Tuesday, November 19, 2013

ለመላዉ ኢትዮጲያዊያን፡- ከሰማያዊ ፓርቲ የተላለፈ ጥሪ.. በታላቁ ሩጫ ላይ ሀዘናችንን እንግለፅ!

ለመላዉ ኢትዮጲያዊያን፡- ከሰማያዊ ፓርቲ የተላለፈ ጥሪ
በሳዑዲ ለሚሞቱና ለሚንገላቱ ወገኖቻችን ያለንን ተቆርቋሪነት
አሁንም ተጠናክሮ መቀጠል አለበት፡፡ ሰሞኑን በአዲስ አበባዉ
ሰልፍ የተፈፀመዉን መንግስታዊ ሽብር ሁላችንም በሀዘን
አልፈነዋል፡፡ ነገር ግን ለብሔራዊ ቡድናችን ያደረግነዉ ጥሪ
በቸልተኝነት መታለፉ ፣ በሀይማኖት ተቋማትም የሚፈለገዉን
ያህል ጥሪዉን ባለመቀበላቸዉ የዘንን ቢሆንም ህዝቡን ከጎናችን
በማቆም የደረሰበትን ነገር ሁሉ በፅናት መቀበሉ አኩርቶናል፡፡
በቀጣይነትም የተለያዩ ስራዎችን ለመስራት ታስቧል፡፡ ከነዚህ
ዉስጥ በመጪዉ እሁድ ህዳር 15 ቀን በአዲስ አበባ በሚካሄደዉ
ታላቁ ሩጫ በኢትዮጲያ ላይ የምንሳተፍ ሰዎች ጥቁር ሪቫኖችን
አድርገን እንድንሳተፍ፤ በአንድነት መንፈስም አጋጣሚዉን በሳዑዲ
ስለሚሞቱና ስለሚንገላቱ ሰዎች ድምፃችንን የምናሰማበት
ሀዘናችንን የምንገልፅበት እንዲሆን ሰማያዊ ፓርቲ በግፉአን
ወገኖቻችን ስም ጥሪ ያስተላልፋል፡፡
የሰማ ላልሰማ ያሰማ!!

No comments:

Post a Comment