Friday, August 23, 2013

በአንድ አገር ሁለት ዓይነት ህግ

የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የስብሰባ ማሰወቂያ ክፍል በጠየቀው ማብራሪያ መሰረት የሰማያዊ ፓርቲ የሠልፍ አስተባባሪ ኮሚቴ ተገቢውን ምላሽ የሰጠ ሲሆን ፤አቶ ማርቆስ ብዙነህ የሰላማዊ ሠልፍና ስብሰባ ማሳወቂያ ኦፍሲር በጽሁፍ ምላሽ መስጠት የሚጠበቅባቸው ቢሆንም በቃል የተቃውሞ ሠልፉ የሚካሄድበት ቦታ በግንባታ ምክንያት እንደማይቻል የገለጹ ቢሆንም ፓርቲው እንዲህ ዓይነቱ ህገ-ወጥ አሰራር እንደማይቀብል እና ከሦስት ቀናት በፊት መንግስት( ኢህአዴግ) በተጠቀሰው ቦታ ፕሮግራሙን እንዳካሄደ እና ይህም መበት ለሁሉም የሚሰራ መሆኑ እና የተቃውሞ ሠልፉ በታቀደው ሰዓትና ቦታ እንደሚካሄድ ለአስተዳደር የስብሰባ ማሰወቂያ ክፍል ገልጻል፡፡
ይህ በእንዲ እንዳል መንግስት (ኢህአዴግ) በመስቀል አደባባይ ያካሄደው ፕሮግራም የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር የስብሰባ ማሰወቂያ ክፍል እውቅና እንዳልሰጠው እና ፕሮግራሙን ያካሄዱት አካላት ለመስተዳደሩ በጹኁፍ ያላሳወቁ መሆኑ ከአቶ ማርቆስ ብዙነህ የሰላማዊ ሠልፍና ስብሰባ ማሳወቂያ ኦፍሲር በገለጹት መሠረት ለመረዳ ተችሎሃል፡፡

No comments:

Post a Comment