Sunday, September 22, 2013

የእስራኤል ኮማንዶዎች ናይሮቢ ከአሸባሪዎች ጋር እየተዋጉ መሆኑ የእስራኤል የዜና ምንጮች እየዘገቡ ነው።

Woman escapses Nairobi mall attack ናይሮቢ ውስጥ ጭንብል ያጠለቁ ወደ 18 የሚጠጉ ታጣቂዎች አንድ ሰፊ የገበያ አዳራሽን ወረው እያደረሱ ባለው የቦንብ ጥቃት እና የተኩስ ሩምታ ቢያንስ 59 ሰዎች መገደላቸውን የቀይ መስቀል ምንጮች አስታወቁ። የገበያ አዳራሹ በሀገሪቱ ወታደሮች በተከበበት በአሁኑ ወቅት ታጣቂዎቹ አሁንም በአዳራሹ ውስጥ እንደሚገኙ ታውቋል።  ታጣቂዎቹ ዒላማ ሲያደርጉ የነበረው ሙስሊም ያልሆኑ ሰዎችን እየመረጡ እንደነበረም ምንጮቹ አክለው ገልፀዋል። ከጥቃቱ ዘግየት ብሎ ወታደሮች የገበያ አዳራሹን በከበቡበት ወቅትም ታጣቂዎቹ ከውስጥ የተኩስ ሩምታ ሲያሰሙ እንደነበር ተዘግቧል። የሟቾቹ ቁጥር ከ59ም ሊያሻቅብ እንደሚችል ተጠቅሷል።
የኬንያ ፖሊስ ከጥቃቱ ፈፃሚዎች አንደኛውን አቁስሎ በቁጥጥር ስር ማዋሉ ተዘግቧል። ሆኖም የጥቃቱ ፈፃሚዎች በትክክል ከየትኛው ቡድን እንደሆኑ እስካሁን ፖሊስ የሰጠው መግለጫ የለም። የሀገሪቱ መንግሥት ጥቃቱ «ከሽብርተኞች» የተቃጣ ነው ሲል ገልጿል።  ኬንያ ከሁለት ዓመታት በፊት በሶማሊያ የሚገኙ እስልምና አክራሪ ታጣቂዎችን ለመውጋት ጦሯን በላከችበት ወቅት የሶማሊያው ኧል ሸባብ ታጣቂ ቡድን በኬንያ ምድር የሽብር ጥቃት በመፈፀም መበቀሉ እንደማይቀር ዝቶ እንደነበር ይታወሳል።  በዛሬው ዕለት የእእስራኤል ልዮ የኮማንዶ ሀይል በአሸባሪዎች  የታገቱትን   ዜጎችና ቁስለኞችን   ለማስለቀቅ ከአሸባሪዎች ጋር እየተዋጋ እንደሆነና አንዲት ሴት ቁስለኛ  እንዳስለቀቁ የእስራኤል የዜና ምንጮች ዘጉአርዲያንና ሲ ኤን ኤንን ምንጭ አድረገው እየዘገቡ  ነው።

No comments:

Post a Comment