Monday, September 14, 2015

የተደበቀው የህወሓት ማንነት ከደደቢት እስከ ቤተመንግስት – ክፍል 2 “ሳሞራ የኑስ በበረሃ በርካታ የህወሓት ታጋይ ሴቶችን ድፍሯል”


የተደበቀው የህወሓት ማንነት ከደደቢት እስከ ቤተመንግስት –  “ሳሞራ የኑስ በበረሃ በርካታ የህወሓት ታጋይ ሴቶችን ድፍሯል” (ክፍል 2)

መለስ ዜናዊ፣ ስብሀት ነጋ፣ ስዬ አብርሃ፣ ስዩም መስፍን፣ አባይ ፀሀዬ፣ ገብሩ አስራት፣ አለምሰገድ ገ/አምላክ፣ አውዓሎም ወልዱ፣ አረጋሽ አዳነ፣ አርከበ ዕቁባይ፣ ፃድቃን ገ/ተንሳይ፣ አበበ ተ/ኃይማኖት እና ክንፈ ገ/መደህን ለረጅም ጊዜ መቀሌ ላይ በመዶለት በኢትዮጵያና ህዝቦቿ ላይ አሲረው የበቀል፣ የዘረፋ፣ የመከፋፈል እና የረጅም ጊዜ የአፈና ስርዐት እቅድ ነድፈው ሰራዊታቸውን በባሌ ልከው እነሱ በቦሌ አዲስ አበባ ገቡ፡፡
TPLF 2
በአንድ ጃቸው መቀሌ ውስጥ ተጠፍጥፎ ተሰርቶ የተሳለ የበቀል ሰይፍ በሌላኛው እጃቸው የዘረኝነት ረጅም ዘንግ ጨብጠው አዲስ አበባ የገቡት የባንዳ ልጆች ስብስብ ሳይውሉ ሳያድሩ የጥፋት ተልዕኳአቸውን ዕቅድ አንድባንድ መተግበር ጀመሩ፡፡
የጥፋት ቡድኑ መሪ መለስ ዜናዊ “ከእናንተ ወርቅ ከሆናችሁት የትግራይ ህዝብ በመፈጠሬ እኳራለሁ፤ እንኳን ከእናንተ ተገኘን፤ እንኳን ይሄ ህዝብ የሌላ አልሆነ፤ እንኳን በሩቅ እያየን የምንቀናባችሁ አልሆናችሁ…” በማለት በአደባባይ ተናግሮ እሱም እንዳያቶቹ ኢትዮጵያዊነቱን ሽምጥጥ አድርጎ ካደ፡፡
ሌላውን የኢትዮጵያ ህዝብ አቋንሸሸ፡፡ ታላቋ ኢትዮጵያ ከትግራይ እግር ስር ተንበርክካ ለዘላለም እንደምትኖርም አወጀ፡፡ ከክህደት የተገኘ የጣልያን ሶልዲ እየበላ ያደገው መለስ ዜናዊ ዕልፍ ዓዕላፍ አባቶቻችንና እናቶቻችን ደማቸውን ያፈሰሱበትን አጥንታቸውን የከሰከሱበትን ሰንደቅ ዓላማ ጨርቅ ነው ብሎ በማራከስ በኢትዮጵያ ምድር ላይ የኢጣሊያንና የፈረንሳይን ባንዲራ ተክለው እደአውለበለቡት አያቶቹ እሱም የወጣለት ባንዳ መሆኑን በሚገባ አስመሰከረ፡፡ “የአክሱም ሐውልት ለወላይታው ምኑነው” ሲልም “የ3 ሺህ ዓመታት ታሪክና ባህላችን መመኪያቸውና መፈክሪያቸው ሁኖ ይገኛል…” በማለት ገና በበርሃ እያሉ የፃፉትን እምነታቸውን በአንደበቱ አረጋገጠልን፡፡ በትጥቅ ትግሉ ወቅት ገና የጥይት ድምፅ ሲሰማ ከጦር ሜዳ በመሸሽ 40 ኪሎ ሜትር የፈረጠጠው መለስ ዜናዊ፤ የድሀውን ገበሬ ልጆች አስጨርሶ ከሱ የሚሻሉትን ሰዎች እያሳሰረ፣ እያስገደለና እያሳደደ ስልጣን ለመያዝ የበቃው መለስ ዜናዊ፣ ድመቶችን በዙሪያው ሰብስቦ ለኢትዮጵያ ህዝብ ነብር መስሎ ለመታየት የሞከረው አነሩ መለስ ዜናዊ ልክ እንደ አያቱ ኢትዮጵያን በገንዘብና በስልጣን ለውጧታል፡፡
ህወሓቶች “አማራው የትግራይን ነፃነት ገፎ ግልፅና ስውር በሆኑ ዘዴዎች /ሸዋዊ ዘይቤዎች/ የትግራይ ህዝብ በድንቁርና፣ በበሽታ፣ በርሀብ አዘቅት ውስጥ እንዲሰምጥ ያደረጉት በተለይም ትግሬነቱን በፍጥነት እንዲክድና ያለውድ በግድ አማራ ለማድረግ ያልሞከሩት ዘዴ ባይኖርም መሬቱ ተቋራርሶ ስለተወሰደበትና የተደራረበ ጭቆና ስለደረሰበት አገሩን ጥሎ ተሰደደ፡፡ ባጠቃላይ በሁኑ ጊዜ ትግራይ በአማራው ነፃነቷን የተገፈፈች መሬቷ ተቋራርሶ የተወሰደባትና የተወሳሰበ ችግር የደቆሰው ህዝብ ሚኖርባት ጭቁን ብሄር ናት፡፡” በማለት ገና በበረሃ እያሉ የፃፉትን የጥላቻ ታሪክ በመስበክ የትግራይን ህዝብ ከሌላው የኢትዮጵያ ህዝብ ለመነጠል ብዙ ለፍተው ደክመዋል፡፡
“ትግራይ ጭቁን ብሄር በመሆንዋ በመንግስት የተደገፈ ወይም በግል የተያዘ ፋብሪካ ሊኖራት አልቻለም ፋብሪካዎች የጨቋኝዋ ብሄር አማራ ዋና ከተማ በሆነችው አዲስ አበባ ውስጥ ተከማችተው ይገኛሉ፡፡” ብለው ገና በበረሃ እያሉ ያምኑ የነበሩ ህወሓቶች ለአርባ አመታት ያለገደብ በዘረፉት የኢትዮጵያ ህዝብ ገንዘብ በትግራይ ህዝብ ስም ግዙፍ የንግድ ድርጅት በማቋቋም እና ፋብሪካዎችን በመክፈት ሌላው ኢትዮጵያዊ በትግራይ ህዝብ ላይ ጣቱን እንዲቀስር አድርገውታል፡፡ ይህም የትግራይ ህዝብ ከጎናቸው እንዲሰለፍ ከሸረቧቸው ታላላቅ ሴራዋች አንዱ ነው፡፡
ህወሓት በአንጠረኞቹ የፖሊት ቢሮ አባላቱ አማካኝነት ቀጥቅጦ የሰራውን የበቀል ሰይፍ ለመጀመሪያ ጊዜ ያሳረፈው ከአገራችን ክንድ ላይ ነው፡፡ ለዘመናት ተደክሞና ተለፍቶ በርካታ ሀብት ፈሶበት የተገነባውን የኢትዮጵያ መከላከያ ሰራዊት አፈራርሶ በእሱ የበርሀ ድኩማኖች ሙሉ በሙሉ ተክቶታል፡፡
ህወሓት ከደደቢት በርሀ የቆረጠውን ረጅም የዘረኝነት ዘንግ ወደቀፎው ሰድዶ በመሸንቆር ኢትዮጵያን ንቦቿን በትኖ ህብረት እንዳይኖራቸው ለማድረግ ሞክሯል፡፡ በተለይም ደግሞ አፈራርሶ እንደገና ለመገንባት የሞከረው የመከላከያ ሰራዊት ክፉኛ የዘር ሰለባ ሆኖ ይገኛል፡፡
ህወሓት በሀገር መከላከያ ስም ያቋቋመው ሰራዊት አየር ኃይልም ሆነ ምድር ኀይል ከቁጥር ግዝፈት በዘለለ አገራችን ሊቃጣባት የሚችል የውጭ ጥቃት ቢኖር በአስተማማኝ ሁኔታ መክቶ ዳር ድንበሯን ማስከበር የሚሆንለት አይደለም፡፡ ሰራዊቱ ሁሉም ማለት በሚቻል ሁኔታ ለእለት ጉርሱ ሲልና ከጓድ መሪ እስከ ኤታማጆር ሹሙ በህወሓት ታጋዮች በግድ ተጠርንፎ ተይዞ መሽሎኪያ ቀዳዳ እያማተረ የሚገኝ ነው ፡፡
ህወሓት ከአገራችን ይገኙ ከነበሩት ወታደራዊ አካዳሚዎች አልፈው የምዕራባዊያንን የጦር ሳይንሥ ኮሌጆች ያዳረሱትንና የወርቁን ዋንጫ ያነሱትን ምርጥ ምርጥ መኮንኖች እያፈሰ በየወህኒው ካጎረ በኃላ በትኖ በማሰደድና ለማኝ በማድረግ በዘር ስሌት ብቻ የጀነራልነት ዳረጎት በቸራቸው የራሱ የበረሀ ድኩማኖች ብቻ ሞልቶታል፡፡ እነዚህ የጀነራልነት ማዕረግን በዕውቀት ሳይሆን በታማኝነት ያገኙ የጦር መሀይም የህወሓት ታጋዮች በሀገር መከላከያ ሰም በስራቸው የሚገኘውን የደሃ ልጅ አስገድደው በፀረ ህዝብነት በማሰለፍ ጦርነት ውስጥ እየማገዱ የስርአቱን እድሜ ለማራዘም ይተጋሉ፡፡በተጨማሪም የአገሪቱን ሀብት በመመዝበር ተግባር ላይም በሰፊው ተሰማርተው ይገኛሉ ፡፡
የኢትዮጵያ ህዝብ ዋነኛ ጠላቶች ከሆኑት የህወሓት ጀነራሎች የተደበቀ ማንነት ከደደቢት እስከ ቤተ- መንግስት የአንዳንዶቹን እነሆ፡፡
1. ጀኔራል ሳሞራ የኑስ
ጀነራል ሳሞራ የኑስ ከሱዳናዊ አባቱ እና ኤርትራዊ እናቱ ኤርትራ ሳህል ከርከበት ተወልዶ ያደግና በአፍላ የጉርምስና ጊዜው በ1950 ዓ.ም ከወላጆቹ ጋር ወደ አክሱም በስደት የመጣ ነው፡፡
ለሰፌድ ስራ የሚያገለግል ዘንባባና አከት በመሽጥ በሚያገኙት እጀግ በጣም አንስተኛ የሆነች የቀን ገቢ ከለማኝ ኖሮ ባልተለየ ሁኔታ ህይወታቸውን ይገፉ የነበሩት የሳሞራ ወላጆች ሳሞራ ትምህርቱን ተምሮ ጨርሶ ለስራ በቅቶ እንደሚያሳልፍላችው በትንሹም ቢሆን ተስፋ ነበራቸው፡፡ ነገር ግን ሳሞራ በትምህርቱ እጅግ በጣም ሰነፍ በመሆኑ 11ኛ ክፍል ላይ በተከታታይ ሶስት ጊዜ በመውደቁ ከአክሱም አብረሃ ወአፅብሃ ትምህርት ቤት በ1968 ዓም ተባረረ፡፡
በዚያ ዘመን አክሱም በአብርሃ ወአፅብሃ ትምህርት ቤት ውስጥ ስመጥር ደደብና በወሮበላነቱ ስመገናና የነበረው ያኔው ብላቴና ሳሞራ የኑስ በድንቁርናው ምክኒያት እስከ መጨርሻው ከትምህርቱ ከተሰናበተ በኋላ የወላጆቹም የእሱም ተስፋ መክኖ ዘንባባና አከት ከመሸጥ በስተቀር ምንም አይነት የሕይወት አማራጭ በማጣቱ በነሀሴ ወር 1968 ዓ.ም ወደ ደደቢት በረሃ በመውረድ ህወሓትን ተቀላቀለ፡፡
በደካማ ጎኑ ዝና ለማፈስ የታደለው ሳሞራ የኑስ ህወሓትን በተቀላቀለ በአጭር ጊዜ ውስጥ በፈሪነቱ ሀገር ያወቀው ፀሀይ የሞቀው ሆነ፡፡ እንደ መለስ ዜናዊ እሱም በተደጋጋሚ ከጦር ሜዳ ሸሽቷል፡፡ የጥይት ድምፅ ሲሰማ የያዝውን መስሪያ አፍሙዝ አዙሮ የአፅፋ መልስ ከመስጠት ይልቅ ጠብመንጃውን ወርውሮ መሸሽጊያ ጥግ ፍለጋ እንደሚጣደፍና በፍርሃት እንደሚርበተበት በቅርብ የሚያውቁት የትግል ጓዶቹ ይናገራሉ፡፡
በድድብናው ከትምህርት ቤት የተባረረው ሳሞራ የኑስ በህወሓት ውስጥ በፍሪነቱ በጦር ሚዳ ባሳየው ነውረኛ ባህሪ ምንም አይነት እርምጃ አልተወሰደበትም፡፡ ይልቁንም የእሱ ቢጤ ፈሪ ለሆነው መለስ ዜናዊና ስብሃት ነጋ ጭምር ጆሮ ጠቢ ሆኖ በታማኝነት በማገልገሉ ባንድ ጊዜ ሀይል መሪ ለመሆን በቅቷል፡፡ ቀጥሎም ፀረ-መለስ ዜናዊ እንቅስቃሴ ያደርጋሉ ብሎ በመፈረጅ በርካታ ታጋዮችን በማስረሽኑ የክፍለ ጦር አዛዠ ሆኖ ተሸሟል፡፡
ሆኖም ሳሞራ የኑስ የወታደራዊ አዛዠነቱን ቦታ ይያዝ እንጂ አንድም ጊዜ እራሱን ችሎ ያዋጋበት ጊዜ የለም፡፡ በሚመራው ስራዊት እጅግ በጣም የሚጠላ፣ ሁሉም የሚያዋርደው እና መሳቂያ መሳለቂያ የሚያደርገው ነበር፡፡
ሳሞራ የኑስ በቅርቡ በ1991 ዓ.ም ከኤርትራ ጋር በተደረገው ጦርነት ገና አንድ ጥይት ሲተኮስ ከዛላንበሳ ግንባር ፍርጥጦ አዲግራት በመግባቱ የሚመራውን ክፍለ ጦር ሙሉ በሙሉ አስደምስሶታል፡፡
ሳሞራ የኑስ አሁንም ቢሆን እስከ ጀነራልነት ማዕረግ ደርሶ የመከላከያ ኤታማጆር ሹም ለመሆን የበቃው ለመለስ ዜናዊ ባለው ታማኝነት ብቻና ብቻ ነው፡፡በመሆኑም መለስና ተከታዪቹ በእነሱ ግምት ለወደፊቱ የስልጣን ህልውናቸው ስጋት የሚደቅኑ አባላትን በማስረሸን ያስወገዷቸው በሳሞራ የኑስ አማካኝነት ነው፡፡ ሀየሎም አርአያን ጨምሮ፡፡ ሱዳናዊው ሳሞራ፤ ኤርትራ ሳህል ከርከበት የተወለደው ሳሞራ፤ ዘንባባና አከት ከጫካ እየለቀሙ የሚሸጡ እጅግ በጣም ችግረኛ ወላጆች ስለነበሩት አንድ ቀን ጠግቦ በልቶ የማያውቀው ሳሞራ፤ የአብረሃ ወአፀብሃ ዝነኛው ደድብ ተማሪና በህወሓት ውስጥ በፈሪነቱ ስሙ ገናና የሆነው ሳሞራ፤ የዛሬው የጦር ሳይንስ መሀይም የመጀመሪያው ጀነራል ሳሞራ የኑስ ከእግር ጥፍሩ እስከ ጭንቅላት ፀጉሩ ድረስ በወንጀል የጠለቀ ነው፡፡ ቂመኛ በመሆኑ ፈሪነቱን ሊያጋልጡ የሚሞክሩ በርካታ ታጋዮችን ጊዜ እየጠበቀ ሰበብ አስባብ በመፍጠር ረሽኗቸዋል፡፡
ሳሞራ የኑስ ሰነፍ፣ ፈሪና አድርባይ ብቻ ሳይሆን ሴሰኛም እንደሆነ ይነገራል፡፡ በበረሃ በርካታ የህወሓት ታጋይ የሆኑ ሴቶችን ድፍሯል፡፡ ይባስ ብሎ የተደፍሩት ሴቶች እንዳያጋልጡት ቀድሞ የፈጠራ ክስ በመመስረት ሐለዋ ወያኔ ወደተሰኝው አደገኛ እስር ቤት ይልካቸውና በዚያው ይረሸናሉ፡፡ ለአብነት ያክል በ1974 ዓ.ም ርግበ ሰለሞን እና ፀጌ ሰለሞን የተባሉትን ታላቅ እና ታናሽ እህትማማቾች በየተራ ካባለገ በኋላ ነውረኛ ተግባሩ ሊጋለጥበት ሲሆን “ሁለቱ ሴቶች አደገኛ ህንፍሽፍሾች ናቸው” በማለት ወደ ፃኢ ሀለዋ ወያኔ ልኳቸዋል፡፡ ከዚያም ጉዳዩ ወደስብሃት ነጋ ተላልፎ ስብሃት ነጋ ሁለቱን እህትማማች ሴቶች አንድ ጉድጓድ ውስጥ ገብተው ተጋድመው በጥይት ተደብድበው እንዲገደሉ አድርጓል፡፡
ሳሞራ የኑስ ዛሬም የመኪናውን የሰሌዳ ቁጥር በጥቁር ፕላስተር እየለጠፈ በየሴተኛ አዳሪዎች ቤት እንደሚልከሰከስ ብዙዎቹ ይመሰክራሉ፡፡
ይህ መረጃ የተገኘው ከአርበኞች ግንቦት 7 ድምጽ ነው:: 

No comments:

Post a Comment