Saturday, March 14, 2015

የምርጫ አስፈፃሚው የደኢህዴን አባል መሆናቸው ተረጋገጠ

ነገረ ኢትዮጵያ
• ነዋሪዎች ከሁለት በላይ የምርጫ ካርድ እንዲያወጡ እየተደረገ ነው
በደቡብ ክልል በምርጫ አስፈፃሚነት የተመደቡ ግለሰቦች የዴኢህዴን አባላት እንደሆኑ ምንጮች ለነገረ ኢትዮጵያ በላኳቸው ሰነዶች አረጋገጡ፡፡ ለአብነት ያህልም አረካ ከተማ የምርጫ ክልል በአስፈጻሚነት እየሰሩ ከሚገኙትን አቶ ግዛው ቴማ የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ አባል መሆናቸው ምንጮች ለነገረ ኢትዮጵያ የተላኩት ሰነዶች ያሳያሉ፡፡ አቶ ግዛው ለፓርቲያቸው የደቡብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ዴሞክራሲያዊ ንቅናቄ (ደኢህዴን) በነሃሴ ወር 2006 12 ብር ከ87 ሳንቲም፣ እንዲሁም በ2007 መስከረምና ጥቅምት የሁለት ወር 25 ብር ከ74 ሳንቲም መዋጮ የከፈሉበት ደረሰኝ የደኢህዴን አባልነታቸውን ያረጋግጣል፡፡

በሌላ በኩል በደቡብ ክልል የተለያዩ አካባቢዎች ነዋሪዎች በግዳጅ ከሁለት በላይ የምርጫ ካርድ እንዲያወጡ እየተገደዱ መሆኑን ለነገረ ኢትዮጵያ ገልጸዋል፡፡ በወላይታ ዞን አረካ ከተማ ነዋሪ የሆኑት አቶ ሕዝቁኤስ ቱጨ ቱፋ ለባለቤታቸውን ለወይዘሮ መሰለች ኬንዳን ጭምር ካርድ እንዲያወጡ የተደረገ ሲሆን፣ በዚሁ ቀን ህዝቡ ካርድ እንዲያወጣ የሚቀሰቅሱ ሌሎች ካድሬዎች ወይዘሮ መሰለች ኬንዳም የባለቤታቸው የአቶ ሕዝቁኤስ ቱጨ ጨምረው ሁለት ካርዶችን እንዲወስዱ ተደርገዋል፡፡ ሌሎች የአካባቢው ነዋሪዎችም በተለያዩ ካድሬዎች አማካኝነት በርከት ያሉ የምርጫ ካርዶችን እንዲወስዱ መደረጉን የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች ገልጸዋል፡፡
በቀን 07/05/ 2007 ዓ.ም ወ/ሮ መሰለች በ173ኛ እና 147ኛ ቁጥር፣ እንዲሁም ባለቤታቸው አቶ ህዝቁኤል ቱጫ ቱፋ በተመሳሳይ ቀን 172ኛ እና 151ኛ ተራ ቁጥር ላይ ተመዝግበው ሁለት ሁለት የምርጫ ካርዶችን እንዲወስዱ ተደርገዋል፡፡ በተጨማሪም ነዋሪዎች መምረጥ ለማይችሉት የቤተሰብ አባላት ጭምር ‹‹ካርድ ውሰዱላቸው›› እየተባሉ በአንድ ሰው በርከት ያለ ካርድ መውጣቱን የነገረ ኢትዮጵያ ምንጮች ገልጸዋል፡፡
11045382_678850302240631_7727559560221046908_n11009130_678850215573973_6496558354382052425_o
- See more at: http://www.zehabesha.com/amharic/archives/39717#sthash.z8p6rVCE.dpuf

No comments:

Post a Comment