Friday, September 27, 2013

ሰበር ዜና – አንድነት ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮችና አባላት ታሰሩ !

09
የቀድሞው የኢትዮጵያ ፕሬዝዳንትና የአንድነት ፓርቲ ሊቀመንበር ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳና በፓርላማ ብቸኛው የተቃዋሚ ተወካይ አቶ ግርማ ሰይፉን ጨምሮ 26 የአንድነት ፓርቲ ከፍተኛ አመራሮችና አባላት ለአምስት ሰአታት ከታሰሩ ቦሃላ ተለቀዋል። የፓርቲው አመራር አባላት የታሰሩት በአዲስ አበባ ከተማ ቅስቀሳ በተሰማሩበት ውቅት ነው። በጉዳዩ ላይ ያነጋግርናቸው የፓርቲው የህዝብ ግንኙንት ሃላፊ አቶ ዳንዔል ተፈራ ይህ ሁሉ ከፍረህት የመነጨ መፈራገጥ እንደሆነ ገልጸው ከህዝቡ ጋር በመሆን እስከመጨረሻው ስረአቱን እንደሚታገሉ ግልጸዋል።

በፖለስ የታሰሩ አመራሮችና አባላት በከፊል
=========================
ዶ/ር ነጋሶ ጊዳዳ – የአንድነት ፓርቲ ሊቀመንበር
የተከበሩ ግርማ ሰይፉ – የአንድነት ፓርቲ ም/ሊቀመንበር
አቶ ስዩም መንገሻ – የድርጅት ጉዳይ ኃላፊ
አቶ ዳንኤል ተፈራ – የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ
አቶ አስራት ጣሴ – ዋና ጸሃፊ
አቶ ተክሌ በቀለ – የፋይናንስ ጉዳይ ኃላፊ
አቶ ሽመልስ ሃብቴ – የማህበራዊ ጉዳይ ኃላፊ
አቶ ሃብታሙ አያሌው – የህዝብ ግንኙነት ም/ኃላፊ
አቶ ብሩ በርመጂ – የብሔራዊ ምክር ቤት አባል
አቶ አበበ አካሉ – የብሔራዊ ምክር ቤት አባል
አቶ እንግዳ ወ/ፃዲቅ – የብሔራዊ ምክር ቤት አባል
አቶ አለባቸው ነጋሽ – አባል
አቶ መካንንት ብርሃኑ – አባል
አቶ እንዳልካቸው ባዩ – አባል
አቶ ብስራት ተሰማ – አባል
አቶ ወንደሰን ክንፉ – አባል
አቶ ኃይሉ ግዛው – አባል
አቶ ደረጀ ጣሰው – አባል
አቶ ገዛህኝ – አባል
አቶ ባዩ ተስፋዬ – አባል
አቶ ወርቁ – አባል
የአንድነት ፓርቲ አመራሮች በእስር ላይ ቢገኙም የፓርቲው አባላት በተለያዩ የአዲስ አበባ አካባቢዎች በሜጋፎን በመታገዝ የቤት ለቤት ቅስቀሳ እያደረጉ ሲሆን ከፍተኛ ቁጥር ያለው በራሪ ወረቀትም በመሰራቸት ላይ ይገኛል፡፡

No comments:

Post a Comment