Monday, October 28, 2013

አድዋዉ ልጅ አድዋ ገባ” የአርማጭሆ ልጅ የት ይግባ?!! (ናደዉ ከዋሽንግተን ዲሲ)

የአድዋዉ ልጅ አድዋ ገባ”
የአርማጭሆ ልጅ የት ይግባ?!!
እንደምን ከረማችሁ ዉድ የኢካዴፍ እድምተኞች “እስቲ ቂማችንን ጥቂት እናቆየዉ” በሚል ርእስ የጀመርኩትን መጣጥፍ “በአሳ ጎርጓሪ ዘንዶ ያወጣል” ቀጥዪ ከክፍል 1-7 ድረስ ይህ ድህረ ገፅ ለንባብ አብቅቶልኛል ክፍል 8-9 ግን ከአንድም ሁለቴ በአደራ ደብዳቤ ሳይቀር ልኬ ሚዛን ባለመድፋቱ ለንባብ አልበቃም(የቅርጫት ራት ሆኗል) ሚዛን የሚደፋ ፅሁፍ ለማቅረብ አስቤ ፅሁፎቼን ቆየት ማድረግ በወሰንኩ ማግስት ዛሬ October 24, ምሽት አንድ ወዳጄ ስልክ ደዉሎ ሰበር ዜና ጀባ አለኝ የአዉራምባዉ አምደኛ ተጋዳላይ ጋዜጠኛ ዳዊት ከበደ ወደ ዘረኛ ግብረአበሮቹ ጉያ መሸጎጡን አጫወተኝ ከላይ በጠቀስኩት ርእስ እንደጠቀስኩት ይህ ሰላይ የትግራይ ጉጅሌ መልእክተኛ አዚህ ሰሜን አሜሪካ ኢሳትንና ሌሎች ጠንካራ ናቸዉ የሚባሉትን ተቃዋሚ ድርጅቶች የመሰለል ተልእኮዉን አጠናቅቆና የዳያስፖራዉን ተቃዋሚ ጓዳ ጎድጓዳ ሰልሎ የቃረማቸዉን የኦዲዮ ቪዲዮና ዳጎስ ያለ ጥራዝ ተሸክሞ አሜሪካ በገባበት አኳኋን ተመልሶ በኢትዮጵያ አየር መንገድ በአራት ኪሎ ቤተመንግስት ገባላችሁ ቡራኬዉንም ተቀብሎ በአዲስ አበባዉ ሸራተን ሆቴል የወሬ ቅራቅምቦዉን ለህወሀት የዜና አዉታሮችና የስለላዉ መረብ ክፍል አለቆቹ እያጋታቸዉ መሆኑን ዉስጥ አዋቂ ምንጮች ሹክ አሉን።
Dawit-Kebede-Awramba-Times-146x200
እዚህ ያለዉ አጃቢዉ ሆድ አደሩ የስዉር ስለላ መረብ ጓዱ የአርማጭሆዉ ጓዱ ወስላታ የደርግ ካድሬ ምርጫዉ ስንሻዉ ቀሪ የመበታተን አጀንዳቸዉን ለማስፈፀም የመመርያ የኪስ ማስታወሻዉን ዳጎስ ካለ የደም ገንዘብ ጋር ተረክቦ ቀጣይ ጥሪዉን ይጠባበቃል በቅርቡም የህወሃት አባልነት ደብተሩ ከምስጋና ጋር እጁ ይገባል።
ነገ አሱም አይኑን በጨዉ አጥቦ ሚስቱንና ልጆቹን እንደለመደዉ ጥሎ ይከተለዋል እስከዚያዉ በአዲስ መልክ በአዲስ መሠሪ ተልእኰ ራዲዮ ጣቢያ የጥላቻና የጋጠወጥ “ዘለፋ ስንቁ” የመንደር አደግ ራዲዮኑን ያገማናል። እኛም ሃይ አንለዉ እጆቻችንን ጉንጮቻችን ላይ አድርገን የገለማ ቀረርቶዉንና ቱማታዉን እናዳምጥለታለን።
ወገኖቼ ኢትዮጵያዉያን ጨካኝና አምባገነን ገዢዎቻችን አገራችንን ጥለንላቸዉ በስደት የመኖር መብታችንን እየከለከሉን ነዉ። ዛሬም እንደትናንቱ በተመሳሳይ ድራማ ያፌዙብናል። አለቆቼ በድለዉኛል አስጥሉኝ አይነት ቀልድ፥እኛም ቄጠማ ጎዝጉዘን ርችት ተኩሰን እንኳን ወደህሊናችሁ ተመለሳችሁ እንላቸዋለን ጓዳ ጎድጓዳችንን መዝብረዉ አላግጠዉብን ተመልሰዉ ይሄዳሉ። ዛሬም እደግመዋለሁ፦”እስቲ ቂማችንን ጥቂት እናቆየዉ”

No comments:

Post a Comment