Tuesday, January 7, 2014

ኮካኮላ የቴዲ አፍሮ ውል እንዲሰርዝ ዘመቻ ተጀመረ

በ 2014 ብራዚል ለሚካሄደው የአለም ዋንጫ ላይ ቴዲ አፍሮ የክብር እንግዳ እንዳይሆን አዲስ ዘመቻ በእነ ጃዋር መሃመድ መጀመሩ ተሰማ።
በዓለም ዙርያ ያሉ ኢትዮጵያውያን በሳውዲ ለተፈናቀሉ ወገኖች እየተረባረቡ ባሉበት በዚህ ፈታኝ ወቅት፤ ጃዋር እና ሜንጫዎቹ ጸረ-ኢትዮጵያዊነት ዘመቻቸውን በስፋት ተያይዘውታል። በዛሬው እለት ከአዲስ አበባ በደረሰን ዜና መሰረት ኮካኮላ የቴዲ አፍሮን የአለም ስፖርት ፌዴሬሽን (ፊፋ) ስፖንሰርነት እንዲያነሳ ጠይቀዋል። አዲስ አድማ ለመጀመርም ዝግጅታቸውን አጠናቀዋል።
በ 2014 ብራዚል ለሚካሄደው የአለም እግር ኳስ ዋንጫ አፍሪካን ወክሎ እንዲገኝ ኮካኮላ ቴዲን የመረጠው መሆኑ ይታወሳል። የአለም ስፖርት ፌዴሬሽን (ፊፋ) ወጣቱ ቴዲ አፍሮ አፍሪካን እንዲወክል መምረጡ ዘረኞቹን አስቆጥቶ እንደነበር የሚታወስ ነው።

ቴዲ አፍሮ በአለም መድረክ ላይ የሚያቀርበው ኢትዮጵያዊ የሙዚቃ ቃና ሀገራችንን እና መላው አፍሪካን የሚያስጠራ ነው።
የሄነከኑ አድማ በኦህዴድ ብርቱ ጥረት የተሳካላቸው እነኚህ ባለ አድማዎች፣ ሰሞኑን የደስታ መግለጫቸውን በየድረ-ገጾቻቸው ላይ እየተለዋወጡ እንደሆነ ተገልጿል። ሄኒከን ኮንሰርቱን የሰረዘው ከኦህዴድ በተላለፈ ቀጭን ትእዛዝ ስለመሆኑ ማስረጃው አሉ።
እነ ጃዋር በዚህ አላበቁም። በዲሴምበር 8፤ 2013 በተላለፈ የአቶ ቡልቻ ደመቅሳ እና ሌሎች ምሁራን ቃለ-ምልልስ ምክንያት የጀርመኑ (ዶቸ ቨለ) የአማርኛ ድምጽ ሬዲዮ ጋዜጠኛ ከስራ እንዲነሳም ከአቤቱታ ጋር ቀጭን ትእዛዝ ለቦርዱ አስተላልፎ ነበር። የዶቸ ቨለ ቦርድ ላይ ኦህዴድ ተጽእኖ ስለሌለው ይህ ዘማቻ ሊሳካ አልቻለም።
የኮካኮላው ዘመቻ የተነጣጠረው በቴዲ አፍሮ ላይ ሳይሆን በአኢትዮጵያዊነት ላይ ስለሆነ በአለም ዙርያ ያሉ ኢትዮጵያውያን ዝምታውን በመስበር በነዚህ ሰዎች ላይ የሶሻል ሚድያ ዘመቻ መክፈት ይገባቸዋል።
ቴዲን በርካቶች እንደሚወዱት ሲያወሩ እሰማለሁ። በሚያስፈልገው ሰዓት ግን የ’ላይክ’ ስጦታቸውን ሢሰጡት አላይም። አንድ ኢትዮጵያዊ አርቲስት በዓለም ዋንጫ ውድድር ላይ እንዲያቀነቅን በፊፋ ሲጋበዝ ቴዲ የመጀመሪያው ነው። ይህ ለአገራችን ታላቅ ኩራትና ክብር ቢሆንም፤መንግስታዊ ሚዲያዎች በዜና ደረጃ እንኳ ጥቂት ሽፋን ሊሰጡት አልቻሉም። ያ ለምን እንደሆነ ይገባናል… ከሁሉም አስገራሚው ነገር ግን ኢህአዴግ የአገርን ስም ያስጠራን እና ስለ ፍቅር እያቀነቀነ ያለን ከያኒን ጨርሶ ለመስበር በተነሳበት ወቅት፤ የቴዲ አፍቃሪዎች ነን የሚሉ ወገኖች አንዲት ሰከንድ በመስጠት በፊፋ ስለመመረጡ የሚያትተው ገጽ ላይ በጣታቸው “ላይክ”ን በመጫን አጋርነታቸውን መግለጽ አለመቻላቸው ነው።የቴዲን የፌስ ቡክ ገጽ ከ150 ሺህ የሚልቁ ሰዎች “ላይክ” ቢያደርጉትም ፤ ከታች እንደምትመለከቱት በመጪው ዓመት በብራዚል በሚደረገው ጨዋታ እንዲያቀነቅን በኮካ ኮላ ስፖንሰር አድራጊነት በፊፋ ስለመመረጡ የሚያትተው ላይ “ላይክ” ያደረጉት ገና 300 እንኳ አልሞሉም። በጣም ይገርማል!! እናም….አገራችንን እንወዳለን የምንል እና ኢትዮጵያዊ አርቲስት በዓለም ዋንጫ መድረክ ላይ የማዬት ጉጉት ያለን ሁሉ በዚህ ገጽ “ላይክ” በማስቀመጥ ኮካ ኮላዎችን እናስደንቃቸው።
http://www.facebook.com/pages/Teddy-Afro-to-represent-Africa-for-2014-FIFA-Coca-Cola-world-cup/217835185067743

No comments:

Post a Comment