Thursday, July 9, 2015

2 ዓለም አቀፍ ሽልማቶችን እስር ቤት ሆና ያሸነፈችው ርዕዮት ዓለሙ

reyot
ጋዜጠኛ ርዕዮት ዓለሙ ተፈታች
(ዘ-ሐበሻ) ጋዜጠኛና መምህርት ርዕዮት ዓለሙ ትናንት ጁላይ 9 ቀን 2015 ዓ.ም የ እስር ጊዜዋን አጠናቃ ተፈታች። የመንግስት ሚድያዎች ጋዜጠኛዋ የአመክሮ ጊዜ ተሰጥቷት እንደተለቀቀች አድርገው ቢዘግቡም እውነታው ግን ርዕዮት የአመክሮ ጊዜዋን ጨርሳ የነበረው ባለፈው ጥቅምት ወር ነበር።
በሽብር ወንጀል ተከሳ 14 ዓመት ተፈርዶባት የነበረችው ይህችው ጋዜጠኛ በይግባኝ ቅጣቱ ወደ 5 ዓመት ዝቅ ብሎላት የነበረ ሲሆን እነዚህን ዓመታት በእስር አሳልፋ ከቤተሰቦቿ ጋር ተቀላቅላለች።

በእስር በነበረችበት ወቅት በሚደርስባት የሰብአዊ መብት ጥሰት የርሃብ አድማ እስከማድረግ ደርሳ የነበረችው ርዕዮት እህቷ እስከዳር ዓለሙ ሳይቀር እንዳትጠይቃት ታግዳ እንደነበር የሚታወስ ነው።
ባለቤቷ ጋዜጠኛ ስለሺ ሃጎስ አንድነት በጠራው ስብሰባ ላይ ተገኝቷል በሚል በፖሊስ ጉዳት የደረሰበት መሆኑም ይታወሳል። ር ዕዮት እስር ቤት እያለችም የዩኔስኮን የፕሬስ ነፃነት አዋርድ እንዲሁም በዓለምአቀፉ የሴቶች የመገናኛ ብዙኃን ድርጅት – International Women’s Media Foundation – IWMF “በጋዜጠኝነት ለተሠራ ጀብዱ ሽልማት” የሚል አዋርዶችን አሸንፋለች።
- See more at: http://www.zehabesha.com/amharic/archives/44912#sthash.Vv3rh1tX.dpuf

No comments:

Post a Comment