Thursday, July 11, 2013

እውነታውና በተግባር ሲተረጎም መልሱ እስር፣ድብደባ፣ከአገር መሰደድ,,,,,,,,,,,,,,,,,,,, በኢትዮጵያ ህገ-መንግስት አንቀፅ 29 ላይ ሀሳብን በነፃነት የመግለፅ መብት ያለገደብ

እውነታውና በተግባር ሲተረጎም መልሱ እስር፣ድብደባ፣ከአገር መሰደድ,,,,,,,,,,,,,,,,,,,,
በኢትዮጵያ ህገ-መንግስት አንቀፅ 29 ላይ ሀሳብን በነፃነት የመግለፅ መብት ያለገደብ

ፕሮፌሰር መስፍን /ማርያም በጋዜጠኛ ተመስገን ክስ ላይ የመከላከያ ቃላቸውን ሰጡ

 ህዝብን ለአመፅ የሚቀሰቅሱ ጽሁፎች ፅፎ አሰራጭቷል ሲል የፌዴራሉ አቃቤ ህግ ክስ በመሰረተበት፤ የቀድሞዋ ፍትህ ጋዜጣ ዋና አዘጋጅ ተመስገን ደሳለኝ ጉዳይ በተመለከተ ፕሮፌሰር መስፍን /ማርያምና በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ የህግ ፋካሊቲ ረዳት ፕሮፌሰር የሆኑት / ያሬድ ለገሰ የተከሳሽ የመከላከያ ምስክር ሆነው በትናንትናው ዕለት ቃላቸውን ለፍርድ ቤቱ አሰምተዋል።የፌዴራሉ አቃቤ ህግ በጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ ላይ ሶስት ክሶችን የመሰረተ ሲሆን፤
1 ክሱ ጋዜጠኛው በቀድሞዋፍትህጋዜጣ ላይሞትን የማይፈሩ ወጣቶችበሚል ርዕስ ስርለምን እንፈራለንየሚል ቀስቃሽ ጽሁፍ ፅፏል ሲል፤ በሁለተኛ ክሱ ላይ ደግሞ
የሁለተኛ ዜግነት ኑሮ በኢትዮጵያበሚል ርዕስ ስር የመንግስትን ስም አጉድፏል ያለ ሲሆን፤
በሶስተኛው ክሱ ደግሞሲኖዶሱና መጅሊሱ የአብዮታዊ ዴሞክራሲ ማጥመቂያዎችበሚል ርዕስ ስር የሁለቱም ሃይማኖት መሪዎች ካድሬዎች ናቸው ሲል ስማቸውን አጉድፏል ሲል ክሱን ይዘረዝራል።
ይህን በተመለከተ የተከሳሹ ጠበቆች፤ ጋዜጠኛው ሀሳብን በነፃነት የመግለፅ ህጋዊ መብቱን ተጠቅሞ የፃፈው ነው ብለው የመከራከሪያ ሀሳብ በማንሳታቸው ፍርድ ቤቱ የመከላከያ ምስክሮችን ቃል ለመስማት ቀጠሮ ይዞ እንደነበር ይታወሳል።

በዚሁም መሰረት ህዝብን ለማሸበር ሞክሯል፤ ፅሁፉን ባዘጋጀበት ወቅት የነበረውን የወቅቱን የአረብ አብዮት ተገን አድርጎ አመፅ ቀስቃሽ ፅሁፎችን ጽፏል የተባለው ጋዜጠኛ ተመስገንን ለመከላከል ምስክር ሆነው የቀረቡት ፕሮፌሰር መስፍን፤የተፃፈው እውነት ነው። እውነት ደግሞ ምንጊዜም ቢፃፍ ለኛም ቢሆን ጥሩ ነውብለዋል። ምክንያት ካልሆነበት በስተቀር ጋዜጠኛ ተመስገን ደሳለኝ የፃፈው ነገር እውነት ነው ብዬ አምንበታለሁሲሉም አክለው የምስክርነት ቃላቸውን ለችሎቱ ሰጥተዋል።

በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ተባባሪ የህግ ረዳት ፕሮፌሰር የሆኑት / ያሬድ ለገሰ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ ያጸደቀቻቸውን እና አለማቀፋዊ ስምምነት የተሰጣቸውን ህጎች እያጣቀሱ ጋዜጠኛው ፅፏቸዋል ተብለው በተጠቀሱትአመፅ ቀስቃሽፅሁፎች ላይ ሙያዊ ትንታኔያቸውን ለፍርድ ቤቱ አሰምተዋል። ምንም እንኳን በኢትዮጵያ ህገ-መንግስት አንቀፅ 29 ላይ ሀሳብን በነፃነት የመግለፅ መብት ያለገደብ የተቀመጠ ቢሆንም ከጋዜጠኝነት ሙያ አኳያም ቢሆን ጋዜጠኛ ተመስገንአመፅ ሊቀሰቅስየሚችል ፅሁፍ ፅፏል ለማለት እንደማይደፍሩ አስረግጠው ተናግረዋል። የፌዴራሉ ከፍተኛ ፍርድ ቤት 16 ወንጀል ችሎት በዚሁ መዝገብ ስር ሶስተኛውንና ቀሪውን የሙያ መከላከያ ምስክር ከጋዜጠኝነት አንፃር ለመመልከት እና የባለሙያውን ቃል ለማድመጥ ለሐምሌ 23 ቀን 2005 . ተለዋጭ ቀጠሮ ሰጥቷል።

No comments:

Post a Comment