኳንንቶችንና ባላባቶችን እየጋበዙ ወደ ዘመናዊነት የሚያሸጋግረውን የቱሪዝምና የሆቴል ሥራ ሀ ብለው የቀደዱት ከዛሬ 109 ዓመት በፊት ነበር . . . በጥንቷ መሀል አራዳ በአሁኗ ፒያሳ እምብርት ላይ። በዓለም ላይ ታላቅ ዝናን ያተረፈው ሂልተን ሆቴል የተመሠረተው ጣይቱ ሆቴል ከተመሠረተ ከ20 ዓመት በሁዋላ እ.ኤ.አ. በ1925 ዓ.ም ነው። ጎበዝና ታታሪ . . . ለአገር የሚቆረቆርና ለቅርስ ግድ የሚለው . . . መንግሥት ቢኖረን ኖሮ በዓለም ላይ ካሉ ጥንታዊ ሆቴሎች አንዱ ባስባልነው ነበር። ያ ሳይኾን ቀርቶ በእሳት ወደመ ለሚል አሳዛኝ ዜና ተዳረገ፤ ተዳረግን።

Monday, January 12, 2015

የአርቲስት አስቴር በዳኔና ሳሞራ ፍጥጫ በደደቢት በረሃ

…አርቲስት አስቴር በዳኔ ከተቀመጠችበት ወደፊት ወጥታ ማይኩን ስትጨብጥ ፍርኃት ቢጤ እንደወረራት ከመጀመሪያው ያስታውቃል፡፡ ‹‹በጣም ነው የሚያስፈራው፤›› በማለት የጀመረችውን አስተያየቷን የያዘችውን ማስታወሻ እያነበበች አስተያየት መስጠት ቀጠለች፡፡
‹‹ይህንን ዕድል ተመቻችቶልን በቴሌቪዥን ስናየው የኖርነው ታሪክ ለማየት ስለቻለን እጅግ ከፍተኛ ደስታ ተሰምቶኛል፡፡ በፊት የነበረኝ ያልተጨበጠ አመለካከት በመረጃ የተደገፈ ሆኗል፤›› በማለት ሐሳቧን ቀጠለች፡፡ ‹‹እውነትን መናገር እወዳለሁ፡፡ የሐሳብ ነፃነትም አለ፡፡ በእርግጥ የፖለቲካ ሰው አይደለሁም፤›› በማለት ታዳሚዎችን ፈገግ ያሰኘች ሲሆን፣ በሒደትም የፍርኃቷ መጠን እየቀነስ የመጣ ይመስላል፡፡

ሳዲቅ አህመድ ለዛ ባለው አነጋገሩ ያላደረግናቸዉ ልናደርጋቸዉ የሚገቡ ነገሮችን ይጠቁመናል

ዳላስ ላይ በተደረገ የኢሳት ገቢማሰባሰብ ዝግጅት ላይ ጋዜጠኛና አክቲቭስት ሳዲቅ አህመድ ለዛ ባለው አነጋገሩ በትግሉ ያላደረግናቸዉ ልናደርጋቸዉ የሚገቡ ነገሮችን ይጠቁመናል:: ያድምጡት – ያተርፉበታል::
https://www.youtube.com/watch?v=VrUaMz2plXE#t=211

ጣይቱ ብጡል

ጀግናዋ ጎንደሬ ጣይቱ ብጡል የተንጎራደደችበት ለሃገራችን ኢትዮጲያ የስልጣኔ ምልክት የነበረው ጣይቱ ሆቴል ሲቃጠል አንጀቴ ቅጥል ነው ያለው ፡፡
ያቺ ያገር እናት እመት መላይቱ
ዛሬም በልቤ ውስጥ በርታለች ጣይቱ
ከሃይለስላሴ ዘውድ መጫን በኋላ ታሪኳ ሆን ተብሎ እንዲደበዝዝ የተደረገችው የደብረታቦሯ የብጡል ወሌ ልጅ ጣይቱ በአፍሪካ ምድር በጊዜው እንደሷ ገናና ጀግና ሴት ተነስቷል ብሎ መናገር ይከብዳል፡
አንዳንድ የታሪክ ጸሃፊያን የአድዋ ድል በጣይቱ ብጡል ሞራል የተሰነቀ ድል ነው ብለውላታል እቴጌ ጣይቱ ንጉስ ምኒሊክ ግዛቱን ለማስፋፋት እና ማእከላዊ መንግስት ለማቋቋም በነበረው የመስፋፋት ፍላጎት ወደ ደቡብ እና ወላይታ ለመዝመት ባቀደ ጊዜ የምኒሊክ ጦር የሚወስደው ጭካኔ የተሞላበት ድርጊት ላይ ከፍተኛ ተቃውሞ ስለነበራት ከመኳንንቱ ጋር በከፍተኛ ሁኔታ በብስጭት ትከራከር እንደነበት ይነገርላታል፡፡

የጠሀይቱ ስንቅ ቤት ቃጠሎ ታላቅ የሆነ ታሪካዊ ጥሪ ነው፣ታሪክ የሌለው ህዝብ አንሁን፣በድሮ አንድነታችን እንፅና!!

ጠሀይቱ ስንቅ ቤት
(ጣይቱ ውቴል)-
ይህ ሜዳው ላይ የሚታየው ግርግር እ.ኤ.አ በ1925 ዓ.ም ላይ የአፋር ማህበረሰብ ልዑካን ዘውዱን ተነጥቆ ዘብጥያ የወረደውን ልጅ እያሱን ለመጠየቅ ከብዙ ቀናት የእግር ጉዞ በሁዋላ አዲስ አበባ እንደደረሱ በዝች ታሪካዊ ውቴል ፊት ለፊት ከምሳ ግብዣው ቀድመው የተቀረፁት ታሪካዊ ምስል ነው።እንዲሁም በ110 ዓመት እድሜዋ ውስጥ ከዚህ በፊት እና ከዚህ በሁዋላ የተደረጉ የተለያዮ ዕልፍ ዐእላፍ ውስጥ ታሪካዊ ትዕይንቶች በዝች ታሪካዊ ውቴል ውስጥ ተፅፈው በሰነድ ይገኛሉ።

ሕወሃት በመንግስት ስልጣን ባለቤትነትና በወንበዴነት መሐል ያለው ልዩነት ተምታቶበታል

ኢትዮጵያን በግፍና በዝርፊያ የሚገዛው የህወሀት ጉጅሌ በመንግስትነትና በወንበዴነት መሀል ያለውን ልዩነት ከ፪፫ ዓመት ስልጣን ዘመን ብኋላ እንኳን ሊገለጥለት አልቻለም። ወይም እንዳመችነቱ ሁለቱን እያምታታ መቀጠሉን እንደብልህነት ቆጥሮታል። መንግስት መሆንንና ባለህገመንግስት መባልን ከመቆነጃጃ ኩልነት ባልተናነሰ በለጋሾቻቸው ባዕዳን ፊት ይጠቀሙበታል እንጂ ለኛ ለዜጎቹማ ወንበዴነታቸውን ሊደብቁን እንኳን አይጨነቁም።
በቅርቡ ህወሀት የትግራይ ሪፐብሊክ ለማቋቋም የክህደት ተግባሩን የጀመረበትን ፵ኛ ዓመት በዓሉን ትግራይ ውስጥ በማክበር ላይ ሳለ የቀድሞው የህወሀት ታጋይ ያሁኑ የሀገሪቱ ጦር ሎች ኤታማዦር ሹም ተብዬው ሳሞራ የኑስ የህወሀት መንግስት ያገራችን ገበሬ ወፎችን ከማሽላው ለመከላከል እንደሚጠቀምበት መስፈራሪቾ የሚጠቀምበት ሕገ መንግስት ላይ የተጠቀሰውን የሀገሪቱን ሰራዊት የፖለቲካ ገለልተኝነት ድንጋጌና ሰራዊቱ “ከፖለቲካ ወገንተኝነት ነጻ ይሆናል” የሚለውን የይስሙላ ህግ ባደባባይ አውልቆ ጥሎ ተቃዋሚዎችን የሚወነጅል ሰፊ ንግግር ሲያደርግ ተደምጧል። ሳሞራ ይህን ንግግር በሚደረግበት ቦታ አፋቸውን ከፍተው ከሚያደምጡት ውስጥ የሀገሪቱን መንግስት እንዳሻቸው የሚዘውሩት የወያኔ ሹማምንት ነበሩ። በዚህ ንግግር ውስጥ ተቃዋሚ ፓርቲዎች የባዕዳን መሳሪያ ሆነው የሀገሪቱን ሉዓላዊነት እንደሚፈታተኑ ሀይሎች በመቁጠር ፍጹም ሀሰትና ጅምላ ፍረጃ ሲያደርግ “እረ ይህ ነገር በመደበኛ ስራህ የስራ ዝርዝር ውስጥ አለመኖር ብቻ ሳይሆን የተከለከለ ነው” ያለው አልነበረም።

ወያኔ ኢትዮጵያን አፍርሶ ወደ ጉሬው ለመግባት

ሞረሽ ወገኔ የዐማራ ድርጅት     ቅዳሜ ጥር ፪ ቀን ፪ሺህ፯  ዓ.ም.                         ቅፅ ፫ ፣ ቁጥር ፰
የመጨረሻ መሠናዶውን እያደረገ ነው
· የትግሬ-ወያኔዎች ከተለያዩ ጎሣዎች እና ነገዶች ሰዎችን መልምለው እና አደራጅተው፣ እንዲሁም የወታደራዊ፣ የደህንነት፣ የአደረጃጀት፣ የአመራር እና የቁጥጥር ሥራ የሚሠሩ የትግሬ-ወያኔዎች መድበው በከፍተኛ ሚሥጢር ኢትዮጵያን የማፈራረስ ሤራ እየተዶለቱ መሆኑን በተጨባጭ መረጃዎች አረጋግጠናል።
ethiopia-map
የትግሬ-ወያኔ የመጨረሻ ግብ ኢትዮጵያን በመበታተን፣ የትግራይ ረፑብሊክ መመሥረት መሆኑን በ1968 ዓ.ም. ይፋ ባደረገው ፕሮግራሙ መሠረት ላለፉት ፵(አርባ) ዓመታት ያደረገው ጉዞ ያሣያል። በጉዞው የኢትዮጵያን የረጅም ዘመን ታሪክ ክዶ በመቶ ዓመት መገደቡን፣ የትግሬ-ወያኔ መሪዎች እና አባሎች በተደጋጋሚ በጻፉዋቸው መጻሕፍት እና በየአጋጣሚው ባደረጉዋቸው ንግግሮች ለሕዝብ ይፋ ማድረጋቸው ይታወቃል። «ኤርትራ በኢትዮጵያ በቅኝ ግዛትነት የተያዘች ናት፤ ስለሆነም ሻዕቢያ የሚያካሂደው የመገንጠል እና የነፃነት ጥያቄ ተገቢ እና ትክክል ነው።» ብለው፣ ከሻዕቢያ በላይ ሻቢያ ሆነው፣ የትግራይን ልጆች የጦር ማገዶ በማድረግ ኤርትራን ማስገንጠላቸው ማንም ሊያስተባብለው የማይችለው ሃቅ ነው።

Sunday, January 11, 2015

ሰበር ዜና ከኤርትራ አርበኞች ግንባር እና ግንቦት 7 አግአዴን አዲስ የጋራ ጥምረት ተመሰረተ አንድነት ሀይል ነው



ሰበር ዜና ከኤርትራ
አርበኞች ግንባር እና ግንቦት 7 አግአዴን አዲስ የጋራ ጥምረት ተመሰረተ አንድነት ሀይል ነው

ምርጫ ቦርድ በአንድነት ጠቅላላ ጉባዔ አልገኝም አለ

የብሄራዊ ምርጫ ቦርድ አንድነት ፓርቲ በጠራው ጠቅላላ ጉባዔ ላይ እንደማይገኝ ገለጸ። ምርጫ ቦርድ በአራት ቀናት ዉስጥ አንድነት ጠቅላላ ጉባኤ ጠርቶ አመራሮችን በሚስጥር አሰጣጥ መምረጥ እንዳለበት መናገሩ ይታወሳል። ሆኖም ትላንት አርብ በምርጫዉ ታዛቢ እንዲልክ በደብዳቤ የተጠየቀው ምርጫ ቦርድ “አየለ የሚባል ሰው ሌላ የአንድነት ጠቅላላ ጉባኤ ይደረጋል የሚል ደብዳቤ ስላሰገባ፣ በሁለት ቦታ መገኘት አንችልም” የሚል ምላሽ ሰጥቷል።

ጣይቱ ሆቴል በእሳት አደጋ ወደመ

በኢትዮጵያ ታሪክ ጥንታዊው እና የመጀመሪያው ዘመናዊ ሆቴል – የእቴጌ ጣይቱ ሆቴል መሆኑ ይታወቃል:: ሆቴሉ 109 አመታትን ያስቆጠረ ነው:: ይህ ጥንታዊ ሆቴል ዛሬ ጠዋት በተነሳ ቃጠሎ ጋይቷል:: በፒያሳ እና በአካባቢው ጥቁር ጢስ ወደ ሰማይ እየተንቧለለ አሁንም ድረስ እየታየ ሲሆን; በዚህ ጥንታዊ ቅርስ መውደም ብዙዎች ከልብ አዝነዋል:: አንዳንድ የአይን ምስክሮች እንደሚሉት ከሆነ – የ እሳት አደጋ መኪና በቅርብ ርቀት ላይ (አራዳ ጊዮርጊስ) የሚገኝ ሲሆን በቃጠሎውም ወቅት በቦታው ደርሶ ነበር:: ነገር ግን እዚያ ደርሰው በሚከፈላቸው ገንዘብ ላይ ሲደራደሩ እሳቱ እየተባባሰ መምጣቱን ገልጸዋል::

ምርጫ ቦርድ በአንድነት ጠቅላላ ጉባዔ አልገኝም አለ

የብሄራዊ ምርጫ ቦርድ አንድነት ፓርቲ በጠራው ጠቅላላ ጉባዔ ላይ እንደማይገኝ ገለጸ። ምርጫ ቦርድ በአራት ቀናት ዉስጥ አንድነት ጠቅላላ ጉባኤ ጠርቶ አመራሮችን በሚስጥር አሰጣጥ መምረጥ እንዳለበት መናገሩ ይታወሳል። ሆኖም ትላንት አርብ በምርጫዉ ታዛቢ እንዲልክ በደብዳቤ የተጠየቀው ምርጫ ቦርድ “አየለ የሚባል ሰው ሌላ የአንድነት ጠቅላላ ጉባኤ ይደረጋል የሚል ደብዳቤ ስላሰገባ፣ በሁለት ቦታ መገኘት አንችልም” የሚል ምላሽ ሰጥቷል።

Friday, January 9, 2015

አምባገነኑ የወያኔ መንግስት አቶ አንዳርጋቸው ፅጌን በአሸባሪነት የከሰሰባቸው ዝርዝርና የክሱ ይዘት።

አዲስ አበባ፣ ሀምሌ 14፣ 2006 (ኤፍ.ቢ.ሲ.) አቶ አንዳርጋቸው  ፅጌ የፌደራል አቃቤህግ በ2001 ዓ.ም አቶ ተፈራ ማሞን ጨምሮ 46 ሰዎች በሽብር ወንጀል ክስ ሲመሰርትባቸው፤ 39ኛ ተራ ቁጥር ላይ ነበር ስማቸው የሰፈረ ሲሆን፥ በወቅቱ እድሜያቸው 53 አመት ነበር ።
       አቃቤህግ አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን ጨምሮ ሁሉንም ተከሳሾች ራሱን የዴሞክራቲክ ጋርድ ብሎ በሚጠራው የሽብር ቡድን ውስጥ ከአባልነት አስከ አመራርነት ተሳትፎ አድርገዋል በሚል ነው የከሰሳቸው ፤ ይሄ የሽብርና የአመጽ የሲቪል ቡድን በህቡዕ የተደራጀው በ1998 ዓ.ም ነው።
ቡድኑ በ2000 ዓ.ም መንግስትን በሃይልና በአመጽ ለመጣል ራሱን ችሎ ከተቋቋመውና ራሱን የኢትዮዽያ የነጻነትና ዴሞክራሲ ሃይል ብሎ ከሚጠራው ወታደራዊ ቡድን ጋር ግነኙነት የፈጠረ ሲሆን፥ እነዚህ በተናጠል የተቋቋሙ ቡድኖች የገንዘብና የሎጀስቲክ ድጋፍ ለማግኘት የሚያስችላቸውን ስምምነትም ያደርጋሉ
በወቅቱ ለሽብር ተልኳቸው የሚፈልጉትን ድጋፍ ያደርጉልናል ብለው ያሰቧቸውን የአሸባሪው የግንቦት 7 አባላትም በሀገር  ውስጥ አፈላልገው ያገኟቸዋል።

ሊያነቡት የሚገባ: በፒያሳው ቦንብ ፍንዳታ ዋና አቀናባሪው ተስፋዬ ገ/አብ መሆኑን ያውቃሉ? (በአለማየሁ መሰለ )

አለማየሁ መሰለ
ለዛሬ የማቀርበው መረጃ ተስፋዬ ገብረአብ እንደ ሸፋን ከሚጠቀምበት የደራሲነት እና
የጋዜጠኘነት ስራ ባሻገር ለማመን በሚያዳግት ይሰራ የነበረውን የወንጀል ድርጊት ፍንትው አድርጎ ያሳያል።
ከዚህ በታች አባሪ ተደርጎ የተያያዘው በእጅ የተጻፈ መረጃ፣በእጄ ላይ ካሉ መረጃዎች መሃከል ትኩረቴን የሳበው ነው።እንደምትመለከቱት በራሱ በተስፋዬ ገብረአብ እጅ የተጻፈ ነው።ከሌሎች መረጃዎች ለየት የሚያደርገው ደግሞ፣እንደሌሎች መረጃዎች በፎቶኮፒ እጄ ላይ የቀረ ሳይሆን፣ዋናው (ኦርጅናል)መሆኑ ነው። ምክንያቱም በቀጥታ ወንጀል የተጻፈበት ሆኖ ስለታየኝ ነው።ከእጅ ጽሁፉ ላይ እንደምትመለከቱት፣መኩሪያ መካሻ ከተባለ ግለሰብ ጋር ድብቅ(ህቡእ) ስራ ለመስራት ጀምረው ነበር።እንደኔ ግምት የኤርትራ መንግስትን ጥቅም በቀጥታም ሆነ በተዘዋዋሪ ያስፈጽማል ብለው ያሰቡትን ተልእኮ ለመፈጸም አሲረው ነበር፡፡እንደ መረጃው ከሆነ መኩሪያ መካሻ የተባለው ግለሰብ ከፒያሳው ቦንብ ፍንዳታ በኋላ ፈርቶ ይሁን ሌላ ባይታወቅም፣ከተስፋዬ ጋር ያለውን ግንኙነት አቋርጧል።የፒያሳው የቦንብ ፋንዳታ ብሎ የተገለጸው ደግሞ ሌላ ሳይሆን በ2002 እኤአ በትግራይ ሆቴል ላይ የደረሰው ፍንዳታ ነው።

በተናጥል ሆኖ ፖለቲካውን ማራመድ ጎታች አይደለም – ይልቃል ጌትነት

Hiber Radio Interview with Eng Yilkal Getnet
ይልቃል ጌትነት
የሚሊዮኖች ድምጽ አገር ቤት በአንድነት ፓርቲ ኤዲቶሪያል ቦርድ የምትታተም  ነፃ ጋዜጣ ናት። በሁለተኛ እትሟ የሰማያዊ ሊቀመንበር አቶ ይልቃ ጌትነትን ይዛ ቀርባለች። ሊቀመንበሩ ከሕዝቡ የሚነሱ ፣  አብሮ ከአንድነት ፓርቲ ጋር አብሮ በመስራት ዙሪያ ያጠነጠኑ ጥያቄዎች የቀረበላቸው ሲሆን፣ የአንድነቱ መሪ አቶ በላይ  ፍቃደ በአዲስ ድምጽ ራዲዮ ከሰጡት አስተያየት የተለየ በአብሮ መስራቱ ዙሪያ ተስፋን የሚሰጥ ሳይሆን ተስፋን የሚይጨለም መልሶችን ነበር የመለሱ።
አቶ በላይ ፍቃዱ ፣ አንድነት፣ ሰማያዊ፣ መኢአድ እና ትብብር ተመሳሳይ የፖለቲካ ፕሮግራም ያላቸው እንደመሆኑ በተናጥል መሆናቸው ትርጉም የማይስጥ ነው የሚል ምላሽ በመስጠት ድርጅታቸው የሕዝብ ጥያቄ  በአክበር ዓብሮ ለመስራት መደረግ ያለበትን ሁልሉ እንደሚያደርግ ማሳወቃቸው ይታወቃል። የሰማያዊ መሪ አቶ ይልቃል ጌትነት ግን፣  በተናጥል ሆኖ ፖለቲካውን ማራመድ ጎታች አይደለም የሚል ምላሽ ሰጥተዋል።

ኢትዮጵያዊያን አንዳርጋቸውን ሲያዩ የሚታያቸው ጽናት፣ አርበኝነትና አልበገር ባይነት ነው። ሲል ግንቦት 7 ለፍትህ፣ ለዲሞክራሲና ለነፃነት ንቅናቄ ገለጸ።

g7-logoግንቦት 7 <<ሁላችንም አንዳርጋቸው ጽጌን እንሁን!!!>> በሚል ርእስ ዛሬ ታህሳስ 29 ቀን ባስነበበው ርእሰ-አንቀጽ፤በህወሓት ሙሉ ቁጥጥር ስር የሚገኘው የፌደራል ፖሊስ እሁድ እለት በቴሌቪዥን ፕሮግራሙ በግፍ እስር ላይ የሚገኘውን የግንቦት 7 ዋና ፀሐፊን አቶ አንዳርጋቸው ጽጌን ለ 10 ደቂቃ አቅርቦት እንደነበር በማውሳት፤ይህ የ10 ደቂቃዎች ምስል ለቁጥር በሚያታክት ሁኔታ ተቆራርጦ የተቀጣጠለ በመሆኑና አቶ አንዳርጋቸው በትክክል ምን እንዳለ የሚያስረዳ ባለመሆኑ፤ በይዘቱ ላይ አስተያዬት መስጠት አስፈላጊ እንዳልሆነ ገልጿል።

ባለቤት የሌለው መሬት – ቤጌምድር! (የመከላከያ ሰራዊት በትግራይ እና አማራ ተዋጊዎች መካከል ሰፈረ (ከዚያስ?))

begemedeir
(ዳዊት ከበደ ወየሳ)
ሉም ኢትዮጵያዊ ስለዚህ አካባቢ እኩል ግንዛቤ ላይኖረው ይችላል:: በመሆኑም ይህን አጋጣሚ በመጠቀም ስለዚህ አካባቢ ታሪካዊ ዳራ ማሳየት አስፈላጊ ሆኗል:: እናም በታሪክ መንኮራኩር ትንሽ ወደኋላ መሄድ ሊኖርብን ነው::
 ይህ የሰሜን አውራጃ ከጥንት ጀምሮ ቤጌምድር ተብሎ የሚታወቅ ሲሆን በራሱ መሪዎች ይተዳደር የነበረ ስፍራ ነው::

በጎንደር አርማጭሆ የተቀሰቀሰው ግጭት ሊበርድ አልቻለም

10923573_1560615314186107_7573440129440943485_nኢሳት ዜና :-ባለፈው ሳምንት ታጣቂዎች በከባድ መሳሪያዎች በመታጀብ በጎንደር አርማጭሆ ውስጥ <<ሶረቃ>> የሚባለውን አካባቢ ወደ ትግራይ ለማካለል በወሰዱት እርምጃ የተነሳው ግጭት እስካሁን ሊበርድ እንዳልቻለ በስፍራው የሚገኘው የኢሳት ወኪል ያጠናቀረው ሪፖርት ያመለክታል።

መታረም የሚገባዉ ማነዉ? ርዕዮት አለሙ ከቃሊቲ እስር ቤት

በግል የህትመት ዉጤቶች አማካኝነት በሀገሬ ዉስጥ የምመለከታቸዉን ችግሮች ለህዝብ ማቅረብና እንደዜጋም መፍትሔ ይሆናሉ ብዬ የማስባቸዉን ሀሳቦች መጠቆም ከጀመርኩ አምስት አመታት አለፉ፡፡ የመጀመሪያ ፅሑፌን ያዘጋጀሁት ” “ስህተቶችን” ለማረም የተፈፀሙ ስህተቶችና የስህተት ማረሚያ እርምጃዎች” በሚል ርዕስ እንደነበረ አስታዉሳለሁ፡፡ በዚህም ፅሑፍ የፕሬስ፣የፖለቲካፓርቲዎች ምዝገባና መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶችን የተመለከቱ አዋጆች የወጡበት ምክንያትና እንደሀገር የሚያሳድሩትን ተፅእኖ ለመዳሰስ ብሎም ኢህአዴግ ከስህተቶቹ እንዲታረም ለመምከር ሞክሬያለሁ፡፡

Ryotየኢህአዴግ ሰዎች በአንድ የገዢዉ ፓርቲ ልሳን በሆነ ድረገፅ አማካኝነት የማስጠንቀቂያ ይዘት ያለዉ ምላሽ መስጠት የጀመሩት ከላይ ከጠቀስኩት የመጀመሪያ ፅሁፌ ጀምሮ የነበረ ቢሆንም በአዲስፕሬስ ጋዜጣ ላይ በአዘጋጅነት ተቀጥሬ መስራት ስጀምር ግን ሁኔታዉ እየባሰ መጣ፡፡ በተለይ የኢትዮጵያ እንባ ጠባቂ ተቋም አዳማ ላይ ከተለያዩ ሚዲያዎች ለተዉጣጣን ጋዜጠኞች የሰጠዉን ስልጠና ከተካፈልኩ በኋል ከስልጠናዉ ጋር በተያያዘ ለህትመት ያበቃሁት ፅሁፍ ኢህአዴጎችን በእጅጉ አስቆጣቸዉ፡፡

Wednesday, January 7, 2015

በአንድነት ፓርቲ ላይ…

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ በተመለከተ ብዙ እየሰማን ነው፡፡ ፓርቲው ራሱን የማፅዳት ሃላፊነት ከተወጣ በኋላ ገዢው ፓርቲ ጥርሱን የነከሰበት ይመስላል፡፡ ብዙ ፈተና እየገጠመው ነው፡፡ በምርጫ ቦርድ ጥያቄ መሰረት ጠቅላላ ጉባኤ በድጋሚ እስከማድረግም ደርሰዋል፡፡በኔ እምነት አንድነት ፓርቲ በበኩሉ ብዙ ርቀት የሄደ ይመስለኛል፡፡ ትእግስታቸው አደንቃለሁ፡፡ ፓርቲው በውስጡ ከጥቂቶች በቀር በዙዎቹ ቁምነገር የሚያስቡ የምናከብራቸውና የምንወዳቸው ጥሩ ሰዎች አሉት፡፡

“ቦርዱ እንዳንሳተፍ ከከለከለን ተመጣጣታኝ እና አማራጭ ፖለቲካዊ ርምጃ ለመውሰድ እንገደዳለን”….አንድነት ፓርቲ!

udjታኀሳስ ፳፱(ሃያ ዘጠኖ) ቀን ፳፻፯ ዓ/ም ኢሳት ዜና :-የውጥረቱ  መካረር ምክንያት የምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ ዶክተር አዲሱ ገብረ እግዚአብሔር  ከቦርዱ ውሳኔ ቀድመው ወደ ድርጅት ሚዲያ በመሄድ ” አንድነትና መኢአድ የውስጥ ችግራቸውን ካልፈቱ በምርጫ ላይሳተፉ ይችላሉ” የሚል መግለጫ መስጠታቸው ነው።
ዶክተር አዲሱ፤ ሁለቱ ፓርቲዎች  በህገ- ደንባቸው መሰረት ውስጣዊ ችግራቸውን እንዲፈቱ  በቦርዱ ቢነገራቸውም ችግራቸውን አለመፍታታቸውን በመጥቀስ፤  አሁን ባሉበት ሁኔታ በምርጫ ሊሳተፉ እንደማይችሉ ነው ያሳወቁት።  “መስመሩን ያልጠበቀ ነው”ያለው የቦርዱ ምክትል ሰብሳቢ መግለጫ ያስቆጣው አንድነት ፓርቲ ትናንት ለኢሳት በሰጠው ምላሽ፤ ፓርቲው ምንም ያልፈታው ችግር እንደሌለ በመጥቀስ፤ ቦርዱ  በምርጫው እንዳልሳተፍ ካገደኝ፤ ተመጣጣኝ የሆነ ፖለቲካዊ ውሳኔ ለመወሰን እገደዳለሁ ማለቱ ይታወሳል።

አሁን አንድነት ግልፅ ጦርነት የታወጀበት ይመስላል – አቶ ኪዳኔ አመነ – የመድረክ ወጣት አመራር

አንድነት ለዴሞክራሲና ለፍትህ ፓርቲ በተመለከተ ብዙ እየሰማን ነው፡፡ ፓርቲው ራሱን የማፅዳት ሃላፊነት ከተወጣ በኋላ ገዢው ፓርቲ ጥርሱን የነከሰበት ይመስላል፡፡ ብዙ ፈተና እየገጠመው ነው፡፡ በምርጫ ቦርድ ጥያቄ መሰረት ጠቅላላ ጉባኤ በድጋሚ እስከማድረግም ደርሰዋል፡፡በኔ እምነት አንድነት ፓርቲ በበኩሉ ብዙ ርቀት የሄደ ይመስለኛል፡፡ ትእግስታቸው አደንቃለሁ፡፡ ፓርቲው በውስጡ ከጥቂቶች በቀር በዙዎቹ ቁምነገር የሚያስቡ የምናከብራቸውና የምንወዳቸው ጥሩ ሰዎች አሉት፡፡

ከሬዲዮና ከቴሌቪዥን በተጨማሪ ድረገፆችን ለመቆጣጠር አዲስ ህግ ተዘጋጀ

በኢንተርኔት የሚሰራጩ ፅሁፎችን, ምስሎችንና ቪዲዮዎችን ለመቆጣጠር ታስቧል 
የግል የሬዲዮ ጣቢያዎች ፈርሰው ከመንግስት ቻናል እንዲከራዩ ለማድረግ ታቅዷል

የሬዲዮና የቴሌቪዥን ስርጭቶችን ለመቆጣጠር ከስምንት ዓመት በፊት በታወጀው ህግ ላይ አዳዲስ ቁጥጥሮችን የሚጨምርና እንዲሁም የኢንተርኔት ስርጭቶችንና ድረገፆችን የሚያካትት ህግ ተዘጋጀ.
ከተለያዩ የሚዲያ ተቋማት ጋር ከትናንት በስቲያ ሃሙስ ውይይት የተካሄደበት ረቂቅ ህግ , ነባሩ አዋጅ ውስጥ የሰፈሩ የባለቤትነትና የፈቃድ አሰጣጥ ቁጥጥሮችን የሚዘረዝር ሲሆን; በኩባንያ መልክ እንጂ በግለሰብ የሬዲዮ ወይም የቴሌቪዥን ድርጅት ማቋቋም እንደማይቻል ይጠቅሳል. የዝምድና ወይም የጋብቻ ግንኙነት ያላቸው ሰዎች ለብቻቸው ባለአክሲዮን የሆኑበት ኩባንያ ፈቃድ እንደማይገኝም ተደንግጓል.

ያለፈው ሥርዓት “አስማተኛ” ሳይሆን አይቀርም!

እኔ የምላችሁ ግን … ኢህአዴግ ሥልጣን ከያዘ ስንት ዓመቱ ነው? ይሄንን ቀላል ጥያቄ የምጠይቃችሁ ወድጄ እንዳይመስላችሁ. ግራ ቢገባኝ ነው. ሌላም ጥያቄ አለኝ – ያለፈው ሥርዓት ከተገረሰሰ ምን ያህል ጊዜ ሆነው? (ውዥንብሩ መጥራት አለበት!) አንዳንዴ ያለፈው ሥርዓት “አስማተኛ” ይመስለኛል. ለምን መሰላችሁ? አንዳንድ ሰዎች አሁንም ከ 24 ዓመት በኋላ እንኳን ስለሱ ማውራት አልተዉም.ለሁሉ ነገር ያለፈውን ሥርዓት ካልጠሩ አይሆንላቸውም – በተለይ የኢህአዴግ ካድሬዎች.
ሰሞኑን EBC ባቀረበው የዜና ዘገባ ላይ “… የሴቶች ጥቃት ያለፈው ሥርዓት ችግር ስለሆነ እንታገለዋለን …” (egentlig ?!) የሚል ነገር የሰማሁ መሰለኝ. እውነቱን ልንገራችሁ አይደል … ራሱ ኢህአዴግም እንኳን የሴቶች ጥቃት “ያለፈው ሥርዓት” ችግር ነው አይልም.እንዲያ ካለማ — ያለፈው ሥርዓት አልተገረሰሰም ማለት ነው. ወይም ደግሞ እንዳልኩት “አስተማኛ” ነው. (መቃብር እየፈነቀለ የሚወጣ!)
ይሄውላችሁ — በሴቶች ላይ የሚፈፀሙ ጥቃቶች ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በዓይነትም በመጠንም እየጨመሩ ለመምጣታቸው ከፖሊስ ፕሮግራም የበለጠ ማስረጃ የለም. (የሴቶች መብት ተሟጋቾችም ምስክር ናቸው!) አስገድዶ መድፈር, አሲድ መድፋት, ከባድ ድብደባና የአካል ማጉደል እንዲሁም አሰቃቂ ግድያዎች … በእጅጉ በርክተዋል. (ሰብዓዊ ልማት ተዘንግቷል!)

የምርጫ ቦርድ ምክትል ሃላፊ አንድነትን እና መኢአድ በምርጫው መሳተፍ እንደማይችሉ ገለጹ

የምርጫ ቦርድ ምክትል ሰብሳቢ፣ አንድነት እና መኢአድ በምርጫ እንዳይሳተፉ መታገዳቸውን ለፋና ራዲዮ ገለጹ። የአንድነት አመራሮች ወደ ምርጫ ቦርድ ሄደው የምርጫ ቦርድን ዉሳኔ በጠየቁ ጊዜ ቦርዱ ነገ ማክሰኞ እንደሚሰበሰብና ቦርዱ እንደሚወስን ቢነገራቸውም፣ ቦርዱ ሳይሰበሰብ ምክትል ሃላፊው፣ ቀደመው በራዲዮ፣ የመኢአድ እና የአንድነት ፓርቲ እንደይሳተፉ መግለጻቸው፣ ከወዲሁ በሕወሃት ማእከላዊ ኮሚቴ የተወሰነና ተግባራዊ የሚሆነው ይሄ ዉሳኔ ይሆናል በሚል እንደሆነ ተንታኞች ይናገራሉ።

Monday, January 5, 2015

ወያኔ የጉራጌ ማህበረሰብ ከሌላው የህብረተሠብ ክፍል ለማጋጨት በወልቂጤ ዩኒቨርሥቲ እየፈጸመው ያለው ደባ ሁሉም ኢትዮጵያዊ ሊገነዘበው ይገባል

By Seyoum Workneh ከላይ በርዕሱ ላይ የጉራጌ ማህበረስብ ከሌላው የህብረተሰብ ክፍል ብዬ የተጠቀምኩት ወያኔ/ኢህአዴግ በጉራጌ ዞን በቸሃ ወረዳ ጉብሬ ከተማ ላይ በህዝብ ድጋፍና እርብርቦሽ የተመሠረተችው ወልቂጤ ዩኒቨርሥቲ ውሥጥ በተግባር እያደረገ ያለውን ጉዳይ ነጠል አድርጌ ለማሣየት እንጂ ወያኔ በሁሉም የሐገራችን ክፍል የተሠማራበት እኩይ ተግባር ጠፍቶኝ እንዳልሆነ ልትረዱልኝ እፈልጋለሁ። ባጠቃላይ ወያኔ ኢትዮጵያ ሐገራችን ለማጥፍት ግቡ አድርጎ የሚንቀሳቀሥ የትኛውንም ህዝብ ሊወክል የማይችል በጥቂት ማፍያ ወንበዴዎች የሚመራ የሆዳሞች ድርጅት ነው። የመጨረሻ የሆነውን ሐገር የማፍረሥ አላማቸው እውን እሥኪሆን ድረሥ ሀገሪቷን መምራት ሥለ ሚፈልጉ ህዝቡ አንድ እንዳይሆን የተቻላቸውን ሁሉ ከማድረግ ወደ ኻላ እንደሚያደርጉ ልንገነዘብ ይገባል። ከፋፍለህ ግዛ (በዘር) መርህ የሚከተለው ወያኔ ላለፉት 23 ዓመታት ህዝቡን እርሥ ብርሥ እንዳይተማመን፤ እርሥ በርሥ እንዲተላለቅ፤ እርሥ በርሥ እንዲጥላላ አያሌ ሥራዎችን ሠርቷል።

ተስፋዬ ገብረአብ ‹የቅዳሜ ማስታወሻ› ወደሚባለው የጡመራ ገጹ ተመልሷል፡፡ወደ ቀልቡ ግን አሁንም አልተመለሰም

ተስፋዬ ገብረአብ ‹የቅዳሜ ማስታወሻ› ወደሚባለው የጡመራ ገጹ ተመልሷል፡፡ወደ ቀልቡ ግን አሁንም አልተመለሰም፡፡ዛሬም ያው ነው፡፡ የሆነ የማይድን በሽታ የያዘው ይመስለኛል፡፡‹ከዚህ ጊዜ በኃላ ስለምትሞት የጀመርከው ነገር ካለ በቶሎ ጨረስ ፡፡›› ተብሎ መርዶ የተነገረው አይነት፡፡ ተስፋዬ በቀሩት ቀናት ለኑዛዜ የሚያበቃ መልካም ነገር ሳይሆን በክፋት የሚያስመነድገው ሳዲስታዊ ግብር ለማድረግ የቆረጠ አይነት ሰው ስሜት በጽሁፎቹ ውስጥ ተዘርቶ ይታያል፡፡
ጽሁፎቹ ጥጋቸው ሰውኛ አይደለም፡፡ተስፋዬ ታሪክ ያገነነው እውነት አይዋጥለትም ተከታትሎ በጥላሸት ቦንብ ካላደባየው ደረቱ ላይ የሚያቃጥለው መሆኑን እያረጋገጠ ነው፡፡ ህዝብ ከህዝብ ባለው ግንኙነት ውስጥ ያለው የመቻቻል ብሂል ከመፈራራት እና ካለመንቃት መንፈስ ጋር ያሰናስነዋል፡፡እንደ ጀመሪ የፊልም ታዳሚ ‹መቼ ነው ድብድቡን የሚጀመረው?› ጥያቄው አልተቋረጠም፡፡ተስፋዬ ከዕድሜውና ከሚኖርበት ሃገር አንጻር የሚጠበቅበት የሃሳብ ግዝፈትና ሰብአዊነትን ገና አልተጠጋውም፡፡‹ዕድሜ ይስጥህ› የሚለው ምርቃት ርግማን መሆኑን ማሳያ እንደ ተስፋዬ ያለው ካልሆነ ማን ሊሆን ይችላል?

ፍትሕ አያረጅም! የኢትዮጵያና የአርሚኒያ ትግል -ኪዳኔ ዓለማየሁ

መግቢያ፤
ኢትዮጵያንና አርሚኒያን ከሚያመሳስሏቸው ጉዳዮች አንደኛው የአንድ ዓይነት የኦርቶዶክስ ሃይማኖት የእምነት መሠረት (ዶግማ) ተከታዮች ያሉባቸው ሐገሮች መሆናቸው ነው። በዚህ ጽሑፍ የማተኩርበት ተመሳሳይነት ግን ሁለቱም ሐገሮች በከባድ የጦር ወንጀሎች ተጠቅተው እያንዳንዳቸው ቢያንስ አንድ ሚሊዮን ሕዝብ የተጨፈጨፈባቸው መሆኑ ነው። ሌላም እጅግ አስጸያፊ ግፍ የተፈጸመባቸው ሐገሮች ናቸው። በተጨማሪም፤ ሁለቱን ሐገሮች ያቀራረባቸው ሌላው ጉዳይ በኦቶማን ዘመነ መንግሥት፤ ከቱርኮች ግፍ በመሸሽ በቀዳማዊ ኃይለ ሥላሴ መንግሥት መልካም ፈቃድ ወደ ኢትዮጵያ የተሰደዱት 40 አርመኖች ኑሯቸውን በሐገራችን መቀጠላቸው ነው። እነዚህ አርመኖችና ተወላጆቻቸው በኢትዮጵያ ተመቻችተው የኖሩና ብዙዎቹም አማርኛውን ያቀላጥፉ እንደ ነበር የታወቀ ነው። በዚህ አጋጣሚ፤ በተባበሩት መንግሥታት ድርጅት አማካኝነት ዱባይ በምሠራበት ጊዜ እዚያ ይኖር የነበረውን፤ ወዳጄን፤አቶ የርቫንትን እያስታወስኩ፤ አርመኖች ያቋቋሟትን ሻርጃ (Sharjah) የምትገኝ ቅድስት ማርያም ቤተ ክርስቲያን ለኢትዮጵያውያን ምእመናን በማጋራታቸው፤ ውለታቸውን አልረሳውም።

ዞን ዘጠኝ ጦማርያን እና ጋዜጠኞች ለአስራ አምስተኛ ጊዜ ተቀጠሩ

zone 9
በዛሬው እለት በካንጋሮ ፍርድ ቤት የቀረቡት የዛኦን ዘጠኝ ጦማርያን እና ጋዜጠኞች ከዚህ ሁሉ ኢ-ፍትሃዊ እስር በኋላም ቢሆን ከፊታቸው ላይ ሳቅና ፈገግታን ሊነጠቁ ያልቻሉ መሆኑ በግልጽ ለአምባገነኖች እና አሽከሮቻቸው አሳይተዋል:: በሙሉ ራስ መተማመን ስሜት እና በታላው ብሩህ መንፈሳቸውን ተላብሰው ካንጋሮ ፍርድ ቤት ይደረሱት ወንድሞቻችን እና እህቶቻችን የአሸናፊነት ስሜት በፊታቸው ይነበባል::ፖሊስ ጉዳዩን የሚከታተሉ እና በፍርድ ቤቱ የተገኙትን ስልካቸውን እንዲያጠፉ ያደረገ ሲሆን በችሎት ክተሰየሙት ዳኛ አንዱ መቀየራቸውም ታውቋል:;እንዲሁም ፖሊስ ያሰራቸውን ጦማርያን እና ጉዳዩን ሊክታተሉ የመጡትን በአይን እንኳን እንዳይነጋገሩ ሲያዋክብ ታይቷል::

የግንቦት 7 ሕዝብ ግንኙነት አቶ ኤፍሬም ማዴቦ ስለ አዲሱ የአንዳርጋቸው ቪዲዮ ተናገሩ (ያድምጡ)

የግንቦት 7 ለፍትህና ለዲሞክራሲ ንቅናቄ የ ዝብ ግንኙነት ሀላፊ አቶ ኤፍሬም ማዴቦ የህወሓት አገዛዝ በአቶ አንዳርጋቸው ላይ ያሰራጨውን ፊልም ጉዳይ በተመለከተ ከህብር ሬዲዮ ጋር ቃለ ምልልስ አድርገዋል:: ያዳምጡት::

“ለ6 ወር ያስተማርኩበት ደሞዝ አልተከፈለኝም” ዶ/ር መረራ ጉዲና

መብቴን ለማስከበር ወደ ፍ/ቤት ላመራ እችላለሁ ብለዋል
የፕሮፌሰርነት ማዕረግ አላግባብ መከልከላቸውን ተናግረዋል
(በአለማየሁ አንበሴ)
ባለፈው ሳምንት በማህበራዊ ድረ-ገጽ በተሰራጨ መረጃ፣የፖለቲካል ሣይንስ መምህርና የተቃዋሚ ፓርቲ አመራር የሆኑት ዶ/ር መረራ ጉዲና፤ ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ በጡረታ እንደተባረሩ ቢነገርም መረጃው እውነት አለመሆኑን ከአንደበታቸው ለማረጋገጥ ተችሏል፡፡ ሆኖም ከዩኒቨርሲቲው ጋር የተፈጠረ ችግር እንዳለ ይናገራሉ – ዶ/ር መረራ፡፡ ችግሩ ምን ይሆን? ጋዜጠኛ አለማየሁ አንበሴ፤ይሄንንና ሌሎች ከመምህርነት ሙያቸው ጋር የተያያዙ ጉዳዮችን ጠይቋቸው ምላሽ ሰጥተዋል፡፡

ኮፍያ ደርበው ፥ ኩሽክ ተከናንበው!! – እንግዳ ታደሰ

አፈር ይቅለላቸውና ! በአንድ ወቅት ልደተ ትውልዳቸው ኤርትራዊ ሆኖ ፣ በነፍጠኝነት ዘመቻ ወላጆቻቸው ሃረር ላይ የወለዷቸው ዶክተር አሰፋ መድህኔ ለሥራ ጉዳይ ኖርዌይ በሚመላለሱበት ወቅት ያወጉን ጨዋታ ፣ ለምን እንደሆነ አላውቅም ዘወትር እየተመላለሰ ያስቀኛል ፡፡ ጨዋታው እንዲህ ነው ፡፡ ዶክተር አሰፋ ወደ ኦስሎ በተደጋጋሚ ብቅ ሲሉ
የድሮ ጓደኛቸውን አቶ ዩሱፍ ያሲንን ወይም በብዕር ስሙ ሃሰን ኡመር አብደላን መጥቻለሁ ብለው ይደውሉለት ነበር ፡፡
ዶክተር አሰፋ ሲመጡ ጨዋታቸው እጅግ መሳጭ ስለሆነ ፣አቶ ዩሱፍ ብቻ ሳይሆን ፣ አቶ ግደይ ዘርአጽዮንን ጨምሮ ፣ ኦስሎ ውስጥ በምትገኘው የኢትዮጵያ ማዕከል ውስጥ ሁልጊዜ የምናገኛቸው ሰዎችም ነበርን ፡፡

Friday, January 2, 2015

ግንቦት 7 – ቀኑ ሲቃረብ መውጫው ይጠባል!

Ginbot 7 weekly editorialኢትዮጵያ ሀገራችን በታሪኳ ከአስከፊ የፈተና አረንቋ ውስጥ ተገፍታ የገባችበት ዘመን ቢኖር ይህ የምንገኝበት ዘመነ ወያኔ ብቻ ነው፡፡ ዜጎችዋ ከፋሽስት ኢጣልያ በከፋ ሁኔታ ይህ ቀረሽ የማይባል የመከራ መአት የወረደባቸውና እየወረ ደባ ቸው የሚገኝበት ዘመን ቢኖር ይህ የምንገኝበት ዘመን ወያኔ ብቻ ነው፡፡ እስር ቤቶች ሞልተው ተጨማሪ እስር ቤቶች መገ ንባት ከልማት ተቆጥሮ የሚፎከርበት ዘመን ቢኖር ይኸው ዘመነ ወያኔ ብቻ ነው፡፡ የሀገሪቱ ብሄራዊ ባንክ ንብረት የሆ ነው ወርቅ በባሌስትራ ለውጦ እስከ መዝረፍ የደረሰ በጠራራ ፀሀይ የህ ዝብና የሀገር ሀብት ታይቶና ተሰምቶ በማይታወቅ ሁኔታ በጥቂቶች የሚዘረፍበት ዘመን ቢኖር የምንገኝበት ዘመነ ወያኔ ብቻ ነው፡፡ የጅምላ እስር፤ የጅምላ ግድያ፤ የጅምላ ስደትና መፈናቀል፤ ይበልጡንም በታሪካችን ታይቶ በማያውቅ መልኩ ለሞት፤ ለእስር፤ ለመፈናቀልና ለስደ ት ምክንያቱ የተገኘንበት ዘውግ የሆነበት ዘረኛ ዘመን ቢኖር ይኸው ዘመነ ወያኔ ብቻ ነው፡፡

አቶ በረከት እሱን መች ጠየቅንህ?

ከፍተኛ ይቅርታ ይህ ጦማር ከ1ኛ እስከ 3ኛ ያለው ተቆርጦ በመቅረቱ ታርሞ ቀርቧል።
ህዝባዊ ወያኔ ሃርነት ትግራይ(ህወሃት)የተመሠረተበትን አርባኛ ዓመት ለማክበር ሽር ጉድ እየተባለ ባለበትና በመጠኑ ከፍተኛ የሆነ የሀገሪቱ የገንዘብ ወጭ ተደርጎ አስረሽ ምችው የሚደለቅበት ሰአት ላይ ያለን ሲሆን የዘድሮው በዓል አከባበር ደግሞ የተለየ ሆኗል አስቀድመው ነው የጀመሩት ያም ሆነ ይህ በዓሉ ለምን ይከበራል? የሚያከብረውስ ማን ነው? ብለን ስንጠይቅ ድርጅቱ በጫካ አሥራ ሰባት ዓመት በትረ ሥልጣኑን ከጨበጠ በኋላ በከተሞች ለሃያ ሦሥት ዓመታት ያህል የምሥረታ በዓሉን በከፍተ የገንዘብ ወጭ እያከበረ ዘልቋል።