Friday, March 20, 2015

የሚሊዮኖች ድምጽ – መደመጥ ያለበት ክርክር በመድበለ ፓርቲ ዙሪያ – ክፍል 1 እና ክፍል 2

“ኢሕአዴግ አርጅቷል። የሐሳብ ድርቀት ደርሶበታል” ኢንጂነር ይልቃል
“ለኢትይጵጵያ ሕዝብ ጥልቅ ፍቅር አለን። ፣ ትልቅ አክብሮትት አለን”
ኢንጂነር ይልቃል
“ኢሕአዴግ የአሁኑ ትዉል የሚመጥን አይደለም”
አቶ ዮናታን ተስፋዬ
“በኢሕአዴግ ክራይቴሪያ ማግኘት ይሻላል፣ በአካዳሚክ ከማግኘት እየተባለ ነው “
“የካቢኔ የካድሬ ወንድምና እህቶች የጠለበ ሥራ ሲያገኙ፣ ሌሎች ድንጋይ ነው የሚፈልጡት!
ዶር መራራ ጉዲና
ዶር መራራ መልእክት ለኢትዮጵይ ሕዝብ “የኢሕአደግ መሪዎች ሰበካ በቀን ሶስት ጊዜ እናበላሃለን እያሉ፣ ግን በቀን ሶስት ጊዜ እንደምታበላ አንተም ታውቃዋለህ።ኢሕአዴግ አንተን እያሳለፍኩልህ ነው እያለ ማንን እያበለጸገ እንዳለ አንተም ታውቀዋልህ። በዩኒቨርሲቲ ደረጃ ጥረህ ግረህ ያስተማርካቸው ወጣቶች ዛሬ ምን እንደሚሰሩ አንተም ታውቀዋለህ። የካድሬዎችን የካቢኔዎች ልጆች ዛሬ እንዴት እንዳለፈላቸው አንተም ታወቀዋለህ። ኢሕአዴግ መንግስት ነጋዴም በሆነበት ስርዓት በየአመቱ ያለ አግባብ ግብር እየተጫነብህ፣ የማዳበሪይ እዳ እየተጫነበህ፣ እንደሚገኝ አንተም ታወቀዋለህ። ……… ታሪክ ሥራ”

ኢንጂነር ይልቃል ከዳያስፖራ ጋር አብራችሁ ትሰራላችሁ ለሚለው ክስ ሲመልሱ በዋናነት በኢትዮጵያ የፈረንጅ ጥገኛ የሆነ መንግስት እብደ ኢሕአዴግ እንደሌለ በመግለጽ ነበር። “ይሄን ያህል ብድርና እርዳት አገኝን እያሉ እንደ ትልቅ ነገር ያወሩ የለም ወይ ? “ ያሉት ኢንጂነር ይልቃል ኢሕአዴግ ከአዉሮፓ ሕብረትና ከመሳሰሉት የሚገኘዉን እርዳታ ባጀት ዉስጥ እስከማስገባት ድረስ የደረሰ እንደሆነም አስረድተዋል።
በውጭ የሚኖሩ ብዙ የኢትዮጵያ ልጆችን እዉቀት፣ ችሎታ መጠቀም ብስለት ነው ያሉት ኢንጂነሩ በዉጭ ያሉትን ኢትዮጱዊያን “እናከብራለን፣ እንወዳቸዋለን ፡አብረናቸው እንሰራለን። ኢሕአዴግ ጥላሸት ስለቀባና ሌላ ስም ስለለጠፈባቸው ብቻ ልዩ ስም መስጠት አያስፈልግም። የአገራችን ልጆች ናቸው” ሲሉ ለነ ሬድዋን ሁሴ ክስ ድብን ያለ መልስ ሰጥተዋል።
ከኢንጂነር ይልቃል ጋር በክርክሩ ይተሳትፉት አቶ ዪናታን በበኩላቸው “ፍረጃና ውንጀላ የኢሕአዴግ ባህሪው ነው” በማለት ነበር መልሳቸዉን የጀመሩት። ኢሕአዴግ ዘመኑን የዋጀ ለዘመኑ የማይመጠን እንደሆነ የገለጺት አቶ ዮናትን ፣ አገራችን አቅራቢያ ያሉ ኬንያ፣ ታዛኒያን እንኳ የሚያክል ስርዓት የኢትዮጵያ እንደሌላት ተናግረዋል።

ክፍል 1 
መድረክ እና ሰማያዊ በተሰጣቸው የመጀመሪያ ስድስት ስድስት ደቂቃዎች የተናገሩትን ይዳምጡ። ዶር መራራ እና ኢንጂነር ይልቃል የተናገሩት ለማዳመጥ 29.50 ደቂቃ ወደፊት መሄድ ይችላሉ።
ክፍል 2
ዶር መራራ፣ ኢንጂነር ይልቃል እና አቶ ዮናታን የተናገሩትን ያድምጡ። ( ወደ 9.23 ወደፊት በመሄድ እስከ 26.00 ከዚያም ለ50.00 እክሰ 58 ያገኙታል።

No comments:

Post a Comment