Wednesday, April 22, 2015

ኢትዮጵያዊ ክርስቲያን ወንድሞቼን አሳልፌ አልሰጥም በሚል በአይሲኤል ሕይወቱን ያጣው ጀማል ራህማን

በሙስሊም ወገኖቻችን ኮራን
አበበ ገላው እንደጻፈው:-
ISIL
አረመኔዎቹ ወያኔዎች ኢትዮጵያዊያን ሙስሊሞችን ከISIS ጋር የተሰለፉ ለማስመሰል አደገኛ ፕሮፓጋንዳ በመርጨት ላይ ናቸው። ይሁንና እውነታው ሙስሊም ወገኖቻችን ክርስቲያን ወገኖቻቸውን ከእርድና ጥይት ለመታደግ መስዋእት እየሆኑ መሆኑን ተረጋግጧል። ክርስትያን ወንድሞቼን አሳልፌ ለሞት አልስጥም ብሎ አብሮ ከተሰውት ኢትዮጵያዊያን መሃል ወንድማችን ጀማል ራህማን ይገኝበታል። ክርስቲያን ወንድሞቹን ለማትረፍ ከአረመኔዎች ጋር ሲሟገት እራሱ ተሰዋ። በታሪክ ለዘላለም የሚዘከር ታላቅና ቅዱስ መሰዋእትነት!! ነፍስህ ለዘላለም በገነት ስለምትኖር ይማርክ ልንህ ልንልህ አይቻለንም።

እኛ ኢትዮጵያዊያን እንዲህ ነን! ምንም ገዢዎች ቢከፋፍሉን አብረን እንኖራለን፣ አብረን እንቆማለን፣ አብረን እንሰዋለን። በዚህ የመከራ ግዜ ሁላችንም በዘር በሃይማኖት ሳንከፋፈል አንድነታችንን አጠንክረን ከውጭም ከውስጥም እንታገል። የክርስቲያኑም የሙስሊሙም አምላክ ይርዳን!!

No comments:

Post a Comment