Wednesday, September 25, 2013

አደብና ወደብ ያሳጣን መንግሥት ሲኩራራ ይገርመኛል

           በተለያዩ ዘርፎች የተለያዩ አመለካከቶች ይኖሩናል፡፡ ለፃድቃን ያለንን አመለካከት ለማንም ተራ ሰው መያዝ አንችልም፡፡ አሊያም ለቤተክርስቲያን ያለንን ክብር ለመንግሥት ላይኖረን ይችላል፡፡ እንዴትስ ሊኖረን ይችላል? መንግሥትና ቤተ ክርስቲያን
 የተለያየ አለማትን ለማዉረስ የሚሰሩናቸዉ፡፡ መንግሥትና ቤተ ክርስቲያን የተለያየ አለማትን ለማየት የሚፈልጉ ተቋማት ናቸው፡፡ ቤተ ክርስቲያን ያላትን ይዛ የምትቆይ ዋጋዋም፣ ድርሻዋምየማይለዋወጥ ናት፡፡ ለመንግሥት ይህ ይሆናል ብዬ አላስብም፡፡ ለምሳሌ የአሁኑ መንግሥት ከቀድሞው የመሻል ተፈጥሯዊ ግዴታ አለበት፡፡ ኢ-መደበኛበሆነ አኳኋን ምንም ቢሆን የምንሄደው ወደ
 ፊት ነው ይባላል፡፡ በመሆኑም ኢህአዴግ ተነስቶ “በትራንስፖርቱ ዘርፍ በአፄ ዮሐንስ ዘመነ መንግሥትከነበረው በ1000% አሻሽዬዋለሁ”
 ቢል ቁጥሩ ጉዳይ ሆኖ መነሳት የለበትም፡፡ መነሳት ያለበት “በዘመኑ ትራንስፖርት መች ነበር?” የሚል ጥያቄ ነው፡፡ይህን ጥያቄ ያልጠየቀ ሰው በቀጥታ የኢህአዴግ ወጥመድ ውስጥ መውደቁ አይቀሬ ነው፡፡ ምክንያቱም የኢህአዴግ ትልቁ ችሎታ “የቁጥር 
መረጃ መጋገር”ነውና፡፡በርግጥ “የኢህአዴግን ቁጥር ያመነ ጉም የዘገነ” አንድ ናቸው ማለት እችል ነበር፡፡ ነገር ግን ይህኛው ፍሬ ነገሩን 
‹‹አለመጨበጥ›› ብቻ አድርጎያስቀረዋል፡፡ እናላችሁ 11.2 በመቶ እያደጉ መኖር ከዚህ የተለየ ትርጉም የለውም፡፡ ደግሞ አደግን እንበል፣ 
ኑሮ ተወዶም፣ ህይወት ተወድዳም፡፡ ግን እኮየምናድገው አንዲት የአሜሪካ የዞን ከተማ ከምታድገው ኢኮኖሚ በ11% እና ከዚያ በታች 
በሚያንስ ድምር ነው፡፡ መቼም የህይወታችንን መሻሻልአለመሻሻል ለመገንዘብ የግድ ኢኮኖምክስ መማር አለባቸው የሚል እምነት የያዘዉ የአቶ መለስ መንግሥት “ኑሮ የተወደደው፤ የዋጋ ንረቱ የጦዘውበምናስመዘግበው ተምዘግዛጊ የኢኮኖሚ 
እድገት ነው” ይሉናል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ በተለይ የነኩት ሁሉ ወርቅ እንደሚሆን ሁሉ አሉታዊ የተባሉነገሮች በገጠሙ ቁጥር ዕድል አድርገው 
ያቀርቡታል፡፡ ባለፉት 21 ዓመታት ሁለት ተመሳሳይ ነገሮችን አስተውዬባቸዋለሁ፡፡ አንድኛ ሁሉንም ነገር ወርቅአድርጎ ማቅረቡ ሲሆን ሁለተኛው ደግሞ ሁሌም የሚገኙበት የጠቅላይነት መንበራቸው ነው፡፡
            የኑሮ ውድነት ከተነሳ ዘንዳ አንድ ነገር ልመርቅ፡፡ አንዲት ባለ ግሮሰሪ በአስር ብር ለገዛችው ሳር እንኳን ለቤቷ፣ ለጀበናዋ ት ረከቦትም
የማትሆን ነበረች፡፡ ታዲያ ይህን ያየ እንድ ተጠቃሚ “ወገን ይሄ ደግሞ ምን ቢሆን ነው ዋጋዉ እንዲህ የተሰቀለው? የተመረተው በኛው ሀገር ነው ግን?”
ሲል ጠይቋል፡፡
             አቶ መለስ መንግሥት በትልቁ የሚከሰስበት አንዱ ጉዳይ ብሔራዊ/ሀገራዊ አንድነትንና የብሔር ብሔረሰቦችን መብት ማመጣጠን
ያለመቻሉ ነው፡፡ የአቶ መለስ ቡድን በአመፂ አብዮተኝነት ስልጣን የጨበጠ በመሆኑ ነገሮችን ከባዶ መጀመር መፈለጉ ያስማማል፡፡ ነገር ግን እጅግ በበዛመልኩ የቀድሞውን የብሔራዊ አንድነት መንፈስ በብሔር ብሔረሰቦች መብት ለመገዳደር ስል ሌላኛውን ጫፍ ያዘ፡፡ ይህን ባነሳሁ መጠን በ1960ዎቹእጅግ ተወዳጅ የነበረውን ጨቋኝ ተጨቋኝ /Dependency theory/ ማውራት ይቀናኛል፡፡ አብዮተኞቹ የዚህን ፅንሰ ሀሳብ አንድ አቅጣጫ በመውሰድኤርትራ እንድትገነጠል፣ ሌሎች የኢትዮጵያ ክልሎችም የመገንጠያ የህግ ድጋፍ የሚሆን ህገ 
መንግሥት በመስራት ደመደሙ፡፡ የሰሞኑ የደቡብ ክልልአሉታዊ ብሔርተኝነትም ከዚህ መች ይዘላል፡፡ የአንድ ክልል ርዕሰ መስተዳድር የሆኑትን አቶ ሽፈራዉ ሽጉጤን ‹‹አማሮች ወደ ሀገራችሁ›› ያሰኛቸዉምን ሆኖ ነዉ፡፡
         ዛሬም ድረስ የአሰብ ጉዳይ እንደ አዲስ ያሳስበኛል፡፡ በርግጥ የመለስ ዜናዊ መንግሥት ‹‹የአሰብ ናፋቂ›› ሊለኛ ይችላል፡፡ ሆኖም ዛሬም አሰብሄጄ 
መዝናናት ያምረኛል፡፡ ሞምባሳ፣ አሊያም ሲሸልስ አሊያም ሲንጋፖር ለምን እንደማይናፍቁኝ አላውቅም፡፡ አዎን የመለስ መንግሥት በብሉይ ትንተናቢፈረጀኝና ቢከሰኝም አሰብን ከነ የአሰብ ራስ ገዝ መሬቷ እናፍቃታለሁ፡፡ ይህ ለጅቡቲ በቀን ከ300 ሚሊዮን ዶላር በላይ በመክፈላችንም አይደለም፡፡አሰብ ከነ ግዛቷ የኢትዮጵያ መሆኗን ከልቡናዬ በተጨማሪ ዶ/ር ያዕቆብ ኃ/ማርያምን አንብቤ አሰብን ያሳጣን ህወሓት እንጂ ህግ ያለመሆኑን፣ ተፈጥሮያለመሆኗን በማረጋገጤ ነው፡፡ በነገራችን ላይ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከሚያውቋቸው ሸቀጦች በቀን 300 ሚለዮን የሚያስወጣው ወደብ ብቻ ነው፡፡ ወደብከመግቢያ መውጪያነቱ በተጨማሪ የያዘውን የደህንነት ጥቅም መዘርዘር አያስፈልገኝም፡፡
            አቶ ስብሃት ነጋ የኤርትራ /አሰብ ጉዳይ ከተነሳ ደግሞ ደደቢት እንደሚገኙ አቋም መያዛቸው ይነገራል፡፡ በአጠቃላይ ህወሓት ውስጥ የመለስቡድን የሚባለው “ኤርትራዊነትን” በማበረታታትና በማቀንቀን ይታወቃል፡፡ በአጠቃላይ ‹‹በመቀነስ›› የሚኩራራ
 መንግሥት አለን፡፡ አቶ መለስ ደመሩከተባለ ‹‹ዜሮ ሰም ጌም›› ከማለት አይዘሉም፡፡ መቀነስ ቢያቆሙ ከዜሮ የሚበልጥ ነገር አይደምሩም፡፡ በተቃራኒዉ
 አጤ ምኒልክ በማስፋታቸዉ/በመደመራቸዉ ሠይጣን ተደርገው ይሳላሉ፡፡
           አመራር እንደሚወስን መረዳት ይቻላል፡፡ ‹‹አመራር እዉቀቱ ብቻ ሳይሆን መንፈሱም ይፈለጋል›› ይላሉ የዘረፉ ባለሙያዎች፡፡ መሪዎቻችንለማህበራዊና ስነ ልቡናዊ ብልፅግና ለምን እንደማይጨነቁ ለማሰብ እሞክራለሁ፡፡ ዋናው ነገር በዚህ ዘርፍ ብዙም ያልተሳካላቸው በመሆናቸው
 ለኛምጭንቅ የለባቸውም፡፡ ዴሞክራሲ፣ መልካም ስነ ምግባር፣ ኢትዮጵያዊ ጨዋነት አልተሳኩም፡፡ ህወሓት/ኢህአዴግ በዚህ በኩል ወድቋል፡፡ በመሆኑም
ተቃራኒው ተሳክቷል፡፡ “ስለ መፃህፍት” የተባለ ፕሮግራም ሰሞኑን በአዲስ አበባ ዩኒቨርስቲ ፕሬስ ቀርቦ ነበር፡፡ አንዱ ታዳሚ ‹‹ለተማሪዎቻችን ምንየንባብ ባህል ሰጠንና መልካም አንባቢ እንጠብቃለን” ሲል ለጠየቀው ጥያቄ ዶ/ር ፈቃደ አዘዘ የራሳቸውን አስተያየት ሲሰጡ “9ኛ ክፍል ስማርከተሰጡኝ 13 መፃህፍት አንዱ ዌብስተርስ ዲክሽነሪ ነበር፤ የክፍል ውስጡን በአንድ በኩል
 የመፃህፍቱን በሌላ ትይዩ እያፃፍኩ ነው የማመሳክረው፤በመሆኑም አጠሬራ ይዤ ለፈተና ክፍል አልገባም ነበር” ብለዋል፡፡ ዶ/ር  ፈቃደ በተቃራኒው ቸልታችን ትክክለኛውን ፍሬ ማፍራቱን ተናግረው ነበር፡፡
           በዲሽ ባመጣነው ነገር “ማንቼ አርሴን” አፈራን፡፡ ሀይላቸንን ስራፈት በማድረግ በጫትና በተለያዩ ሱሶች የናወዘ ትውልድ በበቂ ሁኔታማፍራታችን 
ይታወቃል፡፡ ጫት የተስፋ ማጣት፣ በተፈጥሯዊው በራስ ያለመተማመን፣ እንዲሁም የውሸት ሽግግ መሆኑ ይታወቃል፡፡ እንጠጣለን፣አንዳንድ ሰዎች ወጣቱ
 የጫት ትዉልድ ሆኗል ይላሉ፡፡ በኤድስ እንሞታለን እንዘርፋለን፡፡ ቅብዝብዝ ሆነን ምን አደብ አለን፤ አደብ የሚገዛዉ የተረጋጋትዉልድ ነዉ፡፡ በአጠቃላይ አደብም አሰብም ያሳጣን መንግሥት ግን ይኩራራል፡፡

No comments:

Post a Comment