Sunday, July 28, 2013

! …. የህወሓት የድሮ ታጋይ ‘አሸባሪ’ ተባለ ….! Abraha Desta

ስዒድ አሕመድ ይባላል። የድሮ የህወሓት ታጋይ ነው። በትጥቅ ትግሉ ወቅት የትግራይ ህዝብ ለትግሉ በማነሳሳትና ትግሉ በመምራት ከመጀመርያ እስከ መጨረሻ ግንባር ቀደም ሚና ተጫውቷል።
የደርግ ስርዓት ከተገረሰሰ በኋላ እንደሌሎች ታጋዮች ከውትድርና ተቀንሶ በግል ስራ ተሰማርቶ ህይወቱ ሲመራ ቆየ። ባለፈው ሓሙስ (ሓምሌ 18) የፌደራል ፖሊሶች የትጥቅ መሳርያው እንዲያስረክብ ይጠይቁታል። ስዒድ ደግሞ አሁን ምንም ዓይነት መሳርያ እንደሌለውና የድሮ ትጥቁ ደግሞ ከዓስር ዓመት በፊት በሕጋዊ መንገድ ለመንግስት አካላት ማስረከቡ በማስረጃ ያስረዳል። ፖሊሶቹም ‘በሽብር ተጠርጥረሃል’ በሚል ሰበብ ዓፍነው ይወስዱታል።

የስዒድ ቤተሰቦች ከስራ ቦታው በፖሊሶች ታፍኖ መወሰዱ እንጂ ወዴት እንደወሰዱት (የት እንደታሰረ) ስላላወቁ ከሦስት ቀናት ፍለጋ በኋላ ትናንት (ቅዳሜ) ማታ በኲሓ ታስሮ እንደሚገኝ ለማወቅ ቻሉ። ስዒድ በምን ይሆን የታሰረው?
ስዒድ በትጥቅ ትግሉ የነበረውን ድፍረት ተጠቅሞ ባለፈው የሙስሊሞች የመጅሊስ ምርጫ በቀበሌ ሳይሆን በመስጊድ መከናወን እንዳለበት ጠንከር ያለ አስተያየት ሰጥቶ ነበር። ከዛ በኋላ የመንግስት አካላት ስዒድን ለማሰር ምክንያት ሲያፈላልጉ እንደነበር ለማወቅ ተችሏል።
ስዒድ ለምን ነበር የታገለው? ወይ ወላዲት ትግራይ ዝረከብክዮ መዓት!
It is so!!

No comments:

Post a Comment