Tuesday, May 21, 2013

ባህርዳር ጅንአድ ግቢ ውስጥ አንድ መጋዘን በእሳት ተቃጠለ (ቪዲዮውን አያይዘነዋል ተመልከቱት)


የከተማዋ ነዋሪ ርብርብ በማድረግ ላይ ይገኛል፡፡
በባህር ዳር የሚገኘው የጅንአድ የእጣን ማከማቻ መጋዘን እየተቃጠለ ነው፡፡
 ከአየር ሀይል ከአድማ ብተናና ከከተማ አስተዳደሩ የተውጣጡ የእሳት አደጋ ሰራተኞች እየነደደ ያለውን መጋዘን ለማጥፋት እየተረባረቡ ቢሆንም የእጣኑ መጋዘን ነዲድ እየጨመረ ከአቅም በላይ ሆንዋል፡፡
የተቀጣጠለው መጋዘን በውስጥ በኩል እየነደደ በመሆኑ ለመቆጣጠር አስቸጋሪ ከመሆኑም በላይ ወደ ትልቁና ወደ ዘይት ማከማቻው ሊዛመት ይችላል በሚል ተሰግቷዋል፡፡
የቃጠሎውን ምክንያት በምን እንደሆነ  አልታወቀም፡፡
የባህር ዳር ጅንአድ በአገሪቱ ካሉ ጅንአዶች 10 ትልልቆች አንዱ ነው፡፡

No comments:

Post a Comment