Wednesday, April 22, 2015

አይሲስን ለመቃውም አደባባይ የወጡት የሰማያዊ ፓርቲ ዕጩዎች፣ አመራሮችና አባላት ታሰሩ

addia ababa
(ነገረ ኢትዮጵያ) ዛሬ መንግስት በጠራው የተቃውሞ ሰልፍ በርካታ የሰማያዊ ፓርቲ አባላት፣ አመራሮችና እጩዎች ታስረዋል፡፡ ሰልፉን ለመቀላቀል በጠዋቱ ወደ መስቀል አደባባይ በማቅናት ላይ የነበረችው ወይንሸት ሞላ ሰልፉ ላይ ሳትደርስ የታሰረች ሲሆን አሁን የት እንዳለች አልታወቀም፡፡

ዕጩ ተወዳዳሪ የሆነው ጠና ይታየውን ጨምሮ በርከት ያሉ የሰማያዊ ፓርቲ አባላትና አመራሮች የታሰሩ ሲሆን ከእነዚህም መካከል
ዳንኤል ተስፋዬ፣ ምዕራፍ ይመር፣ ኤርሚያስ ስዩም እና ቴዎድሮስ አስፋው ይገኙበታል፡፡

No comments:

Post a Comment