Tuesday, August 11, 2015

ትላንት ምሽት በአዲስ አበባ የ3 ወጣቶች አስክሬን ኩሬ ውስጥ ተገኘ…

0f5d7-3
በንፋስ ስልክ ላፍቶ ክፍለ ከተማ ልዩ ስሙ ላንድሮቨር ማዞሪያ፣ መሳይ ካባ በተባለ ቦታ ነው ወጣቶቹ ህይወታቸው አልፎ የተገኙት ተብሏል፡፡
በአካባቢው ለመንገድ ስራ ድንጋይ ለማውጣት የተቆፈረ ከ7 እስከ 9 ሜትር ርዝመት ያለው ጥልቅት መለስተኛ ሐይቅ ፈጥሯል፡፡
ሁለቱ 20 አንዱ ደግሞ 25 አመታቸው ነው የተባሉ 3 ወጣቶች የገቡበት ምክንያት ባይታወቅም የአዲስ አበባ እሳትና ድንገተኛ አደጋዎች መከላከልና መቆጣጠር ባለስልጣን ከአካባቢው ነዋሪ በደረሰው ጥቆማ ትላንት ምሽት 3 ሰዓት ላይ የወጣቶቹን አስክሬን አውጥቷል፡፡

ከወጣቶቹ አንዱ ልብሱን አወላልቆ የነበረ ሲሆን ሁለቱ ግን ልብሳቸውን እንዳደረጉ፣ ጫማቸውንም እንደተጫሙ መገኘታቸውን የባለስልጣኑ የህዝብ ግንኙነት ባለሙያ አቶ አዳነ አብርሃ ነግረውናል፡፡
ወጣቶቹ አስክሬናቸው ምሸት 3 ሰዓት እንዲወጣ ቢደረግም በጊዜ ሳይገቡ እንዳልቀረ ተገምቷል፡፡
የአሟሟታቸው ምክንያትም በፖሊስ እየተጣራ ነው ተብሏል፡፡
Source: Sheger Fm

No comments:

Post a Comment