Monday, October 27, 2014

መቐለ በኣብራሃም ገብረመድህን ትወዛወዛለች; ትቆዝማለችም (በአምዶም ገብረስላሴ -ከትግራይ)

ድምፃዊ ኣብራሃም ገብረመድህን ባወጣው ኣዲስ የሙዚቃ ኣልበም መቐለ እየተወዛወዘችም እየቆዘመችም ትገኛለች።
ማነው መቐለን በኤርትራ ዘፈኖች ያበደች ከተማ ብሎ ፅፎላት የነበረው? ኣሁን መቐለ ከተማ በሁሉም ኣቅጣጫዎችዋ የኣብራሃም ዘፈኖች እየተደመጡባት ይገኛሉ።
Abraham gebremedhin
Abraham gebremedhin
ኣዲሱ የኣብራሃም ኣልበም የህዝቡ ነባራዊ ሁኔታ የሚያንፀባርቁ ሁነዋል።
በተለይ “…ማቻ ይስመዓኒ ኣሎ…”(ምቾት እየተሰማኝ ነው) የሚል ዘፈኑ የህወሓት ከፍተኛ ባለስልጣናት፣ ከህወሓት ባለስልጣናት ተጣብቀው ሃብት ያከማቹና በማከማቸት ላይ ያሉት ነጋዴዎች እና ከቀበሌ በላይ ያሉ ባለስልጣናት “ማቻ ይስመዓኒ ኣሎ” የሚለው ዘፈኑ በየሆቴሉ በየተሃድሶው እያዘዙ ያደምጣሉ፣ ይወዛወዛሉ። ምቾት ስለተሰማቸው ኣብረውት “ማቻ ይስመዓኒ ኣሎ” ይላሉ።

ለላኛዋ ተወዳጅ ዘፈን ደግሞ በህወሓት ኣገዛዝ ሁለመናዊ መብቶች ተነፍጎ፣ ፍትህ ኣጥቶ፣ ስራ ኣጥቶ፣ በእዳ ተዘፍቆ ለውጥ እያናፈቀው ያለው ኣብዛኛው ህዝብና እንደ ኣብራሃ ደስታ የመሰሉ የነፃነት ታጋዮች “…ክሓልፍ እዩ…” (ያልፋል) የምትለው ለቅዱስ ዓላማ የሚደረግ እልህ ኣስጨራሽ ትግል ተዘጋጅቻለው፣ ዓላማየ ለማሳካት ኣስፈላጊው መስዋእትነት እከፍላለው የሚል መልእክት ያዘለች የፅናት ዘፈን ያደምጣል።
የህወሓት ካድሬዎች የኣብራሃም ኣልበም ባይወዱትም ማቻ ሲሰማቸው ተገድደው ይጨፍሩበታል።
በነገራችን ላይ ኣብራሃም ገብረመድህን ከነ ዓሚር ዳውድ(የልጁስም ራኢ መልስ)ብሎ ከስየመውና ኩኩናይ ብሎ ለኣቶ መለስ ካወደሰ ሰለሞን ሃይሌ የበለጠ ተወዳጅነቱ እያስመሰከረ ይገኛል።
እነሱ በ”ማቻ ይስመዓኒ ኣሎ” ሲጨፍሩ እኛና የመቐለ ህዝብ ደግሞ “ክሓልፍ እዩ” እናዳምጣለን ለበለጠ የሰላማዊ ትግል እንነሳሳለን።

No comments:

Post a Comment