Thursday, July 9, 2015

የህዝበ ሙስሊሙ ኮሚቴ ጠበቃ ተማም አባቡልጉ የጥብቅና ሙያቸው ኮሚቴዎቹ የጥፋተኝነት ብይን በተላለፈበት ቀን መሰረዙ ታወቀ

ጠበቃ ተማም አባቡልጉ
ጠበቃ ተማም አባቡልጉ

ሰበር ዜና ቢቢኤን
ቢቢኤን ሃምሌ 2/2007

የህዝበ ሙስሊሙ መፍትሄ አፈላላጊ ጠበቃ የሆነው ጠበቃ ተማም አባቡልጉ በፍርድ ቤት ላይ በሚያደርጋቸው ክርክሮች በተለይም መንግስት ከጅሃዳዊ ሀረካት ጀምሮ የሰራቸውን ሸፍጦችና ኢትዪጲያዊ ውስጥ የፍትህ ስርአቱን ዝቅጠት በመረጃና በህግ በማጣቀስ በተለያዩ ሚዲያዎች ላይ በማጋለጣቸው ምክኒያት ከዚህ ክስ ተመስርቶባቸው እንደነበር ይታወቃል፡፡

ከዚህ በተጨማሪም ማስፈራሪያና ዛቻዎች ከመፈጸማቸውን ሌላ እብድ በሚመስል ሰው በመላክ ድብደባ እንደተፈጸመባቸው ይታወቃል፡፡

ይህ ሁሉ ግፍ ተፈጽሞባቸው በጀግንነት ከስራቸው ያልቆሙት እንዲሁም የህግ ክፍተቶችን ጭምር በማጋለጥ፤ ከኮሚቴዎቹ በተጨማሪ መንግስት የከሰሳቸው የነ አብራ ደስታ ጠበቃ የነበሩትን ተማም አባቡልጉን መንግስት በኮሚቴው ላይ የጥፋተኝነት ብይን ባስተላለፈበት እለት የጥብቅና ሙያቸውን ፍቃድ ፍትህ ሚኒስትር መሰዘረዙ ታውቋል፡፡
አቶ ተማም አባቡልጉ ያለ ምንም ፍርሃት እውነታውን በሚዲያዎች ላይ በማጋለጥ ታላቅ አስተዋጾ ያበረከቱ፤ በብዙዎች ዘንድ በጀግንነት የሚጠሩ ፤ ፤ለሙያቸው ያደሩ ጠበቃ መሆናቸው ይታወቃል፡፡ ቢቢኤን ጠበቃ ተማም አባቡልጉን በማነጋገር ተጨማሪ መረጃ ይዞ የሚቀርብ ይሆናል::
- See more at: http://www.zehabesha.com/amharic/archives/44909#sthash.k0E1ZbL7.dpuf

No comments:

Post a Comment