Sunday, March 20, 2016

ነገሩ የሆነው በ1997 ምርጫ ወቅት ነው ።

ከአዲስ አበባና ከተለያየ አካባቢ በአጋዜ ጦር ያታፈሱ ሰላሳ ሁለት ወጣቶች አዲስ አበባ ፓሊስ ኮሚሽን ይታሰራሉ ወቅቱ የተረጋጋ ባለመሆኑ ወጣቶቹ ላይ የሚወሰደውን እርምጃ የሚያውቀው አንድ ሰው ብቻ ነው ። የሚጠበቀው የእሱ ትዕዛዝ ነው ከስር ያሉት የህዝብ ግብር ተሰብስቦ ደሞዝ የሚበሉ ፓሊስ ሜስጥረኞች የስርአቱ ዘብ ጠባቂዋች በወቅቱ የነበሩት ስምንት ነበሩ የእነዛ ሰላሳ ሁለት ሰዋች ነብስ በእነሱ እጅ ሆነ እነሱን የሚያዝ ያ አንድ ግለሰብ ይሰበስብና ይወገዱ የሚል ትዕዛዝ ያዛል ያን ትዕዛዝ ለመፈፀም ሲባል ከባድ መሳሪያ ይመጣል እነዛ ንፁሀንን በእነዛ ስምንት ሰዋች ፊርማ ተረሽነዋል ።

ፊርማወን ፈርመው ፍርድ ያስተላለፉ የፓሊስ አካላት በአሁኑ ወቅት በደህና የስልጣን እርከን ላይ ይገኛሉ ።
ይሄን ያጫወተኝ የእነዛ ንፁሀን ደም እንቅልፍ ያሳጣው አባላቸው ሲሆን ቤተክርስትያን ሊመክረኝ ቁጭ ብለን ለህሊናው የከበደው ከስምንቱ አንድ ነው ።

No comments:

Post a Comment