Friday, December 14, 2012

ዝርፊያ በኢትዮጵያ ባለስልጣኖች ተጧጥፏል !!


በኢትዮጵያ በ2003 ዓም ብቻ 100 ቢሊዮን ብር የሚጠጋ ገንዘብ ተዘርፎ ወደ ውጭ ባንኮች መግባቱ ታወቀ።

ታህሳስ ፬(አራት) ቀን ፳፻፭ ዓ/ም
ጥናቱን ይፋ ያደረገው አለማቀፍ እውቅና ያለው ግሎባል ፋይናንሻል ኢንተግሪቲ ( Global Financial Integrity ) የተባለው ተቋም ሲሆን በፈረንጆቹ አቆጣጠር በ2010 ወይም በኢትዮጵያ አቆጣጠር በ2003 ዓም ብቻ ከኢትዮጵያ በተለያዩ መንገዶች ተዘርፎ ወደ ውጭ አገር ባንኮች የተላከው ገንዘብ 5 ቢሊዮን 600 ሚሊዮን 400 ሺ ዶላር ወይም በጊዜው በነበረው ምንዛሬ ወደ  100 ቢሊዮን  ብር ነው።
ገንዘቡ የተዘረፈው በአብዛኛው በሙስ እና  በታክስ ማጭበርበር ነው። ገንዘብ በከፍተኛ ደረጃ እየተዘረፈ ወደ ውጭ ባንኮች ከሚላክባቸው አለም አገሮች መካከል ኢትዮጵያ የ15ኛ ደረጃን ይዛለች።  በተጠቀሰው አመት ከቻይና 420 ቢሊዮን፣ ከማሌዢያ 64 ቢሊዮን፣ ከሜክሲኮ51 ቢሊዮን፣ ከሩሲያ 43 ቢሊዮን፣ ከሳውዲ አረቢያ 38 ቢሊዮን፣ ከኢራቅ 22 ቢሊዮን፣ ከናይጀሪያ 19 ቢሊዮን፣ ከኮስታሪካ 17 ቢሊየን፣ ከፊሊፒንስ 16 ቢሊዮን፣ ከታይላንድ 12 ቢሊዮን፣ ከካታር 12 ቢሊየን ፣ ከፖላንድ 10 ቢሊየን፣ ከሱዳን 8 ቢሊየን ከዩናይትድ አረብ ኤምሬትስ 7 ቢሊየን እና ከኢትዮጵያ በ ቢሊየን 6 መቶ ሚሊዮን ዶላር ተዘርፏል።
በ2003 ከኢትዮጵያ የተዘረፈው ገንዘብመንግስት በተመሳሳይ አመት ከበጀተው ብሄራዊ በጀት ጋር ተመሳሳይ ነው። አገሪቱ ከውጭ አገር በእርዳታና በብድር ካገኘቸው ገንዘብ ጋር ሲነጻጸር  የተዘረፈው ገንዘብ በ2 ቢሊየን ዶላር ይበልጣል።  ገንዘቡ ተመልሶ ወደ ኢትዮጵያ ካዝና ቢገባ ኖሮ የአባይን ግድብ ያለምንም መዋጮና ቦንድ ግዢ ለማስጨረስ ያሰችላል።
ይህ ተቋም ከአንድ አመት በፊት በኢትዮጵያ አቆጣጠር ከ1993 እስከ 2002 ዓም 8 ቢሊዮን የአሜሪካን ዶላር ከኢትዮጵያ ተዘርፎ በውጭ ባንኮች መቀመጡን ይፋ አድርጎ ነበር። ባለፉት 10 አመታት ከኢትዮጵያ በአጠቃላይ የተዘረፈው ገንዘብ መጠን ከ13 ቢሊዮን ዶላር በላይ ነው።
አቶ ኤፍሬም ማደቦ 8 ቢሊየን ዶላር ከኢትዮጵያ ተዘርፎ መውጣቱ ሪፖርት በተደረገበት ወቅት ባወጡት አንድ ጥናታዊ ጽሁፍ ላይ ገንዘቡ 90 ሁለተኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች፣ 18 ዩኒቨርስቲዎች፣ 27 ኮሌጆች፣ 36 ሆስፒታሎች፣ 180 ጤና ኬላዎ፣ 6 የዘይት ፋብሪካዎች፣ 4 ሲሚንቶ ፋብሪካዎች፣ 1 አባይ ግድብ፣ አራት የግብርና ኢንዱስትሪዎች ሊያሰራ እንደሚችል መግለጻቸው ይታወሳል።
በጥናቱ ውስጥ እነማን የአገሪቱን ገንዘብ እየዘረፉ ወደ ውጭ አገራት እንደላኩ አልተጠቀሰም። ይሁን እንጅ በኢትዮጵያ ውስጥ ከ80 በመቶ በላይ የሚሆነውን ንግድ የተቆጣጠሩትና በአለማቀፍ ንግድ ተዋናይ የሆኑት የህዝባዊ ወያን ሐርነት ትግራይ ኩባንያ ንብረት የሆነው የትግራይ መልሶ ማቋቋሚያ ፈንድ በእንግሊዝኛው  አጠራር ኢፈርት እና የሼክ ሙሀመድ ሁሴን አሊ አላሙዲን ንብረት የሆነው ሚድሮክ ኢትዮጵያ መሆናቸው ይታወቃል።
ከአመት በፊት የተባበሩት መንግስታት ድርጅት የልማት መርሀግብር በቱርክ በተካሄደበት ወቅት፣ የድርጅቱ ባለስልጣናት በጉባኤው ለተሳተፉት አቶ መለስ ዜናዊ የችግሩን አሳሳቢነት ገልጸውላቸው እንደነበር ይታወሳል።
Illicit Financial Outflows from Ethiopia Nearly Doubled in 2009 to US$3.26 Bln, Says New GFI Report
African Nation Lost US$11.7 Billion in Illegal Capital Flight from 2000 through 2009, Writes GFI Economist

December 5, 2011
Clark Gascoigne, +1 202-293-0740 ext.222


WASHINGTON, DC – Corruption, kickbacks and bribery are on the rise in Ethiopia, according to a forthcoming report from Global Financial Integrity, a Washington-based research and advocacy organization.  According to the study, illicit financial flows out of the African nation nearly doubled to US$3.26 Billion in 2009 over the previous year, with corruption, kickbacks and bribery accounting for the vast majority of that increase.

GFI Economist Sarah Freitas, who co-authored the upcoming report with GFI Lead Economist Dev Kar, revealed the data in a blog post today on the website of the Task Force on Financial Integrity & Economic Development (financialtaskforce.org).

Ms. Freitas wrote:

An upcoming report by Global Financial Integrity finds that Ethiopia, which has a per-capita GDP of just US$365, lost US$11.7 billion to illicit financial outflows between 2000 and 2009.  More worrying is that the study shows Ethiopia’s losses due to illicit capital flows are on the rise.  In 2009, illicit money leaving the economy totaled US$3.26 billion, which is double the amount in each of the two previous years.

The report, titled Illicit Financial Flows from Developing Countries over the Decade Ending 2009, shows that the vast majority of the rise in illicit financial flows is a result of increased corruption, kickbacks, and bribery while the remainder stems from trade mispricing.

Ethiopia is one of the poorest countries on earth.  Plagued by famine, war, and political oppression, 38.9% of Ethiopians live in poverty, and life expectancy in 2009 was just 58 years.   In 2008, Ethiopia received US$829 million in official development assistance, but this was swamped by the massive illicit outflows.  The scope of Ethiopia's capital flight is so severe that our conservative US$3.26 billion estimate greatly exceeds the US$2 billion value of Ethiopia's total exports in 2009.

The people of Ethiopia are being bled dry.  No matter how hard they try to fight their way out of absolute destitution and poverty, they will be swimming upstream against the current of illicit capital leakage.  The global shadow financial system happily absorbs money that corrupt public officials, tax evaders, and abusive multi-national corporations siphon away from the Ethiopian people.

The full article can be read here.

Ethiopia is not the only country to be highlighted in the organization’s upcoming study.  Indeed, in a similar blog post published last week, Ms. Freitas revealed that the report, titled Illicit Financial Flows from Developing Countries over the Decade Ending 2009, found that Syria had lost US$23.6 billion in illegal capital flight from 2000-2009.  The report is the annual update to GFI’s previous studies measuring the illicit financial flows out of 160 different developing nations.  This will be the first of GFI’s studies to include data for the year 2009.

To schedule an interview with Ms. Freitas or Dr. Kar, or to receive an embargoed copy of the report, contact Clark Gascoigne at cgascoigne@gfintegrity.org or +1 202 293 0740 ext.222.



Global Financial Integrity (GFI) is a Washington, DC-based research and advocacy organization which promotes transparency in the international financial system.

For additional information please visit www.gfintegrity.org


    No comments:

    Post a Comment