Sunday, December 21, 2014

እስማኤል አሊ ስሮ ለረዥም ጊዜ በክልል ፕረዝድንትነት የቆዩ ብቸኛ የኢህአዴግ አገልጋይ የሆኑበት ምክንያት ምንድነው ?

አኩ ኢብን ከአፋር
የቀድሞው የትግራይ ክልል ፕረዝደንት የነበሩት አቶ ገብሩ አስራት በ 2006 ዓ.ም በጻፉት ሉዓላዊነትና ዲሞክራሲ በኢትዮጲያ በተሰኘው መጽሀፍ ላይ ሰለ እስማእል ዓሊ ሲሮ ሲገልፁ እንዲህ ይላሉ….
(አፋር ክልልን ፍልሥሥ ብሎ የሚመራው ኢስማኤል አሊስሮ ይህ ነው)
(አፋር ክልልን ፍልሥሥ ብሎ የሚመራው ኢስማኤል አሊስሮ ይህ ነው)

በ1993 በኢህአዴግ ውስጥ ቀውስ በተፈጠረበት ወቅት የአፋር ብሔራዊ ዴሞራሲ ፓርቲ ሊቀመንበርና የክልሉ ፕረዝድነት የነበሩ ዓሊ ሲሮ አፈንጋጮችን ደግፎ ለተወሰኑ ቀናት የመለስን ቡዱን ተቃውሞ ነበር።

መለስ ድል አድረግያለሁ የባለንጣዎች ጃኬትም አውልቀያለሁ ካለ በኃላም ዓሊ ሲሮ ደስተኛ አልነበረም።

ሰለሆነም ከክፊፊሉ በኃላ ዓሊ ሲሮ መገምገም ነበረበት ከመገምገምም አልፎ ላሳየው ተቃውሞ መቆንጠጥ ነበረበትና በወቅቱ የፈዴራል ሚኒስትር የነበረው አባይ ፀሐዬና የክልሎች ዴስክ ኃላፊ የነበረው ዘርኣይ አሰገዶም የአፋር ዴሞክራሲ ፓርቲን አመራር ዓሊ ሰሮን ጠርተው ቁም ስቅሉን አሳይተውት ነበር።

ዓሊ ሲሮም ከአፈንጋጮች ጎን ተሰልፈው እንደነበረ እንዲያምን ብዙ አስለፍልፈውታል።
ሁለት አወያዮች ይህን ካደረጉ በኃላ ዓሊ ሲሮ ከስልጣን እንዲወርድ ለመለስ ሀሳብ ቢያቀርቡም አለቃ ፀጋይ በአቆራጭ መለስን ተማጽኖ ከመባረር አድኖታል።
የአለቃ ፀጋይ ዓሊ ሲሮ በስልጣን እንድቆይ መማጸን ከማናውቀው ማላእክ የሚናውቀው ሰይጧን (ሸይጣን) ይሻለናል ከሚል እንደነበረ ምንጮቻችን ነግሮናል።
እውነትም ሁኔታዎች በተለዋወጡበት ሁኔታ እንኳን አብዴፓና መሪው ሌላም አፋር ለውጥ ለማምጣት የሚቸገር ነበረና ዓሊ ሲሮ ባለበት እንድቆይ ተወስኖ ኢህአዴግን ከአስራ ሁለት አመታት በላይ ሊያገለግል ችሏል ይላል መጽሀፉ።
እዚህ ለይ እኔም የራሴ ትንሽ ልጨምረበትና በእርግጥ የእስማእል ዓሊ ሲሮ የአገልግሎት ላይ መቆየት ምክንያት አለቃ ፀጋይ ነው።
ይህም በ1993 ባደረገለት ተማጽኖ ብቻ ሳይሆን መለስ ከሞተ በኃላም ያልተቆረጠ ድጋፍ ከአለቃ ፀጋይ አላቸው።
ይሁን እንጂ መለስ ከሞተ በኃላ አለቃ ፀጋይ እራሱ ይህ የሚባል ስልጣን ባይኖረውም አቆያህለሁ እያለ ከአቶ እስማእል ብዙ ሚሊዮን ብሮች እንደሚያገኝ ይነገራል።
አለቃ ፀጋይ የትግራይ ክልል ፕረዝደንት በነበሩበት ጊዜ ዓሊ ሲሮ መቀለ ሳይዘይሩ (ሳይሳለሙ) ሳምንት አያሳልፉም ነበር።
አሁን ግን ሁለቱም መሀይሞች የሚገናኙት አዲስ አባባ ወይም ሰመራ ቢሆንም አቶ ሲሮ ስልጣን ላይ ለመቆየት ከአለቃ ፀጋይ ሌላ አዲስ ሽማግሌ የቀጠሩ የመስላሉ።
እርሱም የጀቡት ፕረዝደንት የሆኑት እስማእል ኡማር ገሌ ስሆኑ ካለፉት ሦስት ሳምንታት በፊት አቶ እስማእል አሊ ስሮ በማያገባቸው የሁለት አገር ድምበር ከተሞች የፀጥታ ኃላፊዎች በተጠሩበት ሰብሰባ ምክንያት በማድረግ ወደ ጀቡቲ ሄደው ነበር።
በዛን ጊዜ ሁለት እሰማእሎች ተገናኝተው የበሩ መሆኑን ኦና ኢህአዴግ ከእስማእል ኡመር ገሌ የሚፈለገው ብዙ ነገሮች ሰላለው ኢህአዴግን እንዲማጸኑለት እስማእል ዓሊ ሲሮ ጠይቀው ነበር።
ያነ የኢትዮጲያ ኢሳ ጎሳ ተወላጅ የሆኑት ገሌ እስማኤል ዓሊ ሲሮ ለኢሳዎች ልዩ ቀበለዎች እንዲሰጡ ወይም የኢሳ ጎሳ በአፋር ክልል በሰላም እንዲኖሩ እንዲያመቻቹ ጠይቀው አቶ ሲሮ የሁለቱም ጥያቀዎች መልስ ያለው በኢህአዴግ እጅ ውስጥ እንደሆነና እርሰዎ እንድጠይቁ በማለት በሚስጥር ከተሰማሙ በኃላ ወደ ሰመራ ተመልሷል።
ከሳምንት በኃላ የጀቡቲ ፕረዝደንት በአሶሳ በተከበረው የበሔር በሔረሰቦች ቀን ላይ ተግኝተው ወደ አገራቸው ተመልሰዋል።
ከዛም ከሳምንት በኃላ የፈደራል ሚኒረስትር በአፋር ክልል በአዋሽ ከተማ በሁለት ክልሎች ጣልቃ ገብተው የአፋር መሬት ለኢሳ አሳልፈው ስጥተዋል።

No comments:

Post a Comment