Wednesday, November 27, 2013

ኮንዶሚንየም ቤቶች የዝሙት መናሀሪያ ሆነዋል

መንግስት በተለምዶ ኮንደሚንየም ብሎ አንደነገሩ ገነባብቶ ቀብቶ ከሰራቸው እና ለህዝብ ካደላቸው በኣዲስ ኣበባ በየቦታው ባሉ የባለኣራት ፎቅ ኣፓርትመንት የጋራ የመኖሪያ ቤቶች ኣካባቢ የዝሙት፥ የመጠጥ እና የኣደንዛዥ እጽ መናሀሪያዎች ሆነዋል ሲሉ ነዋሪዎች ተናገሩ::
የድሮ ስንቅ እና ትጥቅ በኣሁኑ “ጎተራ” በሚባለው ኮንዶሚንየም ሳይት ውስጥ ያለውን ሁኔታ ከኣካባቢው ነዋሪዎች ኣንዱ እንዲህ ስል ይገልጸዋል፥፥
መደበኛ ስራው የቤት ደላላ የነበረ ሲሆን ኣሁን ግን በኮንዶሚንየም ለሚገኙ ሴተኛ ኣዳሪዎች ማምሻውን ደንበኛ በማፈላለግ ይሰራል፥፥ኣካባቢው ሃያ ኣራት ሰኣት ክፍት ነው:: በስፍራው የቁጥራቸው ትንሽ የማይባል የመጠጥ ፥የጫት ቤቶች : ራቁት መደነሻዎች ጭምር ከ ምድር እስከ ላይ ሶስተኛ እና ኣራተኛ ፎቆች ላይ ይገኛሉ ይለን እና ለ ዝሙት ንግድ የሚሆኑ ክፍሎች ይገኛሉ ይላል::
በዚሁ የቤቶች ሳይት ፤ኣልፎ ኣልፎ መደበኛ ነዋሪዎች ቢኖሩም ፥ በጥቅሉ ስፍራው ግን ሌላይኛው የቀለጠው መንደር ነው ብሎም ይገልጸዋል::
ይቀጥል እና ኣሁን ይላል ኣሁን እንደምታውቀው በኣቅራቢያው ክነበረው ታዋቂው ኮንኮርድ ናይት ክለብ ሴት ፍለጋም ሆነ ለ ጭፈራ ሰዉ መሄድ ኣቁምዋል::ምክኒያቱን ሲያስቀምጥም ሴቱ እና ጭፈራው በሙላ እዚህ ኮንዶሚንየም ስለሚገኝ ፥ ኮንኮርድ ተዘግቶ እሱን የሚያስንቅ ሁሉ ነገር እዚህ ኮንዶሚንየም ስለሚገኝ ነው ይላል:: ኣያይዞም የሴት ኣይነት ከ ህጻናት እስከ ኣዋቂ በሽ እንደሆነ ያሰቀምጥእና ደንበኞቻቸውም ከ መደበኛ ነዋሪ እስከ ባለስልጣን፥ ከዲያስፖራ እስከ የውጭ ዜጋ እንደሆኑ ተናግሮ፤በእነሱም ቊዋንቁዋ [ ኣጠራር] ለ ኣንድ ኣዳር እድሉ ከቀና እስከ ብር ሶስት ሺ አንደሚቀበሉ ጠቅሶ፥ ወጣ ገባ በሚል ቢዝነስም እያንዳንዱዋ በስራው የተሳተፈች ሴት ከዚያ የማያንስ ገንዘብ ሳትሰራ እንደማታድር ይናገራል::
የምኖረው እዚሁ ኮንዶሚንየም ሁለተኛ ፎቅ ላይ ነው ያለው ይሀው ነዋሪ፥ ጎረቤቶቹም ኣንዲት በዝሙት ስራ የምትተዳደር ሱማሌያዊት እና ሌላ የጫት ነጋዴ ሴት እንደሆነችም ጭምር በመግለጽ የ እሱም ስራ ከበፊቱ የቤት ድለላ ስራ በጣም የተሻለ እንደሆነ ገልጾልኛል::
በላፍቶ ፡በብርጭቆ ፉብሪካ እና ካሳንችስ የኮንዶሚንየም ቤቶች ኣካባቢም የዚሁ ኣይነት ተመሳሳይ ድርጊቶች ማድረጊያዎች ሲሆኑ ፥ በቀጣይነትም የ ኣያት እና ጀሞ ተብለው በሚጠሩት ቦታዎችም ይሀው ነገር መከሰቱ ኣይቀሬ መሆኑን ነዋሪዎች ይናገራሉ::
በተጠቀሱት ኣካባቢዎችም የ ኣንድ ስቱዲዮ የኮንዶሚንየም ቤት ዋጋ እስከ ሶስት ሺ ብር ሲከራይ ፥ጭማሪ ኣንድ እና ሁለት ክፍል ደግሞ እስከ ብር ስድስት እና ሰባት ሺ የመከራየት ኣቅም ኣለው፥፥
ዳግም ኣሁንም ከ ኣዲስ ኣበባ

No comments:

Post a Comment