Tuesday, September 24, 2013

የነጻነት አቅድ (ባጭሩ)

 የሕብርት መዓብል
 የእምቢታ ሰራዊት
 የነጻንት አዉሎ ንፋስ፤
ዳዊት ጎልያድን ያንጋለለዉ አንድ ጠጠር ድንጋይ በወንጪፍ ወርውሮ ግንባሩን መቶ ነው፤ አንዱን ትልቅ ተራራ አንድ ትንሽ ወንዝ ሸርሽሮ ያፈርሰዋል፤ ስለዚህ የነጻነት ትግል በልዩ ልዩ ዘዴ የሚክናወን ሲሆን ዋና መሳርያዉ የሰፊዉ ህዝብ ትብብር ነው።
፩. ሰላማዊ ሰልፍ በተወሠነ ቦታ ብⶫ መሆን የለበትም፤ ሕዝባዊ ንቅናቄ ሁኖ በተⶫለ መጥን ትቀነባብሮ በየከተማዉ በየመንደሩ በየቀብሌዉ በየሰፈሩ ቢደረግ ለመቆጣጠር አይቻልም፤ በሚልዮን የሚቆጠር ሰራዊት ማዓበል ይሆናል፤ ይሔም ተከታትሎ ያለረፍት በየቀኑ መደረግ አለበት።
፪. የሕዝብን መብትና ነጻነት፤ ሃብቱንና መሬቱን፤ ሞያዉንና ምግባሩን፤ የዓልት እንጀራዉን የሚነሱ፤ ዜግነቱን የሚያሳጡ፤ ከኑሮ ቦታዉ የሚፈነቅሉ፤ ማናቸዉም ድንግጋትና አዋጆች ድርጊቶች በእምቢታ መቃወም፤ ማሰናከል፤ ማፍረስ፤ እንደዚህ ያለ ድርጊት የትም ቦታ በማንም ወገን ላይ ሲፋጸም በአንድነትና ብሕብረት መቃወም። የእምቢታ ሰራዊት ገንቢ ምሆን።

፫. እያንዳንዱ ዜጋ፤ እያንዳንዱ ሕብረሰብ፤ እያንዳንዱ ባለሞያ፤ ይህ የራሴ ጉዳይ ነው፣ ያገሬ ጉዳይ ነው ብሎ በንጹህ ልቦና ይሄንን ትግባር ከፈጸም፣ ማንም ምንም ሊያቆምው የማይችል የነጻነት አዉሎ ንፋስ ተነሳ ማለት ነው፤ ዉጤቱም የማያጠራር ነዉ። ያለ ትግል ያለ ምስዋትነት የሚገኝ ነጻነት የለም።
ችርነቱ ያማያልቅ አምላክ ምህረቱን ይስጥን።
ኢትዮጵያ ለዘላለም ትኑር።
እመሩ ዘለቀ
መስከረም ፪፻፮ ዓም
ኢትዮሚድያ - Ethiomedia.com
September 23, 2013
አምባሳደር እምሩ ዘለቀ

No comments:

Post a Comment