Saturday, December 6, 2014

ጥቂቶች ሊመነደጉ፤ ብዙዎች አሽቆልቁለዋል!!!


20140911_151218-2-1
Hawi Olani Kesesa
የራበው ሥራ ፈልጐ ማግኘት የማይችልና ልጆቹን ለማስተማር አቅም ያጣ ሰው ከባርነት ነፃ ነው ማለትአይቻልም፡፡” የሚለው የአሜሪካዊው ፕሬዚዳንት ሊንደን ጆንሰን ንግግር እውነትነት አሁን አሁንበጆሮዬ መደወሉ ራሴን እያስገረመኝ መጥቷል፡፡ የዛሬ አምስትና ስድስት ዓመት ገደማ ሰዎች ስለኑሮውድነት ሲጽፍ ብዙዎቻችን እያነበብን ፈገግ ከማለት በቀር ብዙ ልባችን አልተነካም ነበር፡፡ ምናልባትምበጣም አልፎ አልፎ ከምናነባቸው መጣጥፎች ይልቅ መንግስት ስለ ልማት የሚነፋው ጥሩንባ አደናቁሮንይሆናል፡፡ አሁን አሁን የመንግሥት መዝገበ ቃላት “ልማት” የሚለው ትርጓሜ ግራ እያጋባን መጥቶ ጭራሽወደ ብስጭት የተመነዘረብን ብዙ ነን ብዬ አስባለሁ፡፡ መንግስት ልማት የሚለው ከእኛ አፍ “ቫት” እያለየሚነጥቃትን ገንዘብ ሰብስቦ ለሌቦች ካጠገበ በኋላ፣ በፍርፋሪዋ የሚሠራትን መንገድና ጤና ጣቢያ ወይምትምህርት ቤት ነው፡፡ ሌላው ቀርቶ “ኮንደሚኒየምእየተባሉ የተሠሩት ቤቶች አካባቢ ያለውን ግድየለሽነትተመልከቱ፡፡
 የውሃ መፍሰሻ ቦዮቹ ገና ተሠርተው ሳያልቁ ይፈርሣሉ። ሕንፃው ውስጥ ያሉትን የግብርይውጣ ሥራዎች ተውአቸው፡፡ ለመሆኑ ልማትና ዕድገት ምንድነውወረቀት ላይ የሃሰት ሪፖርቶችን ከምሮመቀለድ ነው። ቀልድና ውሸትስ እስከ የት ያዘልቀናልከወር ወደ ወር ሰዎች በልተው የማደር አቅማቸውንእያጡ፣ ልጆቻቸውን ማስተማር ተራራ መቧጠጥ እየሆነባቸው ሲመጣ — እንዴት ስለ ዕድገት ይወራል?ካድሬዎች ስለልማትና እድገት ብዙ ቢለፈልፉም ከሕዝቡ የበለጠ ጓዳውን የሚያውቅ ማንም ሊኖርአይችልም፡፡ አለ ቢባልም ከተራ ቀልድነት አያልፍም፡፡ እርግጥ ነው፤ ባለፉት ሃያ ሁለት ዓመታት ጥቂትሰዎች በኑሯቸው አድገው ይሆናል፤ ለስላሳ መጠጣት የማይችሉ ዛሬ ቤታቸው ውስኪ ደርድረውየሚመርጡበት ዕድል ደርሷቸው ይሆናል፡፡ያ ግን ዕድገት አይደለም፡፡
የማሕበረሰብ ሳይንስ ምሁራን የዕድገትና ልማትን ዓላማዎች እንዲህ ያስቀምጡታል – የሕዝቡን የገቢ መጠን በፍጥነት ማሳደግ ለዜጐች የሥራ ዕድልን መፍጠርመሠረታዊ የሆኑ የማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ፍላጐቶችን ማርካት፤ ማህበራዊ ፍትህን ማስፈን ሥራንና የቁጠባ ባህልን በሕብረተሰቡ ማስረጽ መልካም አስተዳደርናአሣታፊ የሆነ የፖለቲካ ምህዳር መፍጠር ከላይ የተጠቀሱትና ሌሎችም ተጨማሪ ነጥቦች የአንዲት ሀገርንና ሕዝብን ዕድገት መንገድ የሚያሳዩ ናቸው፡፡ ይሁን እንጂአሁን ያለው የአገሪቱ ተጨባጭ ሁኔታ ከዚህ በተቃራኒ መቆሙ ግልፅ ነው፡፡ ቁጠባውንም በውድም ሆነ በግድ በየሰበቡ ለማስለመድ የሚደረገው ጥረት  አይተናል፡፡የፖለቲካው አሣታፊነት ጉዳይ የሕፃን ልጅ ዕቃ ዕቃን የመሰለ ቀልድ ስለሆነ ጉዳዩ ለሰለቸው አንባቢ ይህን አንስቶ እንዲህና እንዲያ ማለት እንደ ደንቆሮ መቁጠርሊመስልብኝ ይችላል፡፡ ጠቃሚ ባህሎችን ማሳደግ በሚለውም መሥመር እያንዳንዱ ብሔር ብሔረሰብና ሕዝብ  ሥነ ጽሑፉንና ባህሉን ማሳደጉን እኔ በግሌእደግፈዋለሁ፡፡ ልክ ነው ብዬም አምናለሁ፡፡ አንዱ በባህሉ እየኮራ፣ ሌላው እያፈረ የሚደበቅባት ሀገር አሁንም እኩልነት የጐደላት ስለሆነች ያንን ሕልም ማለምጠባብነት ነው የሚል እምነት አለኝ፡፡ ሰዎች በወጣትነት መንፈስ በስሜታዊነት ያደረጉትን ነገር ምራቅ ሲውጡ እንኳን ለማስተካከል ያለመቅናታቸው የሚገርምነው፡፡
ሰው በገዛ ሀገሩ ባዕድ እየሆነና እየተገፋ መኖሩ የሚያመጣው ልማት ፈፅሞ ግልጽ አይደለም፡፡ ለመሆኑ መንግስት ማለትስ የሰዎች ስብስብ አይደለም እንዴእንዴትይህንን ነገር ማሰብ ያቅታቸዋልባለሥልጣን ሲኮን ተከትሎ የሚመጣው አጃቢ ወታደር፣ ያበጠ ወንበር የነገን ጉዳይ ያዘናጋልና መሪዎችም ሊያስቡበት የሚገባይመስለኛል። አብዛኛው ሕዝባችን ከእጅ ወደ አፍ እንኳን ኑሮ እያቃተው ከመጣ፤ የመኖር ዕድሉ እየጠበበ ከሄደ ሊፈጠር የሚችለው ነገር ምንድነው ብሎም ማሰብደግ ይመስለኛል፡፡ ህውሃት አማካሪዎች ምናልባት እውነት የማይናገሩ አሸርጋጆች እንደሆኑ የሚካድ አይደለም ሕዝቡ እየተራበ “ጠግቧል እየተማረረደስተኛ ነው” እያሉ ከሆነ ፍፃሜው አያምርም። በርግጥ  ሥልጣን  ላይ ያሉ አባገነኖች እኛ ብቻ ነን ሰው የሚሉትን አባዜ ቢተው መልካም ነው።ህዝብ ምንምአናመጣም የሚለውን ፈሊጥ መልካም አይደለም ሥልጣን ያላቸው ናቸው ለችግሩ መቋጫ መፍትሄ ሊያበጁለት የሚገባቸው በኋላ በሰፈሩት መሰፈር አይቀርምና፡፡
ቶማስ ጀፈርሰን፤ ሁሉም ሰው የየራሱ ዘመን አለው፣ በሕይወት የሌለ ሰው በሕያው ሰው ዘመን ሊወስን አይችልም እንደሚል፣ አሁን ያለውን ኑሮና ሕይወትየማያዩት  መሪ ራዕይ ሊያዘልቀን ይችላል ብሎ ማመን ያስቸግራል፡፡ ባለስልጣን ተብዬዎች ግን በጤፍ ዋጋ፣ በስኳርና በትራንስፖርት ጉዳይ ያለውን ጣጣ ዛሬቢያዩ፣ ራሳቸው ደንግጠው ጭንቅላታቸውን ይይዙ ነበር ዳሩ እነሱ ማን ሆኑና?፡፡ በዓመት ውስጥ ለአንድ የሆቴል ተመጋቢ ቢያንስ ሦስቴና አራቴ ዋጋይጨምርበታል፡፡ ታዲያ ሆዱ ባልጠገበ ሲቪል ሠራተኛ ተሠርቶ፣ ሀገርን ማሳደግ ይቻላል እንዴህውሃቶች  የውሸት አዲስ ሕልም ያልሙ እንጂ — የውሸትአዲስ ራዕይ ያምጡ! ተግባራቸው ግን ዜሮ ነው። የስነ አመራር ምሁሩ ጆን  ማክስዌል እንደፃፉት፤ በየዓመቱ ዶሮዎቹን የክረምት ጐርፍ የሚወስድበት ዶሮአርቢ፣ ሁልጊዜ በዶሮ ላይ የሙጢኝ ማለት የለበትም፤ ይልቅስ ጐርፉ ላይ ዋኝቶ አልፎ ሀብት የሚሆን ዳክዬ የማርባት ጥበብና ዘዴ ሊኖረው ይገባል። መቼምመንግስት ተብዬው ሁልጊዜ በሕይወት በሌሉት ላይ መንጠልጠል ያለበት አይመስለኝም፤ ፕሬዚዳንት ሊንደን ጆንሰን እንዳሉት፤ ድሀና ሀብታም በጠብደልግድግዳ ሲለይ ጥሩ አይደለም። ይልቅስ ግድግዳው የመስተዋት ነውና በኋላ የሚያመጣው መዘዝ መጥፎ ነው፡፡ ከፊሉ በሌብነት እየበለፀገ፣ ሌላው በጨዋነትእየተራበ – ለዘላለም – አይኖርምና መጠንቀቅ ያስፈልጋል፡፡ ዶክተር መረራ ጉዲና እንደሚሉት፤ የራበው ሕዝብ – መሪውን ለመብላት እንደሚነሳ – ካሁኑ ማሰብየግድ ይላል፡፡ ታዲያ – የኛም ምርጫ ይኸው ነው።
ከሃዊ ኦላኒ

No comments:

Post a Comment