Tuesday, August 4, 2015

ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ (ከቴዎድሮስ ሓይሌ)

ከቴዎድሮስ ሓይሌ
“…… ይህ ጦርነት ወደን ሳይሆን ተገደን የገባንበት በመሆኑ ገደልን እያልን የምንፎክርበት አይደለም ፤ በዚያም በኩል ያሉት የኛው ወንድሞች ናቸውና ፤ ምርጫችን ይህ መሆኑ ቢያሳዝንም መብታችንን ለማስከበር ያለው አማራጭ ይህ በመሆኑ ነው ……..’’
ይህን ከላይ የሰፈረውን መልካምና ትሁት አባባል ሰሞኑን የተናገሩት የግንቦት ሰባናትና የአርበኞች ግንባር ሊቀመንበር ዶ/ር ብርሃኑ ነጋ ወደ ወሳኙ ትግል በርሃ ከመውረዳቸው አስቀድሞ ነበር። ‘’ የዘመድ ቄስ እየፈታ ያለቅሳል’’ አበው እንዲሉ እኝህ የኢኮኖሚክስ ሊቅና የነጻነት ትግል መሪ ሳንወድ ተገደን ገባንበት ባሉት ትግል ፈቅደውም ሆነ ተገደው የወያኔ ወታድር ሆነው ለሚሰውት ኢትዮጽያውያን ያላችውን ሃዘንና ቁጭት የገለጹበት ቋንቋ በብዙዎች ዘንድ ክብርና አድናቆትን አትርፎላቸዋል።
Dr Berhanu Nega with Patriotic Ginbot 7 Freedom Fighters
Dr Berhanu Nega with Patriotic Ginbot 7 Freedom Fighters (ESAT PHOTO)
ጀግና ይልሃል እንዲህ ነው በትዕቢት ሳይሆን በትህትና ፤ በፉከራ ሳይሆን በትንተና ፤ በጥላቻ ሳይሆን በወገናዊነት ፤ ሳንጃ ወድሮ ጥይቱን ታጥቆ ለሚፋለመው ወገን ያለውን ፍቅርና ሃዘኔታ የሚገልጽ በጎና አስተዋይ መሪ በመሆን ዶ/ር ብርሃኑ ያሳይው አቀራረብ በታሪክ የሚጠቀስ ነው። ከዚህም በላይ እኝህ ታላቅ ምሁር ህዝባችንን ያስደመሙት ፤ በዚህ ከራሴ በላይ ላሳር በሚባልበት ፤ ራስ ወዳድነት መለያችን በሆነበት ፤ ስግብግብነትና ምንቸገረኝነት በተንሰራፋበት ዘመን ፤ ሃብታም ሲሆኑ እንደ ድሃ ፤ በነጻነት ቢኖሩም እንደ ተጨቋኝ ፤ በምቾት ቢኖሩም እንደ ጎስቛላ ፤ ፌሽታ ደስታ ሁካታና ዳንኪራ ባለበት መኖር እየቻሉ ፤ ረሃብና ጥም ፤ ሞትና ዋይታ እባብና ጊንጥ ወዳለበት ወደከፋው በርሃ ያስውረዳቸው ፤ ሕሊና የሚባለው የሰውነት እዳ ፤ ነጻነት የሚባል ቅዱስ መንፈስ ፤ ሃገር የምትባል መልካም ርስት ፤ ሕዝብ የሚባል ታላቅ ቤተሰብ ፤ የወደቀበትን የግፍ አገዛዝ ለማስወገድ ለውሳኙ ትግል ጠቅለው ወደ ትግሉ ግንባር በማቅናታችው ከፍተኛ እክብሮት ከመቸራቸውም በላይ ለትግሉ መነቃቃትን ፈጥረዋል።

ዶ/ር ብርሃኑ የሃገር ፍቅርና ህዝባዊነት ግድ ያለው ዜጋ በመሆኑ ያኔ ባፍላነት እድሜው የተማሪውን እንቅስቃሴ ተከትሎ ወደ በርሃ በመውረድ የከፈለው የዜግነት ግዴታ ይበቃል ሳይል ባለፉት 40 አመታት ውስጥ ያልተቋረጠ ተሳትፎና ትግል ያካሄደ ከራሱ በላይ ለሌሎች የሚያስብ መልካም ዜጋ በመሆኑ ይህው ዛሬም የምቾት ኑሮውን ትቶ ስለ ሃገርና ወገን ሲል ለመስዋእትነት ተሰልፋል ። ይህ ሰው የፖለቲካ ትግሉን እንደገና ከመቀላቀሉ በፊት ያኔ ገና ወያኔ ስልጣን እንደያዘች ከመሪዎቿ ጋር በነበረው ትውውቅ የፖለቲካና የኢኮኖሚክስ ምክር በመለገስ ለስርአቱ መሻሻል እንዲያደርጉ በማገዝ ያደረገው ጥረት ምንም ውጤት ሊያስገኝ ካለመቻሉም በላይ የዚህን ሃገር ወዳድ ምሁር እንቅስቃሴ በቅጡ ባለመረዳት በግዜው እኔን ጨምሮ በተቃውሞው ጎራና በነጻ ሚድያው የተሰለፍነው ፤ በአድርባይ ምሁርነትና ፤ በጥገኛ ከበርቴነት ቁም ስቅሉን በትችትና ከዛም በዘለለ መደዴ ቃላት እንወቅሰው የነበረውን ሁሉ በመቋቋም በትግዕስትና በስክነት ቆይቶ ያ በታሪካችን የሚዘከረውን የዲሞክራሲና የነጻነት ማዕበል ካንቀሳቀሱት የቅንጅትና የሕብረት ጎምቱ ፖለቲከኞች አንዱና መሪ ተዋናይ በመሆን በተለይ ለሕዝብ በቀጥታ ይተላለፍ በነበረው የቴሌቭዥን ስርጭት የወያኔን ሹማምንት ድንቁርና በማስረጃና በትንተና እያጋለጠ ዶ/ር ብርሃኑ ያሳየው ምሁራዊና ሕዝባዊነት ታሪክ ይማይዘነጋው ሃቅ ነው።
ዶ/ር ብርሃኑ በሰላማዊ መንገድ በምርጫ ስርዐት ሕዝብ የስልጣን ባለቤት ይሆናል ከሚል እምነት በመንሳት በዲሞክራሲያዊ ሂደት ለውጥ ሊያመጣ ከጓዶቹ ጋር ያደረገው ትግል ፤ በቀማኛውና በሕገ አራዊቱ የዳቢሎስ የግብር ልጅ የሆኑት ወያኔዎች ሠብአዊነት የራቃችው የሠላምን መንገድ የዘነጉ ፤ በድንቁርና ተውጠው እሳቤያቸውን ሁሉ ባነገቱት ጠመንጃ ባደረጉ ወንበዴዎች የዶ/ብርሃኑ የሰላም ጉዞ ጨንግፎ ፤ ለሰላማዊና ዲሞክራሲያዊ ትግል የተደርገው ጥረት የማታ ማታ ውጤቱ ለብዙዎች ሞት ለሺዎች እስርና ስደት ከማትረፉም በላይ ለማያቋርጥ ጥቃትና በደል የሚዳርግ ማህብራዊ መገለልንና በማስፈን የማያላውስ የጭቆና አገዛዙን በማስፈኑ ፤ ትዕቢት ያደነደናቸውን ሃገር ሻጮችና ጠባብ ዘራፊ ዘረኞች ለማስወገድ ግድ ያላውን የምርጫዎች ሁሉ መጨረሻ ፤ ከመፍትሄዎች ሁሉ መዳረሻ የሆነውን የብረት ትግል ሊያስተባብር ሊታገልና ሊያታግል እነሆ የሞቀ ቪላውን የምቾት ኑሮውን ትቶ ድንጋይ ትራሱ ዳዋ ልብሱ ኮቾሮ ጉርሱ አድርጎ በጡረታ እድሜው ለሃገርና ለወገን ሲል ወስኖ በርሃ ወርዷል።
የዶ/ር ብርሃኑ ነጋ ወደ በርሃ መውረድ በዕርግጥ ሕሊና ላለው ለዚህ ትውልድ ሃፍረት ነው ፤ በችግር እሳት የሚገረፈው በሃገር አልባነት የሚሠደደው ፤ ሰርቶ የመኖር ነግዶ ማትረፍ ያልቻለው ፤ ባለግዜዎች ላቆሙት የዘር ጣዖት ካልሰገደ እንድባይተዋር ለሚታይው ፤ የባርነት መርግ የግፍ አገዛዝ የተጫነው ዘረኞች በጎጥ ተጠራርተው በሚከብሩብት ፤ ደናቁርት የስልጣንና የጥቅም ምንጮችን በተቆጣጠሩበት መኖር አይደለም ተስፋ ማድረግ እንኳ በማይቻልበት ሃገር እየኖረ ያለው ይህ ትውልድ ፤ ለመብት ለነጻነቱ ዋጋ መክፈል እያለበት ፀጥ ያለው ፤ እየሞተ የሚፈራውን እየተራበ የሚስቀውን ፤ እየዘፈነ የሚሰደደውን ፤ ከዚህ አስከፊ ሰው በላ አገዛዝ ለመላቀቅ ወኔ ያጠረውን ፤ ይህ የኔ ትውልድ ፤ ለመታደግ ብርሃኑ የወሰድው እርምጃ የሚያኮራ ቢሆንም ፤ እኛ የዚህ ትውልድ አባላት የዚህን ምሁርና ባለጸጋ ፤ ምንም ሳያጣ የእኛን ችግር ችግሩ አድርጎ ከጨካኞች መዳፍ ሊያላቅቀን በተምሳሌትነት ሁሉን ትቶ በርሃ የወረደውን መሪ ፈለግ በመከተል ን ለመብታችን ለመፋለም እንነሳ ዘንድ ለራሳችን ቃል መግባት ይኖርብናል።
ይህ ትውልድ ከዶ/ር ብርሃኑ ከቶስ ምን ይማራል? ይህ ሰው ታላቅ ምሁርና ባለጸጋ ሲሆን ለሃገርና ፤ ለዚህ ትውልድ ሲል ሃብት ፤ንብረቱን ፤ማዕረግ ፤ ክብሩን፤ የደመቀ የአሜሪካ ቅንጡ ኑሮውን ፤ ልጆችና ሚስቱን ፤ ብቻ ሁሉን ትቶ በርሃ ወረደ ። ይህ ትውልድ በሃገሩ ለመኖር መብት ነጻነትና የስራ እድል አጥቶ በሊብያ እንደክብት እንዲታረድ ፤ በደቡብ አፍሪካ እንደቆሻሻ እንዲቃጠል ፤ በሳውዲና በየመን እንደውሻ ተቆጥሮ እንዲገላታ ሃገር አሳጥቶ ያሰደደው አዋርዶ ያዋረድው የሸጠና የለወጠው ፤ በሃገሩም ተምሮ ድንጋይ አንጣፊ አንገት በመድፋቱ ፈሪ ተደርጎ ከሃገሩ ሃብት የበይ ተመልካች በመሆን የቀንና የሌት ህልሙ ነገ ምን በልቼ እውል ይሆን በሚል ተለውጦ ኑሮ ዳግት ሆኖብህ በዘር ሚዛን ከስራው እድል እየተገፋህ እነታሪኬ ባጭሩ በዘርና በፖለቲካ ታማኝነት ሁሉን ማድረግ ሲችሉ፤ በብርሃን ፍጥነት እነ እንቶኔ ኢንቨስተር ሆነው ቤትህን በላይህ እያፈረሱ ከከተማ ሲያባርሩህ ከቀበሌ እስከ ቤተመንግስት የአንድ ቋንቋ ተናጋሪ ሹማምንት በታማኝነት እየተሾሙብህ ሰርቶ የመኖር ነግዶ የማትረፍ መብትህ በነዚህ ወራሪ የወያኔ አፓርታይድ ጉጅሌዎች ጫማ ተደፍጥጦ እስከመቼ ትኖራለህ!
ወያኔዎችን ወደ ኋላ ሄደህ ታሪካቸውን ብታጣራ ካንተ ያልተሻሉ ለመማርና ለመስልጠን የማይመቹ የአቦጊዳ ሽፍቶች ፤ የባንዳ ልጆችና ቁሳዊና መንፈሳዊ ድሆች ከገላቸው እድፍ ከጎፈሬያቸው ተባይ ውጭ እንኳን አንተን እያስራቡ እነሱ ጮማ ሊቆርጡ ደረቅ ጋቤጣ እንኳ ብርቃቸው የነበረች ቁጭራወች ዛሬ ሃገርህን ወረው ከእናትህ መዐድ በእኩልነት እንዳትቋደስ እጅህን እያሳጠሩ ኑሮህን የመከራ ያደረጕትን የቀን ጅቦች ልትፋለም በምትችለውና ባለህ አቅም ሁሉ እንድትንቀሳቀስ ታሪክ ሃይማኖት ሰው የመሆን ሞራል ግድ ይሉሃል። ወጣቱ ሆይ ዶ/ር ብርሃኑን የመሰል ሊቅና በሳል መሪ እግዚያብሄር አድሎህ ይህን የፋሽስት የሌባና የዘረኛ መንጋ በግዜ ለማስወገድ ካልተነሳህ ተስፋ የሌለህ በመሆኑ በሞራል በወኔና በቆራጥነት ክብርህን ልታስመልስ በቀለም ይሁን በፍራፍሬ አብዮት ፤ በሰላም ይሁን በአመጽ ፤ በጓንዴ ይሁን በጎራዴ ፤ በኤርትራ ይሁን በኡጋዴ ፤ በድግምት ይሁን በቃልቻ ፤ ብቻ በምትችለውና በማንኛውም መንገድ የትግሬ ነጻ አውጭ (ሕወሃት) በሚባለው ወሮበላ የሌባና የባዕዳን ቅጥረኛ ስብስብ ላይ ክንድህን ታነሳ ዘንድ ግዜውና ሁኔታው ግድ ይሉሃል።
ይህ ደግሞ
ይቻላል! ተችሏልም! መቻልም አለበት!!!

No comments:

Post a Comment