Monday, August 26, 2013

ግብረ ሰዶም (Homosexual) በኢትዮጽያ

ግብረ ሰዶም የሚለው መጠሪያ የተገኘው ከመፅሐፍ ቅዱስ ነው:: የሰዶም ስራ እንደ ማለት ነው:: ሰዶም እና ገሞራ በመፅሐፍ ቅዱስ ታሪክ ውስጥ ያሉ መንደሮች ናቸው:: በዚያም ጊዜ በነዚህ መንደር ወንድ ከወንድ: ሴት ከሴት ይዳራ ነበር: አንድ ሴት ከብዙ ወንዶች ጋርም ወሲብ ትፈፅም ነበር:: እግዜርም በዚህ ተበሳጭቶ ከተማዋን በእሳት አጠፋት:: ከዛ ጊዜ ጀምሮ ወንድ ከወንድ ጋር ሴት ከሴት ጋር ሚዳሩት ግብረ ሰዶማዊያን:: ነገሩን ደሞ ግብረ ሰዶም መባል ጀመረ:

ግበረ ሰዶማውያን በኢትዮጽያ በጣም የተወገዙ ናቸው:: እራሳቸውን ደብቀው የሚኖሩ(አሁን አሁን ግን በስብሰባ አደዳራሽ በግልፅ መሰብሰብ ጀምረዋል) እንደሌላው አለም ‘I AM A GAY’ ብሎ ባደባባይ ‘ሚደነፋ እኛ ሃገር ላይ የለም (የወደፊቱን ባናቅም) እንደውም ግብርሰዶማዊነቱ ከታወቀ ወይ ከተጠረጠረ ያሰው ይገለላ:: እንደሰው ሳይሆን ‘ሚቆጠረው እንድ አውሬ ነው::

ሰሞኑን አንድ ታስሮ የተፈታ አብሮ አደጌ ስለ እስር ቤት ቆይታው ሲያጫውተኝ ስለ ግብረ ሰዶማዊያን አነሳሁበት:: ግብረሰዶማዊያን በእስር ቤት ውስጥ ያላቸውን የህይወት መስተጋብር ባጭሩ እንዲህ አብራራልኝ “አንድ ሰው ቡሽቲነቱ ከታወቀ ማንም ወደሱ አይጠጋም:: ከማንም ጋር አይቀላቀል:: የሚተኛውም ለብቻው ሽንት ቤት አጠገብ ነው:: ከሱው ጋር የታየ ሰው በቃ አለቀለት ያሰው ጌ ነው ተብሎ በሰፊው ይወራበታል ወደ እሱ የተጠጋ ሰው የልጁ አይነት እጣፈንታ ስለሚገጥመው ወደሱ ማንም ዝር አይልም::” 



የግብረሶደማዊያን ጭካኔ

አሁን አሁን እነዚህ ግብረሰዶማዊያን መገናኛ አላቸው:: ማህበርም አላቸው:: በውልም ተለይቶ ይታወቃል:: ግብረ ሰዶማዊ ያልሆነን ሰውም ወደ እነሱ አባልነት አስገድዶ በመድፈር: በመደለል ይቀላቅላሉ:: ከዚህ በፊት በአዲስ ጉዳይ መፅሔት ላይ ዳንኤል ክብረት የአንድ ህፃን ልጅን ታሪክ በመንገር ህፃናት እንዴት በነዚህ ሰዎች እንደሚታለሉ :እንዴት ጠመቃው እንደሚከናወንባቸው አስነብቦናል- I AM A GAY የሚል ቲሸርት ሁላ እስከ ማስለበስ:: እዚሁ መፅሔት ላይም በተደጋጋሚ የነዚህን ሰዎች ጭካኔ አንብበናል::

ከወራቶች በፊት እኔ በምኖርበት አካባቢ አንድ ግብረሰዶማዊ ወንድሙን ሽንት ቤት(የራሳቸው ቤት ውስጥ ያለ) ሲደፍር እናት ደርሳ ለፖሊስ አስይዛዋለች:: ግን ልጇን ከመደፈር ግን አላደነችውም:: ግን ይህ ግብረሰዶማዊ እንዴት ወንድሙ ላይ ሊጨክን ቻለ? በነሱ አተያይ ይህ ጭካኔ አይደለምን? ወንድሙን ስለሚወደው እሱ ትክክል ነው ብሎ ስላመነበት ሚወደውን ወንድሙን ውደነሱ አባልነቱ መጨመሩ ነውን?(አንድ ቤተሰብ ውስጥ አንድ ልጅ ሃይማኖቱን ሲቀይር በቆይታ ብዛት ወንድሞቹን እህቶቹን አንዳንዴም ወላጆቹን እንደሚቀይረው ነውን?) አንድ ሃይማኖተኛ እምነቱን እንደ ሚሰብክ እና ወደ እራሱ ሃይማኖት እንደሚስበው አይነት ነውን? ወይንስ ልጁ መጀመሪያውኑ እሱም ተደፍሮ ኖሮ ሲቆይ እሱም ተወስውስ አምሮት ነውን?

አብዛኞቻችን እንደሰማነው እዚው በመዲናችን ህፃናት ተማሪዎች በአስተማሪዎቻቸው ተደፍረዋል:: ጎዳና ተዳዳሪዎች በእንርዳችሁ ሰበብ ተደፍረዋል:: ወደ አሜሪካ እና አውሮፓ ለመሄድ ብዙች ሳይፈልጉ ግብረሰዶማዊ ሆነዋል:: ጥብቅ ሃይማኖተኛ ሆነው ‘ከጋብቻ በፊት ወሲብ ክልክል ነው’ ሚለውን ትዛ ላለመተላለፍ ሴትን ለማናገር ፍርሃት ውስጥ ተጀቡነው ስንቶች እድሜያቸው አልፎባቸው ህፃናት ወንዶችን ደፍረዋል::

እሺ መፍትሄውስ ምንድን ነው?

ብዙ ጊዜ ስለዚህ ቅጠአምባሩ ለጠፋ ጉዳይ ስለ መፍትሄው ከቡዙዎች ጋር ሳወራ እንደመፍትሄ ‘ሚያቀርቡት መንግስት ማያዳግም እርምጃ እንዲወስድ ነው (ቂጣቸውን በሳንጃ እንደማለት) ግብረሰዶማዊነት ባህላችንን ስለሚያጠፋ መንግስ ጠንከር ያለ እርምጃ እንዲወስድ ያሳስባሉ:: እኔ ግን ፈፅሞ በዚህ አልስማማም:: በኋይል ‘ሚጠፉ ቢሆን ኖሮማ ያኔ ከብዙ ሺህ አመታት በፊት እግዜሩ በእስት ባጠፋቸው ነበር::

የጠፉትን ለመመለስ ከሚደረገው ጥረት በላይ ሊጠፉ የተዘጋጁትን ህፃናት ልንታደጋቸው ይገባል:: አሁን መደባበቁ አያስፈልግም:: የኤድስ ስርጭትን እንዴት በመነጋገር እንደቀነስነው ታሪክ ማገላበጥ አይጠበቅብንም::በእድሜያችን ያየነው ነው:: በየትምህርት ቤቱ ለህፃናት ስለግብረሰዶማዊነት ጉዳት ማስተማር(በካሪኩለም ደረጃ:: ባይሎጂካል ጉዳቱን በስፖርት እና ባይሎጂ ትምህርት ውስጥ የባህል ጉዳቱን በሲቪክ ትምህርት ውስጥ በማካተት) በየመንደሩ ታች ድረስ በመውረድ ማስተማር:: ሊጠፉ የተዘጋጁትን ማዳን እንችላለን:: እኔ ጀምሬዋለው ለታናሽ ወንድሜ ስለ ግብረሰዶም ጉዳት አስተምረዋለው:: መጠንቀቅ ስላለበት ነገርም እነግረዋለው::

ግብረሰ ደማውያኑን ደግሞ ካገለልናቸው:: ቂጣቸውን በሳንጃ ከወጋናቸው:: በኛ ላይ የበቀል ስሜት ነው ‘ሚያድርባቸው:: እንደማንኛውም ሰው ብናያቸው: ብናቀርባቸው በኛ ላይ ‘ሚያደርሱትን የመድፈር ድርጊታቸውን ይቀንሱታል: ግብረሰዶማዊነት ህጋዊ በሆነባቸው ሀገራት ያለው የመደፈር ቁጥር እና ህጋዊ ባልሆነባቸው ሀገራት ያለው ቁጥር በጣም ልዩነት አለው:: እኔ የተሰማኝን ተናግሬለሁ ::

ማግለል:: ቂጣቸውን በሳንጃ መውጋት:: በአጠቃላይ የኋይል እርምጃ ይህን ችግር ሊቀርፈው አይችልም:: እንኳን እኛ እግዜሩም በኋይል ሊያቆመው አልቻለምና::

No comments:

Post a Comment