Sunday, April 7, 2013

በፌስ ቡክ “ስም አጉድፈሀል” የተባለው ተማሪ በ5 ሺ ብር ዋስ ተፈታ


መጋቢት ፳፰ (ሀያ ስምንት) ቀን ፳፻፭ /

ኢሳት ዜና:-በአዲስ አበባ ሳይንስና ቴክኖሎጂ የመጀመሪያ አመት ተማሪ የሆነው  ማንያዘዋል እሸቱ ለኢሳት እንደገለጠው ከአንድ ሳምንት እስር በሁዋላ፣ የአርባ ምንጭ ፍርድ ቤትስትፈለግ ትመጣለህበማለት 5 ብር ዋስ ለቆታል። ወደ ፈተና ለመግባት ሲዘጋጅ ሶስት ፖሊሶች መጥተው የፍርድ ቤት ማዘዣ በማሳየት እንደወሰዱትና በአርባ ምንጭ እስር ቤት አንድ ሳምንት ማሳለፉን ተማሪ ማንያዘዋል ገልጿል።

ተማሪ ማንያዘዋል፣ አርባ ምንጭ ዩኒቨርስቲ በሙስና መዘፈቁን እንዲሁም በአገሪቱ ያለው የመብት አፈና መጨመሩን የሚገልጽ ጽሁፍ በድረገጽ አውጥተሀል ተብሎ መያዙን ገልጿል
አቃቢ ህግ በቂ ማስረጃ አላገኘሁም በማለቱ እንደተለቀቀ የገለጠው ተማሪ ማንያዘዋል፣ ይሁን እንጅ 5 ብር በሁለት ሳምንት ውስጥ እከፍላለሁ ብሎ ቃል በመግባት በመፈታቱ፣ ይህን ገንዘብ ካልከፈለ ወደ እስር ቤት እንደሚመለስ ተናግሯል። የደሀ ልጅ በመሆኑ ገንዘብ መክፈል እንደማይችል የገለጠው ተማሪ ማንያዘዋል፣ ፍርድ ቤቱ ቶሎ ውሳኔ ቢሰጠው ከጭንቀት እንደሚገላገልም ገልጿል።አሁን ከአሁን መጥተው ይወስዱኝ ይሆንበማለት  ትምህርቱን ተረጋግቶ መማር እንዳልቻለም ተናግሯል።
በጠባብ ክፍል ውስጥ 25  ሰዎች ታስረው እንደነበር፣ ከሙቀቱ በተጨማሪ ቱሁዋን አስቸግሮት እንደነበር አልሸሸገም። ተማሪ ማንያዘዋል ፖሊሶች እና ፍርድ ቤቱ ላደረገለት ትብብርም ምስጋና አቅርቧል።
ተማሪ ማንያዘዋል 4 ነጥብ በማምጣት ዩኒቨርስቲ መግባቱም ታውቋል። በሚማርበት ዩኒቨርስቲም እንዲሁ ከፍተኛ ውጤት እያስመዘገበ አለ 21 አመት ወጣት ነው።

No comments:

Post a Comment