Saturday, July 11, 2015

በሰማያዊ ፓርቲ አባላት ላይ ተከፈተው የእስር ዘመቻ ዛሬም ቀጥሏል

ዛሬ ሐምሌ 4 2007ዓ.ም ረፋዱ ላይ አቶ መርከቡ ሃይሌ ሰሞኑን ሲከታተሉት በነበሩ ደህንነቶች እና ፖሊስ ታፍኖ ለጊዜው ወደአልታወቀ ቦታ ተወስዷል፡፡
በተመሳሳይ ሁኔታ ትናንት በኢህአዴግ የታሰረው አቶ ደብሬ አሸናፊ ዛሬ ረፋዱ ላይ ቤቱ በከፍተኛ የታጠቁ ሃይሎች ተከቦ ፍተሻ የተካሄደበት ሲሆን አሁን በጉለሌ አካባባቢ ላዛሪስት ፖሊስ ጣቢያ ታስሮ እንደሚገኝ ተረጋጧል፡፡

በሌላ በኩል ትናንት ታፍነው የታሰሩት በሰሜን ሸዋ የሰማያዊ ፓርቲ የተወካዮች ምክር ቤት ዕጩ የነበሩትን አቶ ዘነበ ደሳለኝ፣ የፓርቲው ንብረት ያዥ የሆኑትን አቶ መንግስቱ ተበጀና የቀድሞው አንድነት የቀጠና አመራርና በአሁኑ ወቅት የሰማያዊ ፓርቲ አስተባባሪ የሆኑትን አቶ ቴዎድሮስ ሀብቴ ውጬ አቶ ምንተስኖት ወንዳፈራሁ እና አቶ ብሩ አይደፈር የተባሉ የሰማያዊ አባላት ታፍነው መታሰራቸውን ታውቋል፡፡
Semayawi Party- Ethiopia's photo.

No comments:

Post a Comment