Sunday, June 14, 2015

በጊቢ ገብርኤል አካባቢ በተነሳ ቃጠሎ ካለቅያሪ ልብስ የቀሩ 25 ሰዎች የድረሱልን ጥሪ እያሰሙ ነው

wereda 8
wereda 8 addis
wereda 8 addis ababa
wereda 8 gibi geberil
(ዘ-ሐበሻ) በአዲስ አበባ ወረዳ ስምንት በተለምዶ ጊቢ ገብርኤል አካባቢ ተብሎ በሚጠራው ሰፈር በደረሰ የ እሳት አደጋ ቤታቸው የወደመባቸው ወገኖቻችን ለወገኖቻቸው የድረሱልን ጥሪ እያሰሙ መሆኑን ለዘ-ሐበሻ የደረሰው መረጃ አመለከተ::
የዘ-ሐበሻ ዘጋቢዎች አካባቢውን ሄደው ከጎበኙ በኋላ እንደጠቀሱት ሰኔ 3 ቀን 5 ሰዓት አካባቢ በደረሰው ቃጠሎ 25 ሰዎች ንብረታቸው እና ቤታቸው ወድሞባቸው ካለቅያሪ ልብስ ቀርተዋል::

የዚህ የ እሳት አደጋ መንስ ኤ ምን እንደሆነ ገና እየተጣራ መሆኑን የጠቀሱት የዘ-ሐበሻ ዘጋቢዎች ነዋሪዎቹ በአሁኑ ወቅት ወረዳ 8 ላይብረሪ ውስጥ ተጠልለው እንደሚገኙና የወገኖቻቸውን እርዳታና ማጽናናት እንደሚሹ ተገልጿል::
በ እሳት አደጋው ጉዳት ከደረሰባቸው መካከክል ስሜ እንዳይጠቀስ የተፈለገች እህት በቅርቡ ወደ ቻይና ለመሄድ በዝግህት ላይ የነበረች ቢሆንም ሁሉም የመጓጓዣ ዶክመንቶቿ በአደጋው ቃጠሎ እንደደረሰበት ለማወቅ ተችሏል::
- See more at: 

No comments:

Post a Comment