Wednesday, May 7, 2014

ብአዴን ማን ነው? (ገብረመድህን አርአያ፣ አውስትራሊያ)

ገብረመድህን አርአያ፣ ከአውስትራሊያ

Click here for PDFAto Gebremedhin Araya is one of former Tigray People Liberation Front (TPLF) leaders

የአንድን ድርጅት ማንነቱን ከማቅረብ በፊት ቀደም ብሎ የተፈጸመውን ስህተት፣ ቀጥሎም ኢህአፓን ለማጥፋት በህወሓት እና በሻእቢያ የደረሰበትን ጥቃት አጠር ባለ መልኩ ማቅረብ አስፈላጊ ይሆናል።
የስትራተረጂ ስህተት ለከባድ ወድቀት ይዳርጋል።
ኢህአፓ ትግሉን የጀመረው ገና በ1960 መጀመሪያ ነበር። አብዮቱ እየተቀጣጠለ ሃገር አቀፍ ሆነ። ዘውዳዊ ስርዓት ወድቆ በማርክሲዝም ሌኒኒዝም ርእዮተ ዓለም የሚመራ ሶሻሊዝም የኢትዮጵያ ስርአት እንዲሆን ነበር። ይህ ግራ አክራሪ ስታሊኒዝም በቀ. ኃ. ሥ. ዩኒቨርሲቲ ይማሩ በነበሩ የተሰባሰበ ቡድን፣ የወቅቱ አብዮተኞች ተገቢውን መልክ የያዘ አደረጃጀት ያልነበረው፣ አብዮተኛ የሚል ስም በማግኘታቸው ብቻ “ዲሞክራሲያ” ተብሎ የሚታወቀውን የኢህአፓ ልሳን በየሳምንቱ በመበተን አሁን ኢትዮጵያ የደረሰባትና እየደረሰባት ያለው ከባድ ችግር የከፈተው እነ ዋለልኝ መኮንን እና የኢህአፓ ግብረአበሮቹ የስታሊን ደቀ መዛሙርት ኢትዮጵያን አደጋ ወስጥ ጣሏት። በዚህ ወቅት ሰፊውን ትኩረት የሰጡት፤

1. በኤርትራ ጥቅያቄ ላይ ኢህአፓ ያለው አቋም ኤርትራ ከዚህ ቅኝ አገዛዝ ነፃ በመሆን ተገንጥላ ነፃ መንግሥት ማቋቋም ሙሉ መብቷ መሆኑን ያምናል፤
2. ኢትዮጵያ የብሄር ብሄረሰቦች ወህኒ ቤት እንደመሆኗ የኢህአፓ አቋም በዚሁ ጥያቄ ላይ ርቱእና ግልጽ ሲሆን፣ ብሄር ብሄረሰቦች የራሳቸውን እድል በራሳቸው በመወሰን እስከ መገንጠል መብታቸው ያልተገደበ ነው ይላል።
ይህ ትንታኔ ማንም ኢትዮጵያዊ በተጨማሪ ለማረጋገጥ ክፈለገ “ዲሞክራሲያ” ቅጽ 8 ቁጥር 1፣ የካቲት 23 ቀን 1973 የታተመውን ሙሉ ሃሳቡን በድጋሚ ጽፎታል፣ የቃላት ለውጥ በትንሹ ቢኖርበትም። ይህንን ጽሑፍ ለማግኘት EPRP በሚለው ድረገጽ በመግባት የዲሞክራሲያን እትም ከ1961 እስከ ዛሬ የሚለውን ፈልጋችሁ አንብቡ። ይህ ጽሑፍ የሚያሳዝነው ኢህአፓ አሲምባ
እንደገባ ታጋዮቹ በፈጠሩት ጫና በሻእቢያ 1ኛ ጉባኤ 1969 መጨረሻ የአቋም ለውጥ በማድረግ ኤርትራ የኢትዮጵያ አካል ናት፤ የኤርትራ ጥያቄ የዲሞክራሲ ጥያቄ በመሆኑ ትግሉ የሁሉም ኢትዮጵያዊ ትግል ስለሆነ ኤርትራም የዚሁ አካል እንጂ ቅኝ ተገዢ አይደለችም በማለት በጉባኤው የሰጠው ውሳኔ ቅጥረኛው ህወሓት ታህሳስ 1972 የኢህአፓ ተዋጊ ክንፍ ሰራዊት ከባድ መስዋእትነት ክፍሎ በወያኔ ተደመሰሰ። በውጭ ሃገር የሚኖሩ የኢህአፓ አመራር በየካቲ 1973 በዲሞክራሲያ ልሳን ያወጡት ጽሑፍ የኢህአፓው ተዋጊ ክንፍ ኢህአሠ ታጋይ ለናት ሃገሩ ኢትዮጵያ የከፈለውን መስዋእትነት ውድቅ ለማድረግ የታቀደ ነው፤ ለምን?
ከላይ የተጠቀሱት ሁለት ነጥቦች የኢህፓ አመራር በዲሞክራሲያ ልሳኑ ደጋግሞ በመዘርዘር ጠባቦችና ጸረ ኢትዮጵያ አንድነትና ሉአላዊነት ሃይሎች እንዲፈጠሩ አደረገ። [ሙሉውን ለማንበብ እዚህ ይጫኑ]

No comments:

Post a Comment