Saturday, July 27, 2013

ትዝታ ዘ ባንዲራ፤ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የዘቀዘቁት ባንዲራ

abe Tokichaw

ትላንት በሙስሊም ኢትዮጵያውያን ተቃውሞ ላይ ኢቲቪ አንድ ግለሰብ የሆነ ነገር ሲያውለበልብ አሳየንናተቃዋሚዎቹ ለባንዲራ የሚሰጠውን ክብር በማንቋሸሽ የተቀዳደደ ባንዲራ ሲያውለበልቡ ነበር ብሎ አሳየን… 1 ሰውዬ የተቃዋሚዎቹ ተወካይ ስለመሆኑ ምንም ማስረጃ የለም፡፡ 2 የያዘው ነገር ባንዲራ ስለመሆኑም መለየት አልተቻለኝምየሆነ ሆኖይቺ ዜና ወሬ ከየት ትዝ እንዳለችኝ እንጃላቷድጋሚ አትሜያታለሁ….

ጤና ይስጥልጅ ወዳጄ እንዴት አሉልኝ። ጤና ኑሮ ሁሉ አማን ሁሉ ሰላም ነው? የኔ ነገር መቼም ሰሞኑን ሳቀርባቸው የነበሩ አጫጭር ጨዋታዎች አንድም ግዜ እንኳ ሰላም ሳልልዎት ቀጥታ ወደ ወሬዬ ስገባእንዴት ያለው ወሬኛ ወጥቶታል!?” ብለው ሳይታዘቡኝ አይቀሩም። ለዚህ ነው ዛሬም ሌላ ትዝብት ሳይከተለኝ ቀድሜ ሰላምታ ያቀረብኩት።ምናለ ሁሉ ሰው እንዳተ ከጥፋቱ ቢፀፀትይበሉና ያኩሩኝ እንጂእኔ የምልዎ ወዳጄ እኒህ ጠቅላይ ሚኒስትራችን ከዚህ በፊት ባንዲራንጨርቅብለውት አስኮርፈውን አልነበር? ከዛ በስንት ግዜውየባንዲራ ቀንብለው አሳውጀው ክብረ በዓል ክብረ በዓል ሲያንበሻብሹን ህዝቡበአስራ ምናምን አመታቸውም ቢሆን እንኳን ተፀፀቱብሎ ይቅር ብሏቸው ሲያበቃ፤ አሁን ደግሞ ሰው አያየኝም ብለው ነው መሰል፣ በጎረቤት አገር ኬኒያ ባንዲራውን እንዴት እንዴት እንደዘቀዘቁት ተመለከቱልኝ?

አይዬእኚህ ሰውዬ ምን እየነካቸው እንደሆን እንጃ? ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነውብኝ እንጂ (አድሮ ቃሪያ ሆኑሳ! ብዬ ብተርትባቸው ደስታዬ ነበር።)

የምር ግን ጠቅላይ ሚኒስትራችን ምን እየነካቸው ነው እንዲህ ህዝባቸው እንደ አይኑ የሚያየውን ነገር ሁላ ማጣጣል እና ማንቋሸሽ የሚቀናቸው። አንዳንድ በነገሩ ብስጭት ያሉ ግለሰቦች ምን እያሉ እንደሚናገሩ ሰምተውልኛል? “አቶ መለስ ልክ እኛን በጠቅላይ ሚኒስትርነት መጠቅለል የጀመሩ ግዜ እርኩስ መንፈስ ደግሞ እርሳቸውን ጠቅሏሏቸዋል!” እያሉ እየተናገሩቸው እኮ ነው።

ባንዲራ የሀገራችን ሰው በጣም የሚያከብረው ትልቅ ዋጋ የሚሰጠው ነገር ነው። (እኔ ራሴ አሁንነገር ነውስላልኩ ህዝቤን ይቅርታ ጠይቃለሁ።) የኛ ሰው ሲለምን እንኳአረ በባንዲራው…” ብሎ ከጠየቀየለኝምአይባልም። በአዲሱ የባንዲራ አዋጅ ሳይከለከል አይቀርም እንጂ፤ ህዝቡ ባንዲራውን ከመውደዱ የተነሳ በሰርጉ፣ በለቅሶው፣ በቤት ምርቃቱ ሁሉ አይለየውም።

በነገራችን ላይ አዲሱን የባንዲራ አዋጅ ጠንቅቀው ያውቁታል? (ይሄኔ በሆድዎበየቀኑ አዳዲስ አዋጅ ይወጣልና ስንቱን አውቀዋለሁ? ብለው ሊጠይቁኝ እንደሚችሉ እጠረጥራለሁ።) የምርም ግን አገራችን በኢኮኖሚ እድገት ብቻ ሳይሆን በአዋአጅ እድገትም ከሌሎች አገራት ጋር ስትነፃፀር ታላቅ እመርታ እያሳየች እኮ ነው። የመያድ አዋጅ፣ የሽበርተኞች አዋጅ፣ የመሬት አዋጅ የባንዲራ አዋጅየወዘተ አዋጅ… (ይህንን ልብ ያለ አንድ ወዳጄ ምን አለ መሰልዎ…? ይቺ ሀገር ከዚህ በፊት በምን ነበር የምትተዳደረው…? ብሎ ጠይቆናል። አንድ ችኩል መላሽ ታድያበግብርናብሎ መልሶለታል።

በሰንደቅ አላማው አዋጅ በርካታ ነገሮች ተካተዋል። አብዛኛዎቹ በኮከቧ ለይ ያጠነጠኑ ሲሆኑ፤ በጥቅሉ ግንባንዲራን ያዋረደ ይዋረዳልአይነት ትርጉም አለው።

እና ታድያ ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ አዲሱ አዋጅም ህዝቡም እንዲህ የሚያከብረውን ሰንደቅ እየደጋገሙ ክብሩን ዝቅ ማድረግ ምን ይሉት ፈሊጥ ነው…? ደሞስ ሰሊጥ እንጂ ፈሊት ኤክስፖርት አይደረግ፣ አይለጠለጥ፣ አየሸጥ፣ አይለወጥ…! እውነቴን እኮ ነው በአጉል ፈሊጥ ከህዝብ ጋር ከመቀያየም አራዳ መሆኑ አይሻልም ይላሉ ወዳጄ? ለነገሩ እርድናውስ ከየት ይመጣል? ነገር ግን ቢያንስ ምክር በመስማት አራዳ መሆን ይቻላል።

አረ ጎበዝ፤ ጠቅላይ ሚኒስትሩን መክሮ አራዳ የሚያደርጋቸው፤ አንድ ሰው እንዴት ይጠፋል? አስቲ በቅርብ የምታገኟቸው ከሰሙ በምክር ካልሰሙ በአሽሙር ንገሯቸው፤ ለነፍስ ይሆናችኋል።

እውነቴን እኮ ነው፤ መቼም ጆሮ ለባቤቱ ባዳ ነው። የሳቸውንም ጆሮ ደፍረን ባዳ ነው ባንለው እንኳ ቢያንስ ግንያኮረፈ ዘመድከመሆን አያመልጥም እና፤ ስለርሳቸው የሚባለውን በሙሉ አጥርቶ የሚሰማላቸው አልመሰለኝም።

ቢሰሙማ ኖሮ ቢያንስ ትንሽ ትንሽ ጥንቃቄ ያደርጉ ነበር። ይህው ባለፈው ሰሞን አያታቸው፤ የአቶ ዜናዊ አባት የሆኑት አቶ አስረስ ለጣልያን በባንዳነት አገልግለዋል። የሚል በፎቶ የተደገፈ መረጃ በፌስ ቡክ ላይ ተለጥፎ ነበር። ይህንን ተከትሎም ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተደጋጋሚ ያሳዩዋቸው ያልተገቡ ባህሪያት ከዛ የተነሳ ነው ብለው የሚጠረጥሩ በርካቶች አስተያየት ሰጪዎች መጥተዋል።

ለምሳሌ ከኤርትራ ጋር ያንን ሁሉ ጦርነት አድርገን ስናበቃ ራሳችን ባሸነፍነው ጦርነት ባድመ ስትሰጥ ዝም ማለታቸው፣ ከዛ በፊትም ቢሆን አሰብን ያህል ወደብ ለመከራከር የሚያስችላቸው በርካታ ታሪካዊ ማስረጃዎች እየነበሩዋቸውግመል ውሃ አጠጡበትብለው እንደዋዛ መተዋቸው፣የአክሱም ሀውልት ለደቡብ ምኑ ነው?” ብለው ህዝብ እና ህዝብን ማራራቃቸው፣ ባንዲራን ጨርቅ ነው ማለታቸው፣ አሁን ደግሞ ይለይላችሁ ብለው፤ ባንዲራውን መዘቅዘቃቸውይሄንን ሁሉ ከአያታቸው አቶ አሰረስ ጋር እያያዙት አሁንም ሰውዬው ሀገሪቷን ጥምድ አድርገገው ከያዙ ጥቅመኛ ባንዳዎች ጋር እያመሳሰሏቸው ነው። ቀድሞ ያደረጉትን እንኳ ይሁን ጉርምስናም ጉልምስናም ይዟቸው ነበር ብለን እናስብ…!

ይሄ የሆነው ግን አሁን በቅርቡ ነው። ኬኒያ፣ ደቡብ ሱዳን፣ እና የኛይቱ ኢትዮጵያ ላሙ የተባለ የጋራ ወደብ ለመገንባት ኬኒያ ላይ ተገናኝተው ነበር። እንግዲህ በዚህ ዝግጅት ላይ ነበር ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትራችን ክቡሩን ባንዲራ (ለዛውም ኮከብ ያለበትንምን ያስቅዎታል?) እውነቴን ነውኮ አዲሱ የባንዲራ አዋጅኮከብ የሌለው ባንዲራ መያዝ ነውር ነውብሎናል…! በርግጥ በዛው ልክ ባንዲራውን መዘቅዘቅም ነውር ነው። እርሳቸው ግን ዘቅዝቀው ይዘውታል።

እስከ ዛሬ ድረስ እንደምናውቀው ባንዲራ የሚዘቀዘቀው ወይም የሚቃጠለውና የሚቀደደው በሀገሩ መንግስት ላይ ተቃውሞን ለመግፅ ነበር። ታድያ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ህዝቡን ነው የራሳቸውን መንግስት ነው የሚቃወሙት…!?

ልቦና ይስጣቸው ወይም ሌላ የሚወዱት ሀገር እና የሚወዱት ባንዲራ ይስጣቸው ብዬ በአንድ እግሬ ቆሜ እፀልያለሁ! ያግዙኝ ወዳጄ!

በመጨረሻም

ይሄን ጉድ አየህው?” ብሎ ፎቶግራፉን የላከልኝን የልብ ወዳጄ ሲሳይን አመስግኑልኝ።

ትዝታ ባንዲራ፤ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የዘቀዘቁት ባንዲራ

ትላንት በሙስሊም ኢትዮጵያውያን ተቃውሞ ላይ ኢቲቪ አንድ ግለሰብ የሆነ ነገር ሲያውለበልብ አሳየንናተቃዋሚዎቹ ለባንዲራ የሚሰጠውን ክብር በማንቋሸሽ የተቀዳደደ ባንዲራ ሲያውለበልቡ ነበር ብሎ አሳየን… 1 ሰውዬ የተቃዋሚዎቹ ተወካይ ስለመሆኑ ምንም ማስረጃ የለም፡፡ 2 የያዘው ነገር ባንዲራ ስለመሆኑም መለየት አልተቻለኝምየሆነ ሆኖይቺ ዜና ወሬ ከየት ትዝ እንዳለችኝ እንጃላቷድጋሚ አትሜያታለሁ….

ጤና ይስጥልጅ ወዳጄ እንዴት አሉልኝ። ጤና ኑሮ ሁሉ አማን ሁሉ ሰላም ነው? የኔ ነገር መቼም ሰሞኑን ሳቀርባቸው የነበሩ አጫጭር ጨዋታዎች ላይ አንድም ግዜ እንኳ ሰላም ሳልልዎት ቀጥታ ወደ ወሬዬ ስገባእንዴት ያለው ወሬኛ ወጥቶታል!?” ብለው ሳይታዘቡኝ አይቀሩም። ለዚህ ነው ዛሬም ሌላ ትዝብት ሳይከተለኝ ቀድሜ ሰላምታ ያቀረብኩት።ምናለ ሁሉ ሰው እንዳተ ከጥፋቱ ቢፀፀትይበሉና ያኩሩኝ እንጂ

እኔ የምልዎ ወዳጄ እኒህ ጠቅላይ ሚኒስትራችን ከዚህ በፊት ባንዲራንጨርቅብለውት አስኮርፈውን አልነበር? ከዛ በስንት ግዜውየባንዲራ ቀንብለው አሳውጀው ክብረ በዓል ክብረ በዓል ሲያንበሻብሹን ህዝቡበአስራ ምናምን አመታቸውም ቢሆን እንኳን ተፀፀቱብሎ ይቅር ብሏቸው ሲያበቃ፤ አሁን ደግሞ ሰው አያየኝም ብለው ነው መሰል፣ በጎረቤት አገር ኬኒያ ባንዲራውን እንዴት እንዴት እንደዘቀዘቁት ተመለከቱልኝ?

አይዬእኚህ ሰውዬ ምን እየነካቸው እንደሆን እንጃ? ጠቅላይ ሚኒስትር ሆነውብኝ እንጂ (አድሮ ቃሪያ ሆኑሳ! ብዬ ብተርትባቸው ደስታዬ ነበር።)

የምር ግን ጠቅላይ ሚኒስትራችን ምን እየነካቸው ነው እንዲህ ህዝባቸው እንደ አይኑ የሚያየውን ነገር ሁላ ማጣጣል እና ማንቋሸሽ የሚቀናቸው። አንዳንድ በነገሩ ብስጭት ያሉ ግለሰቦች ምን እያሉ እንደሚናገሩ ሰምተውልኛል? “አቶ መለስ ልክ እኛን በጠቅላይ ሚኒስትርነት መጠቅለል የጀመሩ ግዜ እርኩስ መንፈስ ደግሞ እርሳቸውን ጠቅሏሏቸዋል!” እያሉ እየተናገሩቸው እኮ ነው።

ባንዲራ የሀገራችን ሰው በጣም የሚያከብረው ትልቅ ዋጋ የሚሰጠው ነገር ነው። (እኔ ራሴ አሁንነገር ነውስላልኩ ህዝቤን ይቅርታ ጠይቃለሁ።) የኛ ሰው ሲለምን እንኳአረ በባንዲራው…” ብሎ ከጠየቀየለኝምአይባልም። በአዲሱ የባንዲራ አዋጅ ሳይከለከል አይቀርም እንጂ፤ ህዝቡ ባንዲራውን ከመውደዱ የተነሳ በሰርጉ፣ በለቅሶው፣ በቤት ምርቃቱ ሁሉ አይለየውም።

በነገራችን ላይ አዲሱን የባንዲራ አዋጅ ጠንቅቀው ያውቁታል? (ይሄኔ በሆድዎበየቀኑ አዳዲስ አዋጅ ይወጣልና ስንቱን አውቀዋለሁ? ብለው ሊጠይቁኝ እንደሚችሉ እጠረጥራለሁ።) የምርም ግን አገራችን በኢኮኖሚ እድገት ብቻ ሳይሆን በአዋአጅ እድገትም ከሌሎች አገራት ጋር ስትነፃፀር ታላቅ እመርታ እያሳየች እኮ ነው። የመያድ አዋጅ፣ የሽበርተኞች አዋጅ፣ የመሬት አዋጅ የባንዲራ አዋጅየወዘተ አዋጅ… (ይህንን ልብ ያለ አንድ ወዳጄ ምን አለ መሰልዎ…? ይቺ ሀገር ከዚህ በፊት በምን ነበር የምትተዳደረው…? ብሎ ጠይቆናል። አንድ ችኩል መላሽ ታድያበግብርናብሎ መልሶለታል።

በሰንደቅ አላማው አዋጅ በርካታ ነገሮች ተካተዋል። አብዛኛዎቹ በኮከቧ ለይ ያጠነጠኑ ሲሆኑ፤ በጥቅሉ ግንባንዲራን ያዋረደ ይዋረዳልአይነት ትርጉም አለው።

እና ታድያ ጠቅላይ ሚኒስትሩ፤ አዲሱ አዋጅም ህዝቡም እንዲህ የሚያከብረውን ሰንደቅ እየደጋገሙ ክብሩን ዝቅ ማድረግ ምን ይሉት ፈሊጥ ነው…? ደሞስ ሰሊጥ እንጂ ፈሊት ኤክስፖርት አይደረግ፣ አይለጠለጥ፣ አየሸጥ፣ አይለወጥ…! እውነቴን እኮ ነው በአጉል ፈሊጥ ከህዝብ ጋር ከመቀያየም አራዳ መሆኑ አይሻልም ይላሉ ወዳጄ? ለነገሩ እርድናውስ ከየት ይመጣል? ነገር ግን ቢያንስ ምክር በመስማት አራዳ መሆን ይቻላል።

አረ ጎበዝ፤ ጠቅላይ ሚኒስትሩን መክሮ አራዳ የሚያደርጋቸው፤ አንድ ሰው እንዴት ይጠፋል? አስቲ በቅርብ የምታገኟቸው ከሰሙ በምክር ካልሰሙ በአሽሙር ንገሯቸው፤ ለነፍስ ይሆናችኋል።

እውነቴን እኮ ነው፤ መቼም ጆሮ ለባቤቱ ባዳ ነው። የሳቸውንም ጆሮ ደፍረን ባዳ ነው ባንለው እንኳ ቢያንስ ግንያኮረፈ ዘመድከመሆን አያመልጥም እና፤ ስለርሳቸው የሚባለውን በሙሉ አጥርቶ የሚሰማላቸው አልመሰለኝም።

ቢሰሙማ ኖሮ ቢያንስ ትንሽ ትንሽ ጥንቃቄ ያደርጉ ነበር። ይህው ባለፈው ሰሞን አያታቸው፤ የአቶ ዜናዊ አባት የሆኑት አቶ አስረስ ለጣልያን በባንዳነት አገልግለዋል። የሚል በፎቶ የተደገፈ መረጃ በፌስ ቡክ ላይ ተለጥፎ ነበር። ይህንን ተከትሎም ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተደጋጋሚ ያሳዩዋቸው ያልተገቡ ባህሪያት ከዛ የተነሳ ነው ብለው የሚጠረጥሩ በርካቶች አስተያየት ሰጪዎች መጥተዋል።

ለምሳሌ ከኤርትራ ጋር ያንን ሁሉ ጦርነት አድርገን ስናበቃ ራሳችን ባሸነፍነው ጦርነት ባድመ ስትሰጥ ዝም ማለታቸው፣ ከዛ በፊትም ቢሆን አሰብን ያህል ወደብ ለመከራከር የሚያስችላቸው በርካታ ታሪካዊ ማስረጃዎች እየነበሩዋቸውግመል ውሃ አጠጡበትብለው እንደዋዛ መተዋቸው፣የአክሱም ሀውልት ለደቡብ ምኑ ነው?” ብለው ህዝብ እና ህዝብን ማራራቃቸው፣ ባንዲራን ጨርቅ ነው ማለታቸው፣ አሁን ደግሞ ይለይላችሁ ብለው፤ ባንዲራውን መዘቅዘቃቸውይሄንን ሁሉ ከአያታቸው አቶ አሰረስ ጋር እያያዙት አሁንም ሰውዬው ሀገሪቷን ጥምድ አድርገገው ከያዙ ጥቅመኛ ባንዳዎች ጋር እያመሳሰሏቸው ነው። ቀድሞ ያደረጉትን እንኳ ይሁን ጉርምስናም ጉልምስናም ይዟቸው ነበር ብለን እናስብ…!

ይሄ የሆነው ግን አሁን በቅርቡ ነው። ኬኒያ፣ ደቡብ ሱዳን፣ እና የኛይቱ ኢትዮጵያ ላሙ የተባለ የጋራ ወደብ ለመገንባት ኬኒያ ላይ ተገናኝተው ነበር። እንግዲህ በዚህ ዝግጅት ላይ ነበር ክቡር ጠቅላይ ሚኒስትራችን ክቡሩን ባንዲራ (ለዛውም ኮከብ ያለበትንምን ያስቅዎታል?) እውነቴን ነውኮ አዲሱ የባንዲራ አዋጅኮከብ የሌለው ባንዲራ መያዝ ነውር ነውብሎናል…! በርግጥ በዛው ልክ ባንዲራውን መዘቅዘቅም ነውር ነው። እርሳቸው ግን ዘቅዝቀው ይዘውታል።

እስከ ዛሬ ድረስ እንደምናውቀው ባንዲራ የሚዘቀዘቀው ወይም የሚቃጠለውና የሚቀደደው በሀገሩ መንግስት ላይ ተቃውሞን ለመግፅ ነበር። ታድያ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ህዝቡን ነው የራሳቸውን መንግስት ነው የሚቃወሙት…!?

ልቦና ይስጣቸው ወይም ሌላ የሚወዱት ሀገር እና የሚወዱት ባንዲራ ይስጣቸው ብዬ በአንድ እግሬ ቆሜ እፀልያለሁ! ያግዙኝ ወዳጄ!

በመጨረሻም

ይሄን ጉድ አየህው?” ብሎ ፎቶግራፉን የላከልኝን የልብ ወዳጄ ሲሳይን አመስግኑልኝ።

No comments:

Post a Comment