Wednesday, February 27, 2013

ኢቴቪ የታገደውን ፊልም ማስተላለፉ የሚታወስ ሲሆን በአሁን ሰዓትም ጠ/ሚ/ ኃ/ማርያምን ጨምሮ ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ሊከሰሱ ነው ኢቴቪና ፌዴራል ፖሊስም ይከሰሳሉ


 “ጃሃዳዊ ሀራካትበሚል መጠሪያ በኢትዮጵያ ራዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት የተዘጋጀው ዘጋቢ ፊልም ላይ የፌዴራል ከፍተኛ ፍርድ ቤት አራተኛ ወንጀል ችሎት የዕግድ ትዕዛዝ ቢያስተላልፍም የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ግን በቅርብ ግዜ  ዘጋቢ ፊልሙን አስተላልፏል። 
ዘጋቢ ፊልሙ የታሰሩ የሙስሊም ወገኖችን ሰብዕና ሊያጎድፍ ይችላል በሚል ሰኞ ጥር 27 ቀን 2005 በተፋጠነ ስነ-ስርዓት ክስ መመስረቱን የገለፁት ጠበቃ ተማም አባቡልጉ ናቸው። 

እንደጠበቃ ተማም ገለፃ፤ ዶክመንተሪ ፊልሙ በሽብርተኝነት ተጠርጥረው የተያዙ ሰዎች ንፁህ ሆነው የመገኘት መብታቸውን የሚጎዳ ነው የፍርድ ቤቱን ነፃና ገለልተኛነት የሚጎዳ፣ ፍርድቤቱንም የመድፈር፣ ተጠርጣሪዎቹ ነፃ ቢወጡ እንኳን ሊካስ እና ሊተካ የማይችል፣ የማይመለስ ጉዳት ያደርስባቸዋል። ተጠርጣሪዎቹ ተከላከሉ ቢባል እንኳ የመከላከያ ምስክሮችን አቅርበው እንዳያሰሙ ተፅዕኖ ያሳድራል፤ ፊልሙ የተዘጋጀው ሚዛናዊነቱን ሳይጠብቅ፣ ተጠርጣሪዎቹ አስተያየታቸውን እንዲሰጡ ሳይጠየቅና ሳይፈቅዱ መሆኑን ጠበቃ ተማም ተናግረዋል። 
ይሁን እንጂ /ቤቱ የእገዳውን ትዕዛዝ ካስተላለፉ በኋላ የከፍተኛ /ቤት ፕሬዝዳንት ውሳኔውን የምናስተካክለው ነገር አለ በሚል የፍ/ቤቱን ውሳኔ በመውሰዳቸው በፍ/ቤቱ ትዕዛዝ መፈፀም ላይ ጥርጣሬ እንዳላቸው ፊልሙ ከመተላለፉ በፊት ጠበቃው ስጋታቸውን ገልፀው ነበር 
በሕግ ላይ ትልቅ ክህደት እየተፈፀመነው ያሉት ጠበቃ ተማም የከፍተኛው /ቤት ውሳኔ ለኢትዮጵያ ሬድዮና ቴሌቪዥን ድርጅት ደርሶ፤ የድርጅቱ ሰራተኞች ፈርመው መቀበላቸውን አረጋግጠናል ብለዋል። ነገር ግን የከፍተኛ /ቤት ፕሬዝዳንቱ የእግድ ትዕዛዙ ላይ የጎደለ ነገር አለ በሚል በእጃቸው ይገኛል ሲሉ ቅሬታቸውን ገልፀዋል። 
ሆኖም ጣቢያው በትናንት ምሽት ፕሮግራሙ ላይ ፕሮግራሙን አስተላልፎታል። ከፊልሙ መታገድ ጋር በተያያዘ የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቭዥን ድርጅት የስራ ኃላፊዎችን አግኝተን ለማነጋገር ያደረግነው ጥረት አልተሳካም።


በኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት በቅርቡ ከተላለፈው ‘‘ጅሃዳዊ ሃራካት’’ ዘጋቢ ፊልም ጋር በተያያዘ ጠቅላይ ሚኒስትር /ማርያም ደሳለኝን ጨምሮ ከፍተኛ የሀገሪቱ የመንግስት ባለስልጣናት ላይ የወንጀልና የፍትሃብሔር ክስ ሊመሰረት ነው። ከመንግስት ከፍተኛ ባለስልጣናት ባሻገር በኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት (ኢሬቴድ) እና በፌዴራል ፖሊስ ተመሳሳይ ክስ ይመሰረትባቸዋል።
ከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናቱ እና የተጠቀሱት ተቋማት ላይ ክስ የሚመሰረተው ሰሞኑን ‘‘ጃሃዳዊ ሃራካት’’ በሚል በኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ደርጅት የቀረበው ዘጋቢ ፊልም በሽብርተኝነት ተጠርጥረው በሕግ ጥላ ስር ያሉትን ተጠርጣሪዎች መብት ሲጣስ መከላከል ባለመቻላቸው፣ ስልጣናቸውን ያለአግባብ በመጠቀማቸው፣ በሕዝብ ሐብት ያለአግባብ በመገልገላቸው፣ የተሰጣቸውን የሕዝብ አደራ ባለመወጣታቸውና በሃይማኖት ጣልቃ በመግባታቸው የወንጀልና የፍትሐብሔር ክስ ይመሰረትባቸዋል። ክሱን የሚመሰርቱት በአሁኑ ወቅት በሽብርተኝነት ተጠርጥረው ጉዳያቸው በሕግ እየታየ ባሉት ተጠርጣሪዎች ጠበቆች አማካኝነት ሲሆን ክሱም በሁለት ደረጃ ተከፍሎ እንደሚቀርብ ለማወቅ ተችሏል።
ክሱን እያዘጋጁ ከሚገኙት ጠበቆች አንዱ የሆኑት ጠበቃ ተማም አባቡልጉ ክሱን በማስመልከት በተለይ ለሰንደቅ ጋዜጣ እንደገለፁት ጠቅላይ ሚኒስትሩን ጨምሮ በመንግስት ባለስልጣናት ላይ የሚመሰረተው ክስ ጠቅላይ /ቤት ይቀርባል ብለዋል። በኢቲቪ ላይ የሚመሰረተው የፕሬስ ክስ ቀጥታ በከፍተኛው ፍርድ ቤት የሚቀርብ ሲሆን ክሱም ከሞራል ጉዳት ጋር እንደሚያያዝ ጠበቃው አስታውቀዋል።
‘‘መጀመሪያ ክርክራችን ዘጋቢ ፊልሙ እንዳይተላለፍ ነበር። ከተላለፈ በኋላ ግን ይግባኝ ማለት ሳይጠበቅብን ይሄንን ጉዳት ባደረሱ አካላት ማለትም ፊልሙን በሰሩት፣ ፖሊስና የደህንነት ኃይሎች ጨማምረን ክሱ እንመሰርታለን’’ ያሉት ጠበቃ ተማም በፕሬስ ህጉ መሰረትም ዘጋቢ ፊልሙ በተላለፈ በሦስት ወራት ውስጥ ክስ መመስረት እንደሚያስችልም አያይዘው ገልፀዋል።
በኢቲቪ በተላለፈው ዘጋቢ ፊልም ላይ በሚመሰረተው ክስ እስከ 100ሺህ ብር የሞራል ካሳ እንደሚጠየቅ በከፍተኛ የመንግስት ባለስልጣናት ክስ ደግሞ በሌላ መዝገብ በፌዴራል ጠቅላይ /ቤት በሚመሰረተው ክስ ለደንበኞቻችን የሞራል ካሳ እንዲካሱ፣ ደንበኞቻችን ይቅርታ እንዲጠየቁ፣ በተመሳሳይ የአየር ጊዜ ተሰጥቷቸው ደንበኞቻችን የራሳቸውን ኀሳብ እንዲሰጡ፣ በሃይማኖት ውስጥ በተደረገ ጣልቃ ገብነት ለደረሰው ጉዳት ኃላፊነት እንዲወስዱ የሚያደርግ ክስ ነው ብለዋል።
‘‘ክሱ ጠቅላይ ሚኒስትሩን የማያካትትበት ምክንያት የለም። የሀገሪቱ መሪ እሳቸው ናቸው። ፖሊስም እያደረገ ላለው ነገር ለምሳሌ ተጠርጣሪዎችን ቶርች በማድረግ ጭምር እንከሳለን። የሀገሪቱ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፕሬዝዳንት ዘጋቢ ፊልሙ ያግዱ፣ አያግዱ የሚለውን አጣርተን የሚመለከታቸውን አካላት ለይተን ክሱን ለመመስረት ተዘጋጅተናል። ክሱን ለማዘጋጀት አስፈላጊ መረጃዎችን እየሰበሰብን ነው። በቅርቡም ክሱን እንመሰርታለን’’ ሲሉ ጠበቃ ተማም ጨምረው ገልፀዋል።
ደንበኞቻችን እራሳቸውን በማይከላከሉበት ሁኔታ ታስረው፣ መልስ እንዲሰጡ ባልተደረገበት ሁኔታ ስማቸው እንዲጠፋ መደረጉ አግባብ አለመሆኑን የጠቀሱት ጠበቃው ዘጋቢ ፊልሙ የደንበኞቻችንን መልካም ባህሪ የገደለ (Character assination) ነው ብለዋል።
መንግስት በሽብርተኝነትና ከህገ-መንግስቱ በተቃራኒ ሃይማኖታዊ መንግስት ለማቋቋም ሲያሴሩ አግኝቻቸዋለሁ፤ በሶማሊያ ከሚንቀሳቀሰውና ከአለም አቀፍ አሸባሪ ቡድን አልቃይዳ ጋር ከሚንቀሳቀሰው አል-ሻባብ ጋር ተመሳጥረው ሲሰሩ አግኝቻቸዋለሁ ባላቸው ተጠርጣሪዎች ላይ ዘጋቢ ፊልም ማቅረቡ ይታወሳል።
ፊልሙ ከመተላለፉ በፊት የኢትዮጵያ ሬዲዮና ቴሌቪዥን ድርጅት በፌዴራሉ ከፍተኛ /ቤት አራተኛ ወንጀል ችሎት የእግድ ትእዛዝ ቢያስተላልፍም ፊልሙ ለሕዝብ አይታ መቅረቡ አይዘነጋም፤ ፊልሙ ለተመልካቾች ከቀረበ በኋላም አነጋጋሪ ሁኔታ መፈጠሩም ይታወቃል።
ምንጭ ሰንደቅ ጋዜጣ በዘሪሁን ሙሉጌታ ሰንደቅ ጋዜጣ 
ኢትዮጵያ በክብር ለዘላለም ትኑር !!!

No comments:

Post a Comment