Wednesday, December 4, 2013

መቐለ እንደገና በእሳት ጋጠሎ ጋየች! Abraha Desta

(ለህወሓት ደጋፊዎች ‘ተናጠች’ ልበለው ቃል ተሳሳተ ብላቹ ለመተቸት እንዲመቻቹ)
ትናንት ማክሰኞ በትራንስፎርመር መቃጠል ምክንያት 70 ዎርክሾፖች በ06 ቀበሌ (ኢንዱስትሪ ዞን) በእሳት ቃጠሎ መውደማቸው ፅፌ ነበር።
ዛሬ ሮብ ሌሊት ደግሞ በዓዲ ሐቂ ገበያ የእሳት ቃጠሎ አደጋ ደርሶ ብዙ ንግድ ቤቶች ወድመዋል። በተመሳሳይ አጋጣሚ ዛሬ ሮብ ጠዋት በዓዲሹምድሑን ሰፈር በእሳት ቃጠሎ አደጋ ንብረት ወድመዋል።

መቐሌ በሁለት ቀናት ዉስጥ በሦስት አቅጣጫዎች (ሰሜን፣ ምዕራብና ደቡብ) የእሳት አደጋ ሰለባ ሆናለች። የማክሰኞው አደጋ በትራንስፎርመር መቃጠል ምክንያት ሲሆን የዛሬው የዓዲ ሐቂና የዓዲሹምድሑን ቃጠሎ መንስ ኤ ግን እስካሁን በትክክል አልታወቀም።

No comments:

Post a Comment