Thursday, February 26, 2015

እምቢተኝነት

በአዋጅ የተደነገጉ የሕዝብን አሳብን በነጻነት የመግለጽ፣ የመደራጀትና የመሰብሰብ እንዲሁም ሰላማዊ ሰልፍ የማድረግ መብትን እየሸረሸሩና አዋጅን በተራ መመሪያ እየሻሩ የስቃይ ቀንበሩን ያከብዱበታል ፡፡በየትኛውም ሁኔታ ማለትም የሰብአዊ መብቱ የተረገጠውን፣ የሃገሬ ጉዳይ ያገባኛል ስላለ እንደ ሁለተኛ ዜጋ እየታየ የሚሰቃየውን የነፃነት ታጋይ፣ በስርዓቱ ብልሹና የተዝረከረከ አሰራር በኑሮ ውድነት እየማቀቀ ያለው የህብረተሰብ ክፍል ለጥያቄው ተገቢውን መልስ ወይ መፈትሄ ከመስጠት ይልቅ በተራ ካድሬያዊ ዲስኩር ከላይ ለዘረኛው ስርዓት ቃል አቀባይ ከሆነው ጠ/ሚ ተብዬው እስከ ልማታዊ ጋዜጠኛ ነን እስከሚሉት ድረስ በርሃብ ለጠወለገው ምስኪን ሕዝብ ጥጋብን፣ በገዛ ሃገሩ ፍትህ አጥቶ ለሚሰቃየው ፍትሃዊነትን እንዲሁም ሰብአዊ መብቱ ተገፎ ነፃነቱን ለተነጠቀው ሕዝብ ዴሞክራሲን ነጋ ጠባ ይሰብኩታል፡፡

ይህው የወያኔ ዘረኛ ቡድን ስለፈጠረው ሃገራዊ ቀውስ ብዙ ብዙ ቢባልም የዚህን መርዘኛ ስርዓት ሰንኮፍ ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ ነቅሎ ለመጣል ከምርጫ ይልቅ ሕዝባዊ እምቢተኝነት(አመጽ) ስለመሆኑ ስርዓቱ በሚያሳየውና ከሚሰጋባቸው ነገሮች ለመረዳት ይቻላል፡፡
እንደሚታወቀው በተደጋጋሚ የተካሄዱት ምርጫዎች ከምርጫ 97 ውጪ በቀጥታም ይሁን በተዘዋዋሪ ለወያኔ መሳሪያ ከመሆን ወጪ የስርዓቱ የአፈና መዋቅር ተቃዋሚዎችን የሚያወላዳ አልነበረም፡፡ ይህ ማለት ይካሄዱ የነበሩ ምርጫዎች በህውሃት ዘረኛ ቡድን በተጠና የአፈና እንዲሁም በዋነኝነት ምርጫን ምርጫ ሊያሰኙ የሚችሉ ገለልተኛ ተቋማት በጠቅላላ በስርዓቱ መዋቅር የተዋጡና የተተበተቡ በመሆናቸው ለመገናኛ በዙሃን ሸፋንና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ መደለያ ካልሆነ በስተቀር ምርጫው ሳይጀመር ውጤቱ የታወቅ እንደ ነበር ከማንም የተሰወረ አደለም፡፡ ስለሆነም የህውሃት ቡድን አምስት አመት ጠብቆ የሚመጣ ምርጫ ከላይ እንደተጠቀሰው ለአንዳንድ ግብአት ይጠቀምበት እንደሆን እንጂ ምርጫ ስለተቃረበ እንቅልፍ የሚያጣ አይመስልም ምክንያቱም የምርጫ አስፈጻሚ አካላት እስከ ፍትህ ስርዓቱ በእጁ ናቸውና፡፡
የልቁንም ለዚህ እኩይ ስርዓት የራስ ምታት የሚሆንበትና ሰላም የሚነሳው ሕዝባዊ እምቢተኝነት(አመጽ) ነው፡፡
ከሰብኣዊ

No comments:

Post a Comment