Monday, April 27, 2015

የት ሄደን እናልቅስ ?

yilikal
የት ሄደን እናልቅስ
የት ሆነን እንተንፍሰ
የወንድሞቼን ደም የት ሄጄ ልመልስ
ሀገር ነበር እኮ ሁሉንም ማስረሻ
ሀዘን ይሁን ስጋት ከሁሉ መሸሻ
ወንድሜ ሲቃጠል በሳውዝ አፍሪካ ላይ
ስጋዬ ቢታረድ በሊብያ ምድር ላይ
እህቴንም ባጣት በዛ በየመን ላይ
ሀዘኔ ቢበዛ ውስጤ ቢቆስልብኝ
መንግስት እንደሌለው ማንም ሲገልብኝ
ምንም እንኳን ባጣ ሄዶ ሚያተርፍልኝ
ደርሶ ሚያስጥልልኝ
እኔው ተነሳሁኝ እህህ ልለው
ሀዘኔን ቁጭቴን ሁሉን ላሳውቀው
አቅሜም እንኩዋን ባልችል ባልሆን ከጎናቸው
ሀዘኔን በሀገሬ ፍቅሬን ላሳያቸው
ሆ ብዬ ተነሳው በኢትዮጵያ ምድር ላይ

በጀግኖቻችን ደም በፀናች ሐገር ላይ
በእንባዬ እየታተብኩ በህዝቦቼ ስቃይ ጉዞዬን ጀመርኩኝ ወደ አደባባይ
መንግስት እንኮን ራርቶ ወደ ህዝቡ እንዲታይ
ድንገት ሳላስበዉ ምኑንም ሳላውቀው
በእንባዬ እየታተብኩ ጉዞዬን ስጎዘው
መጣብኝ ወገኔ እኔኑ ሊመታ
በሐዘን ላይ ሐዘን ወደ ኔ ሊያመታ
እጅን አነሳኝ እግሩን ዘረጋብኝ
በጣም በጭካኔ ዱላ አሳረፈብኝ
ላዝን የወጣሁት ለ ገዛ ደማችን
አማራ ይሁን ትግሬ አንድ ነው ሕዝባችን
እስላም ክርስቲያኑ አንድ ነው ኑሮአችን
ኢትዮጵያዊነት ነው የኛ መለያችን
ምነው ጨከንክ ወገን በገዛ ደምክ ላይ
እናትክ በእንባ እንዲ ስትሰቀይ
ዋይ! ዋይ! ስትል እምዬ ልጇ ተበልቶባት
አንተ ግን መተካት በእርግጫ ገፋካት
የ 9 ወር ቤትን እማን እረሳካት
ቆም ብዬ ሳየው ማዝነው ለ ራሴ ነው
ግንምን ዋጋ አለው ሚያዝንበት ለሌለው ።

ገጣሚ ፍፁም
ከ ደቡብ አፍሪካ

No comments:

Post a Comment